HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 277
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+3830 días
Archivo de publicaciones
=> "ልጆቼ ሆይ! ራሳችሁን መለወጥ ሳትችሉ የሌላን ነፍስ ማዳን ወይንም ሰዎችን መርዳት አትችሉም፤ ነፍሳችሁ በልዩ ልዩ ምስቅልቅል ውስጥ ሆኖም የሌላውን ሰው መንፈሳዊነት ስርዓት ማስያዝ አይቻላችሁም፤ እናንተ ራሳችሁ የውስጥ ሰላም ከሌላችሁ ለሌሎች ሰላምን ማስገኘት አትችሉም፤ ብዙውን ጊዜ የሰዎችን በኛ ምክንያት ለበጎ ነገር መነሳሳትና ነፍሳቸውም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የምናየው ወደ በጎ ይቀርቡ ዘንድ በአፍ በምንነግራቸው ነገር ሳይሆን በእኛ ላይ በተግባር በሚገለጥ የመንፈስ ጸጋና ስጦታ ነው።" (አባ ጊዮርጊስ ዘገስጫ)
=> "ከጸሎት በቀር ንስሐ መግቢያ በር አለ ብሎ የሚናገር ቢኖር እርሱ በሰይጣን የተታለለ ነው።" (ማር ይስሐቅ)
=> "በእውነት ዝናብን እንደምትናፍቅ ደረቅ መሬት እግዚአብሔርን መናፈቅ መጠማት ይህ አይደለምን? ዋላ ወደ ውሃ ምንጮች እንደሚናፍቅ አቤቱ ነፈሴ እንዲሁ ወደ አንተ ትናፍቃለች፥ ነፍሰ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች። መቼ እደርሳለሁ? አምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?።" (መዝ.41-1-2) (አባ ጊዮርጊስ ዘገሰጫ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"የምወደው ልጄ ይህ ነው"
ጌታችን ከሐዋርያቱ መካከል "አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ጴጥሮስ፣ ዮሐንስንም" ወደ ቅዱሱ የታቦር ተራራ ብቻቸውን ይዟቸው ወጣ።(ገላ 2፥9) ከተራራውም ጫፍ ሲደርሱ ሦስቱ ደቀ መዛሙርት የመምህራቸው ፊት እንደ ፀሐይ ሲያበራ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሲሆን ተመለከቱ። እነሆም ከቀደሙት ጻድቃን ታላላቆቹ ሙሴና ኤልያስ በታቦር ተገኝተው ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
እነዚህ የብሉይ ኪዳን ነቢያት የትንቢታቸው ፍጻሜ ከሆነው ክርስቶስ ጋር ምን ተነጋገሩ? መቼም በጊዜው ከጌታ ጋር ውለው ያድሩ እንደ ነበሩት ተማሪዎቹ ሐዋርያት "አትሙትብን" አይሉትም። በሺህ ለሚቆጠሩ ዓመታት ሱባኤ የያዙለትና ደጅ የጠኑት የድኅነት ተስፋ እናዳይፈጸም "ይቅር አትሙት" እንዴት ይላሉ? ስለዚህ ከብሔረ ሕያዋን የመጣው ኤልያስና ከብሔረ ሙታን የመጣው ሙሴ በአንድ ላይ "በኢየሩሳሌም ሊፈጸም ስላለው ስለ መውጣቱ (ስለ መከራው፣ ሞቱ)" ያነጋግሩት ነበር።(ሉቃ 9፥31)
በታቦር ተራራ ላይ የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መልእክተኞች ተገናኙ። በባሕር ላይ በእግሩ የተራመደው ጴጥሮስ፣ የኤርትራን ባሕር እጁን ዘርግቶ የከፈለው ሙሴን አየው።(ማቴ 14፥29፣ ዘጸአ 14፥21) የሰማርያ ሰዎች በተቃወሙ ጊዜ "እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው" ያሉ ያዕቆብና ዮሐንስ፣ ከሰማይ እሳት አዝንሞ ሃምሳ አንዱን ወታደሮች ያስበላ ኤልያስን ተመለከቱት።(ሉቃ 9፥54፣ 2ኛ ነገ 1፥10)
ሁለቱ ምስክሮች እንደ ተሰወሩም ወዲያው ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ ሦስት ዳሶች እንሥራ ብሎ ጌታውን ጠየቀ። ሐዋርያው በዚህ ተራራ ላይ መቅረት የፈለገው ያለ ምክንያት አይደለም። መድኃኒታችን አስቀድሞ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄድ ዘንድ ከሽማግሎችና ከካህናት አለቆች ከጻፎችም ዘንድ ብዙ መከራ ይቀበልና ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲነግራቸው ቅዱስ ጴጥሮስ "አይሁንብህ፤ አይድረስብህ" ሲል ሊከላከለው ሞክሮ ነበር። ለዚህም በጊዜ "ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል" ተብሎ ተገስጾበታል።(ማር 9፥31-33) ይሁን እንጂ አሁንም ቅዱስ ጴጥሮስ ያለውን ሁሉ እድል ተጠቅሞ ጌታን ወደ ኢየሩሳሌም ከመሄድና በካህናት አለቆች እጅ ተላልፎ ከመሰጠት ማስቀረት ስለሚፈልግ "ጌታ ሆይ፦ በዚህ(በታቦር ተራራ) መሆን ለእኛ መልካም ነው" ብሎ ተናገረ።
እርሱም ይህን ገና ሲናገር ሳለ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው። ከደመናው "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት" የሚል ድምፅ መጣ። ሐዋርያቱ ይህን ድምጽ የሰሙት ሙሴ እና ኤልያስ ከክርስቶስ ተለይተው ከሄዱ፣ እነርሱም ወድቀው ከነበሩበት ከተነሡ በኋላ ነው። ይህም ከደመናው ውስጥ ሲወጣ ስለ ሰሙት ቃል "ለማን የተነገረ ይሆን?" ብለው እንዳይጠይቁና ምስክርነቱ ለክርስቶስ ብቻ የተሰጠ መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ እንዲረዱ ነው። በዚሁም ላይ ደመናው ወርዶ የጋረደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ ሳይሆን ሐዋርያቱንም ጭምር ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚነግረን ደመናው ጌታን ብቻ ጋርዶት ቢሆን ኖሮ፣ ሐዋርያቱ "እርሱን ስሙት" የሚለውን ቃል ራሱ ክርስቶስ ለራሱ የተናገረው ሊመስላቸው በቻለ ነበር።
ቅዱስ ጴጥሮስ "አትሙት" ያለው መምህሩን በፍጹም ልቡ ስለሚወደው መሆኑ አያጠራጥርም። ነገር ግን ጴጥሮስ ጌታን የቱንም ያህል ቢወደው፣ ፍቅሩ ግን ከወለደው ከባሕርይ አባቱ ከአብ አይደለም ሊበልጥ ሊነጻጸርም አይችልም። ታዲያ አብ በእርሱ ደስ የሚለው፣ የሚወደው፣ አንድያ ልጁ እንዲሞት ፈቃዱ ከሆነ፣ የአብን ያህል ሊወደው የማችለው አረጋዊው ጴጥሮስ ለምን "አትሙት" እያለ ይቃወማል?!
አብ ምትክ የሌለው ልጁ ወልድ ሰው ሆኖ በክፉዎች እጅ ሲንገላታ እና እስከ መስቀል ሞት ሲደርስ እያየ ዝም ያለው ስለማይወደው አይደለም። ዓለም ያለ ልጁ መከራና ሞት ስለማትድን ነው እንጂ። ከዚህ ምን እንማራለን? ዛሬም ወደ መከራ የምንገባ የጸጋ ልጆቹ የምንሆን እኛ ክርስቲያኖች "እግዚአብሔር እንዲህ ስሆን ዝም ያለኝ ስለማይወደኝ ነው" አንበል። ባገኘን ጥቂት የሥጋ መከራና ሕመም የሚበልጠውን የነፍስ ጤና የምንሸምት ከሆነ እግዚአብሔር ዝም ይላል። ዝም የሚለው መከራችንን ስለማያይ ሳይሆን ከመከራው ጀርባ ያለው ዓላማ ታላቅና የተቀደሰ እንደ ሆነ ስለሚያውቅ ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ያለ ጸሎት ሰይጣን ምን ያደርገኛል እያሉ ለሚፎክሩ | በክርስትና መዘግየት ዋጋ ያስከፍላል | እውነትን ተናግሮ ከመሸበት ማደር | ቀሲስ ሄኖክ ወ/ደማርያም 🔥😭 https://youtu.be/dOLV3OlH81k
Repost from ((ከመንፈሳዊ ውጊያዎች የሚሰጠውን ትምህርት መልቀቂያ ቻናል))
የአጋንንት ሴራ እና ተንኮላቸው!!!
https://youtube.com/watch?v=APU-y3Rz7bU&si=nL87D2vEHNU3YfU1
ታዋቂው ሙዝቀኛ ከተፈወሰ በኋላ የተናገረው | ኦርቶዶክስን አላውቃትም ነበር | የደብረ ታቦር (ቡሄ) ምስጢር | የጸሎታችን ፍሬ ምንድነው? መምህር ግርማ 😱🔥🚩
https://youtu.be/h4D3DORmZbk
ሦስት አይነት ባህሪይ ያላቸው መናፍስቶች || የመተት ዕድሳትን ለማስቆም | የኢትዮጵያውያን ጠቋር ከባድ ነው | መምህር ግርማ ወንድሙ | ተስፋዬ አበራ 🔥😱😭
https://youtu.be/kOjHVEMn60A
=> እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ የመታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!!
=> "በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል..."
ዳን. ፲፪፥፩ /12፥1/
=> በኃይላት መላእክት ላይ የተሾመ መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል።
=> በእብራይስጥ ቋንቋ ሚካኤል ሲተነተን "መኑ ከመ አምላክ፣ ማን እንደ እግዚአብሔር" ማለት ነው።
=> የሰማይ ሰራዊት ሁሉ አለቃቸው፤ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ ይህ ኃያል መልአክ እስራኤል ዘሥጋን ሲረዳ እንደቆየ በመጽሐፍት ተጽፏል።
=> ቅዱስ ሚካኤል እኛንም ከዲያብሎስ ወጥመድና ተንኮል ይጠብቀናል፤ በጸሎቱም በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ የታመነ ነው።
=> በጸብና በጦርነት ምትክ ሰላምና መግባባትን ይሰጠን ዘንድ ቅዱስ ሚካኤል በጸሎቱ ያግዘ፣ ይርዳን።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች ዛሬ በቴሌግራም በቀጥታ ስርጭት ላይ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ነሀሴ 11 ከምሽቱ 1:30 ሰዓት የቀጥታ ስርጭት ይካሄዳል።
በመሆኑም በቀጥታ ስርጭቱ ላይ በመግባት ይከታተሉ።
https://t.me/kesishenokLive
በማማተብ አጋንንት በጭራሽ አይርቅም 3ቱ እንድ ክርስቲያን ልኖሩት የሚገባው ነገር ሜድተሽንና የከራማ የዛር አጋንንት | መምህር ግርማ ወንድሙ 🚩😭😱🔥
https://youtu.be/W3Z-MrZKY6E?si=8_GnRa8MECjF5cio
ትዳራችንና ፈተናዎቻችን አሸንድዬና መንፈሳዊ አንድምታው እኔ ለሲኦል ነው የተፈጠርኩት || መምህር ግርማ ወንድሙ | ኢዮብ ይመኑ | ተስፋዬ አበራ 😱💥
https://youtu.be/zBcF2Khx_k8?si=L-e7VyJAHDdL12xF
=> የመንፈሳዊ ዝምድና ሞትን ተሻግሮ የሚሄድ ለዛ ነው ወዳጄ ዝምታው አቅቶን አይደለም ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው። ለዛ ነው ዝምታው አቅም አንሶን ጉልበት አጥተን አይደለም። እውነተኛ አገልጋይ የሚዋጋው ከፊት ያለውን ስለሚጠላ ሳይሆን ከኋላ ያሉትን ስለሚወድ ነው! (እናንተ ክፉ ነገርን አሰባችሁብኝ፤ እግዚአብሔር ግን ዛሬ እንደ ሆነው ብዙ ሕዝብ እንዲድን ለማድረግ ለመልካም አሰበው።) (ኦሪት ዘፍጥረት 50፤20) => https://www.youtube.com/watch?v=-6nuu674dqA #ሸር_ማድረጋችሁን_እንዳትረሱ! ለሁሉም ይዳረስ!
=> የማይቋረጠው መንፈሳዊ አገልግሎት በገጠሪቱ እና በከተማ በዓለማት ህዝበ ክርስቲያን ባለበት ሁሉ እንደእሳት እየተቀጣጠለ በቅርቡ ይጀመራል። ተዘጋጁ ውዶች! => https://www.youtube.com/watch?v=-6nuu674dqA
(እግዚአብሔር የታሰሩትን ይፈታል፤!)
መዝሙረ ዳዊት 146፤7
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#_በአሜሪካ_በሎስአንጀለስ_ከተማ!
ሼር በማድረግ መልእክቱን አጋሩ! ተዘጋጅታችኋል ቤተሰቦቼ። ብዙዎቻችሁ ስትጠይቁኝ ነበር ይሄው ቀሲስ ሄኖክ ወደ አሜሪካ ሎሳንጀለስ ይመጣሉ ለአገልግሎት ሁላችሁም የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ ሸር አድርጉ። 🙏🙏🙏
👉 @kesishenokweldemariam2240 🙏🙏🙏
👉 @haileG2239
👉 @estifo2239
ልጆችን በቅድስና እንዴት እናሳድግ? | የቤተሰብ ዛር እንዲሁ ዝም ብሎ አይለቅም | የአጋንንት ተንኮል ተረት ተረት የሚመስላቸው | መምህር ግርማ ወንድሙ 💥🚩😱
https://youtu.be/xFChIZmGZQQ?si=l3Zrkd8FZdU8st7t
=> እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ወርሃዊ የመታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ። "የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።" (ያዕ. ፭፥፲፮ /5፥16/) => https://www.youtube.com/watch?v=-6nuu674dqA
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
=> "ጾም የፀሎት ምክንያት ናት፤ የፀጋ ዕንብ መገኛ ናት፤ አርምሞን የምታስተምር ናት፤ ለበጎ ስራ ሁሉ ታነቃቃለች፤ የፀዋሚ ስጋው ምንጣፉን አንጥፎ ሌሊቱን ሁሉ ተኝቶ ማደር አይቻለውም በምን ጎኑ ይተኛዋል? ሰው አብዝቶ በጾመ ያህል በዚህ መጠን በትህትና ሁኖ እያለቀሰ ይፀልያል፤ ፀሎታት ከልቡናው ይታሰባሉ አንድም ፀሎተ ልብ ይሰጠዋል፤ በፊቱ የትእግስት ምልክት ይታያል በኃጢአቱ ያዝናል ክፉ ህሊና ይርቅለታል የበጎ ነገር መገኛ መከማቻ በምትሆን በጾም ይኖራልና፤ ጾምን የናቀ ያቃለለ ሰው በጎውን ነገር ሁሉ ከራሱ አራቀ።" (ማር ይስሐቅ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
አባቶቻችን ስለ ኃጢአተኛ እንዲህ አሉ:–
=> "በጽድቁ ከሚመካ ጻድቅ ሰው ይልቅ ስለ ኃጢአቱ የሚያለቅስ ዘማዊን እግዚአብሔር አብዝቶ ይወድደዋል።" (ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
=> "የትናንት ታሪክ የሌለው ጻድቅ የነገ ተስፋ የሌለው ኃጢአተኛ የለም።" (ቅዱስ አውግስጢኖስ)
=> "አቤቱ እንደ እኔ ያለ ኃጢአተኛ እንደ አንተ ያለ መሐሪ የለምና ይቅር በለኝ።" (ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
=> "ቤተ ክርስቲያን ሐኪም ቤት ናት እንጂ በነፍሳት ላይ የምትፈርድ ፍርድ ቤት አይደለችም። ስለ ኃጢአትም ስርየትን ትሠጣለች እንጂ ፍርድ አትሠጥም።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
=> "ኃጢአትን ለማዋጋት ስትሞክሩ ኃጢአተኛውን እንዳትወጉ ተጠንቀቁ።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ወንድ ልጅ እንደ ሴት የወር አበባ || ተኮላሽ ኢያሱ የዛር አጋንንት || ሴሰኛ የሚያደርጉ መናፍስቶች || ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ | መምህር ተስፋዬ አበራ 🔥😱💥🚩 https://youtu.be/vHW8u1RUf-Y
