cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Ethio 251 Media

ETHIO 251 is an independent media offering you News, Political Analysis and Information feeds.

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
22 936
Suscriptores
+20624 horas
+6897 días
+2 73730 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Photo unavailableShow in Telegram
አስቸኳይ መረጃ ወደ ጎንደር አይምባ የድሮን ጥቃት ለመፈፀም ትዕዛዝ ወርዷል። ድሮኖች GPS እያነበቡ ነው በሰዓታት ውስጥ ጥቃት ይፈጸማል። ጎጃም መራዊ ሦስት ቦታዎች ደቡብ ጎንደር ስድስት ቦታዎች ማምሻዉን የድሮን ጥቃት ትዕዛዝ ተሰጥቶባቸዋል። አስቸኳይ መረጃ ለሁሉም ይድረስ! ሌሊት ጭምር  ድሮን ጥቃት ይፈጸማል ተብሏል።
Mostrar todo...
👍 99😭 23 4😁 1
ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋና ግፍ እየተከታተለ በመዘገብ የህዝብ ልሳን ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሚዲያው በሚያቀርባቸው መረጃዎች አገዛዙን በማጋለጡ፤ አገዛዙ ሚዲያውን በመዝረፍ፣ ጋዜጠኞችን በማሳደድ እንዲሁም በተደጋጋሚ እና በተደራጀ መልኩ ቻናሎቹን እያዘጋበት ይገኛል፡፡ በዚህ የተነሳም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋት ጦርነት ሰሚ እንዳያገኝ የአገዛዙ ፍላጎትና እቅድ ቢሆንም፤ ኢትዮ 251 ሚዲያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም ለህዝብ ድምጽ በመሆን የአገዛዙን ገመና ያለማቋረጥ እያጋለጠ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን ጦርነት ለመመከትና ህልውናውን ለማስጠበቅ የሚዲያው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያም ይህንን ኃላፊነቱን በመረዳት ባለሙያዎች በመጠናከርና በሁሉም ቀጠናዎች ዘጋቢዎችን በመመደብ እየሠራ ይገኛል፡፡ ይህ ጥረቱም የአገዛዙን ገመና ከማጋለጥም በተጨማሪ፤ የፋኖን እያንዳንዱን የትግል ውሎና ጀብዱ በመዘገብና ሰንዶ በመያዝ ላይ ነው፡፡ ይህን ጥረቱን በተጠናከረ መልኩ እንዲያከናውን የፋይናንስ ድጋፍ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ ስለሆነም ኢትዮ 251 ሚዲያን በዚህ የጎፈንድሚ አካውንት በመደገፍ የአማራን ህዝብ ትግል ይደግፉ ስንል በአክብሮት ጥሪ እናቀርብለዎታለን፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያ!! https://gofund.me/a2d99937
Mostrar todo...
ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media, organized by Ethio251 Zena-Tequam

ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪን እንደግፍ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢ… Ethio251 Zena-Tequam needs your support for ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media

👍 56👎 4
02:13
Video unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ ለአሜሪካ አምባሳደር የተሰጠ ምላሽ። የከበረ ሰላምታ ለሁላችሁም! አሁን ስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ወደ ስልጣን ከመጣ እነሆ ስድስት ዓመታት አለፉ። ታዲያ፣ በእነዚህ ስድስት ዓመታት አማራዎች በብሄራቸው ምክንያት ተነጥለው ተፈርጀዋል፣ በክፉ ተጥላልተዋል፣ ተፈናቅለዋል፣ ተጠቅተዋል፣ በጅምላ ተጨፍጭፈዋል። ይህ ሁሉ የሆነው በክልል መንግስታት ብቻ ሳይሆን፣ እንደያውም በበለጠ በሚያሳስብ ደረጃ፣ በፌደራል መንግስቱ ተዋናይነት ነው። ተመልከቱ፣ ከ 1966ቱ አብዮት ጀምሮ፣ በተለያዩ ብሄር ተኮር ድርጅቶች አማካኝነት አማራዎች በብሄራቸው ምክንያት ላለፉት ሃምሳ ዓመታት ሲጠቁ ኖረዋል። ያለፉትን ስድስት ዓመታት ለየት የሚያደርገው ነገር ፣ የዚህ ብሄር ተኮር ጥቃት ዋና ተዋናይ ራሱ አገዛዙ መሆኑ ነው። ታዲያ፣ እኛ አማራዎች ይህንን የአገዛዙን ጥቃት ለመከላከል ከመነሳት ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረንም። ከታሪክ መማር አለብን። የዘር ፍጅትን ለመፈፀም አቅም ያለው አካል መንግስት ብቻ ነው፤ በተለይ አክራሪ ብሔርተኛ ሆነው የመንግስትን ስልጣን የያዙ ኃይሎች። የምንታገለው እንደ ህዝብ የመኖር መብታችንን ለማስከበር ነው። የመኖር መብት ደግሞ የመብቶች ሁሉ መሰረት ነው። ለዚህ ነው ምንም እንኳን የትግላችን የመጨረሻ መቋጫው ፖለቲካ ቢሆንም፣ አሁን ያለን ትግል ከፖለቲካ በላይ የህልውና ትግል ነው እያልን አጥብቀን የምንናገረው። ስለሆነም፣ እስከአሁን ድርድርን አስመልክቶ ስናራምደው የነበረው አቋም ባለበት የሚቆም ቢሆንም፣ ጥያቄው "በምን መልክ ነው?" የሚል ነው እንጂ፣ በትግሎች ሂደት ድርድር አንዱ የሂደቱ አካል እንደሆነ እንገነዘባለን። በዚህ በኩል የአሜሪካ መንግስት የአማራን ህዝብ የሚወክለውን ፋኖን እና አገዛዙን ለማነጋገር ሁኔታዎችን ለማመቻቸት እየሞከረ ነው። ይህ ጥረት ፍሬ ሊያፈራ የሚችለው ዋና ዋና የፋኖ አደረጃጀቶች ያቀፈ አንድ የአማራ ፋኖ ድርጅት በመጀመሪያ ሲቋቋም ነው። ይህንን ስራ ለማጠናቀቅ ትንሽ ጊዜ ያስፈልገናል። የአማራን ህዝብ ወክሎ በሙሉ ስልጣን ሊናገር የሚችለው እንዲህ ያለው ድርጅት ብቻ ነው። የአሜሪካን መንግስት፣ ብሎም የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ በአጠቃላይ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የዘር ፍጅትን (ጄኖሳይድ) ለመከላከል ስለምታደርጉት ጥረት ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው። ፈጣሪ ከሁላችንም ጋር ይሁን!! እስክንድር ነጋ፣ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ሠራዊት!
Mostrar todo...
👍 70👎 15 10👏 7🙏 1
ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋና ግፍ እየተከታተለ በመዘገብ የህዝብ ልሳን ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሚዲያው በሚያቀርባቸው መረጃዎች አገዛዙን በማጋለጡ፤ አገዛዙ ሚዲያውን በመዝረፍ፣ ጋዜጠኞችን በማሳደድ እንዲሁም በተደጋጋሚ እና በተደራጀ መልኩ ቻናሎቹን እያዘጋበት ይገኛል፡፡ በዚህ የተነሳም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋት ጦርነት ሰሚ እንዳያገኝ የአገዛዙ ፍላጎትና እቅድ ቢሆንም፤ ኢትዮ 251 ሚዲያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም ለህዝብ ድምጽ በመሆን የአገዛዙን ገመና ያለማቋረጥ እያጋለጠ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን ጦርነት ለመመከትና ህልውናውን ለማስጠበቅ የሚዲያው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያም ይህንን ኃላፊነቱን በመረዳት ባለሙያዎች በመጠናከርና በሁሉም ቀጠናዎች ዘጋቢዎችን በመመደብ እየሠራ ይገኛል፡፡ ይህ ጥረቱም የአገዛዙን ገመና ከማጋለጥም በተጨማሪ፤ የፋኖን እያንዳንዱን የትግል ውሎና ጀብዱ በመዘገብና ሰንዶ በመያዝ ላይ ነው፡፡ ይህን ጥረቱን በተጠናከረ መልኩ እንዲያከናውን የፋይናንስ ድጋፍ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ ስለሆነም ኢትዮ 251 ሚዲያን በዚህ የጎፈንድሚ አካውንት በመደገፍ የአማራን ህዝብ ትግል ይደግፉ ስንል በአክብሮት ጥሪ እናቀርብለዎታለን፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያ!! https://gofund.me/a2d99937
Mostrar todo...
ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media, organized by Ethio251 Zena-Tequam

ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪን እንደግፍ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢ… Ethio251 Zena-Tequam needs your support for ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media

👍 36
Photo unavailableShow in Telegram
ዐቢይ አሕመድ የጥፋት እጆች በአፋር በኩል ወደአስመራ… ባለፈው ጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ ዐቢይ አሕመድ  ወደአፋር ተጉዞ የአፋር የጎሳ መሪዎችን  አግንቶ ስለመለያየቱ መረጃዎች መውጣታቸው ይታወሳል። የዐቢይ አሕመድ አንዱ የሴራ ተግባር "አፋርን አንድ አደርጋለሁ" በሚል የጎሳ መሪዎቹን ወደሱ የፖለቲካ ፍላጎት ለመሳብ ማሰቡ ነው። በዚህ ሁኔታ እግሩን የተከለው ዐቢይ አሕመድ የኤርትራ አፋርን በተመለከተ ከሚንቀሳቀሱ የኤርትራ ተቃዋሚዎች ጋር ግንኙነት መጀመሩን ከሰሞኑ የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ። በኤርትራ ደንከልያን -(አፋርን) - በሚመለከት እየተሰማ ያለው የዐቢይ አህመድ የሴራ ፖለቲካ የቀጠናዊ ግጭት ፍላጎቱ አካል ተደርጎ የሚታይ ነው። ቀደም ሲል በዲያስፖራው በኩል በዋናነት ካናዳ እና አሜሪካ ባሉ አንድ “ኤርትራዊ ሀገረ-አፋር በስደት” (Eritrean Afar State in Exile- EASE) የሚባል ዓለም-አቀፋዊ ድርጅት እንደተቋቋመ ይታወቃል። ድርጅቱም ባዘጋጀው ሰነዱ ላይ በይፋ ካስቀመጣቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች አንዱ በዓለም-ዓቀፋዊ ሕግ መሰረት “የአፋር ህዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰንና ራስ ገዝ” ማረጋገጥ የሚል ፖለቲካዊ ሽፋን ያለው በተግባር ግን የኤርትራን ሀገራዊ-ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑ ይታወቃል። በአጠቃላይ የድርጅቱ ዋና ዓላማና ግብ ደንከሊያን በአፋር ተወላጆች ቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረግ ነው ይላል። በዚሁ የአፋር ዓለም ዓቀፋዊ ድርጅት ትልቅ ሚና ከሚጫወቱት አንዱ ፕሮፌሰር ጆዘፍ ማግነት የሚባል ካናዳዊ ነው። ፕሮፈሰሩ የምዕራቡ ዓለም ስለኤርትራ ምን እንደሚያስብ አንዱ ነፀብራቅ ነው። ይህን ፕሮፌሰር የዐቢይ አሕመድ ሰዎች ቀጥረውት በቀጠናው ዙሪያ እያማከራቸው እንደሆነ የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህ የአፋር ዓለም-ዓቀፋዊ ድርጅት ከሚያቀርባቸው ጥያቄዎች አንዱ በብሔር/ጎሳ ፌዴራሊዝም ላይ የተመሰረተ “የብሄር ብሄረሰቦች መብት (ሪጅናል አውቶኖሚ)” ማረጋገጥ የሚል ነው። ይህን የቆየ የምዕራባዊያን ሴራ ዐቢይ አሕመድ ወደሌላ የቀውስ ምዕራፍ ሊያሳድገው በጉዳዩ ላይ ጥናት ሲሰሩ ከኖሩ የምዕራቡ ዓለም ወኪሎች ጋር ሆኖ በአፋር በኩል እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የአፋር ልሂቃን ሆይ፦ በአገር ውስጥ በገጠመው ተቃውሞ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባው ዐቢይ አሕመድ ቀጠናውን ወደአደገኛ ቀውስ ጎትቶ በማስገባት በድንበር ተሻጋሪ ግጭት ሥልጣኑን ማራዘም የፈለገ መሆኑን አውቃችሁ "ወግድ ይሁዳ…!" ልትሉት ይገባል። በአፋር ኢሳ ግጭት ቀጠናውን ሲያውክ የቆየው ነፍሰ በላው ዐቢይ አሕመድ አፋርን ከገዛ ወገኑ ጋር ወደአደገኛ ግጭት ሊከተው የግጭት ድግስ እያዘጋጀለት ነውና አፋር ሆይ እወቅበት።
Mostrar todo...
👍 117 17😁 2🤔 2
Photo unavailableShow in Telegram
ሰበር ዜና! የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ አካል የሆነው ቋራ ኦሜዳድ ክፍለጦር ቋራ ወረዳን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ። ክፍለጦሩ አዳሩን እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሲያደርግ ያደረ ሲሆን በመጨረሻም ሶስት ካምፖችን መደምሰስ መቻሉን የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቃል አቀባይ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል። አሶል አካባቢ የሚገኘ የሚሊሻና የፀረ ሽምቅ ካምፕ፣ ሽመልእግር መውጫ የሚገኝ የአድማ ብተና ካመሰፕ እና አለሙ በር አካባቢ የሚገኝ የመከላከያ ኃይል ካምፕ ሙሉ በሙሉ የተመታ ሲሆን አድማ ብተና፣ ፀረሽምቅና ሚሊሻ እጅ የሰጠው እጅ ሰጥቶ የተረፈው ተደምስሷል ያለው ደግሞ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር አዛዥ ፋኖ ሸጋ ጌታቸው ነው። የክፍለጦሩ አዛዥ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ጨምሮ እንደገለጸውም ራሱን የመከላከያ ኃይል ብሎ የሚጠራው ገዳይ ቡድን ከተመታው እና ከተማረከው የተረፈው ካምፑን ጥሎ በመፈርጠጥ ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን አቅጣጫ ፈርጥጧል ብሏል። በአሁኑ ሰዓት ወደ ኢትዮጵያ አቅጣጫ ያለው መስመሩ የተቋረጠበት ሲሆን አልጣሽ ፓርክ ከመግባትና ወደ ጎረቤት ሱዳን ሀገር ከመሰደድ የዘለለ አማራጭ የለውም ብሏል። የነብስ አውጭኙን በከባድ መሳሪያ ከርቀት እየተኮሰ እየፈረጠጠ እንደሚገኝ እና ፋኖም እየተከተለ እያሳደደው እንደሆነ ሻለቃ ሸጋው ጌታቸው ለሚዲያችን ተናግሯል። በተልዕኮው በቋራ ኦሜዳድ ክፍለጦር ስር የሚገኙ 100 አለቃ ደጀኔ ብርጌድ፣ ነብሮ ብርጌድ እና ዳግማዊ ቴውድሮስ ብርጌድ እየተሳተፋ ይጋኛል ሲል ሻለቃው ተናግሯል።
Mostrar todo...
👏 87👍 40 28🔥 3
Photo unavailableShow in Telegram
"የላስታ ብቻ የጠላት ምሽግ ሰብረነዋል" የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ላስታ አሳምነው ክፍለጦር የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ የላስታ አሳምነው ፅጌ ክፍለጦር ባደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ የላሊበላ አየር ማረፊያን መቆጣጠሩን የላስታ አሳምነው ክፍለጦር ዋና  አዛዥ አምሳ አለቃ ወንድሙ ማሩ ለኢትዮ 251 አስታውቋል! ለረጅም ጊዜ የአገዛዙ ኃይል ምሽግ አድርጎት የነበረችው ከላስታ ወረዳ አንዷ ከተማ የሆነችውና ጠላት በብቸኝነት ተቆጣጥሯት የነበረችው የሹምሽሃ ከተማን ነጻ ማውጣቱን አስታውቋል። የአገዛዙ ኃይልና የላሊበላ ኤርፖርት መቀመጫ የሆነችው ሹምሽሃ ከተማ ከአገዛዙ ነጻ መውጣቷ ድርብ ድል መሆኑን የገለጸው የክፍለጦሩ አዛዡ ሹምሽሃ ከተማ ወይም ላሊበላ ኤርፖርት አገዛዙ ኃይል መሽጎ የነበረ ሲሆን ይሄን ድል ዛሬ ማግኘታችን የአገዛዙን የሰቆጣ አውራ ጎዳና፣ የገለሶት አቅጣጫ፣ የሳርዝና ሚካኤል እና የኩልመስክ አቅጣጫን መንቀሳቀሻውን እንደቆረጥንበት ይታወቅ ብለዋል። በሌሎች ዝርዝር መረጃዎች እንመለሳለን። https://t.me/ethio251media
Mostrar todo...
112👍 61🔥 13👎 1🥰 1😁 1
Photo unavailableShow in Telegram
ፋኖ  የላሊበላ አየር ማረፊያን ተቆጣጠረ! የአማራ ፋኖ በወሎ የላስታ አሳምነው ፅጌ ክፍለጦር  ባደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ የላሊበላ አየር ማረፊያን መቆጣጠሩን የላስታ አሳምነው ክፍለጦር ዋና አዛዥ አምሳ አለቃ ወንድሙ ማሩ ለኢትዮ 251 አስታውቋል!
Mostrar todo...
216👍 59👏 34🔥 17😁 3
14:31
Video unavailableShow in Telegram
የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ዋና አዛዥና ምክትል አዛዡ በወቅታዊ ጉዳይ የወሎ ግንባር ኢትዮ 251 ሚዲያ ዘጋቢ ጋር ልዩ ቆይታ አድርገዋል። ወሳኝ መልዕክቶች ተላልፈዋል፥ ያድምጡት!
Mostrar todo...
👍 158 36👏 2👎 1😁 1