HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 273
Suscriptores
+424 horas
+127 días
+2530 días
Archivo de publicaciones
«ምጽዋት በአባቶች አንደበት»
"አንተ ልትበላው ያልፈለግኸው እንጀራ የተራቡት ሰዎች እንጀራ ነው። በቁም ሳጥንህ ውስጥ ሰቅለህ የተውከው ልብስ ዕርቃኑን የሆነው ሰው ልብስ ነው። የማታደርጋቸው ጫማዎችህ ባዶ እግሩን የሚሔድ ሰው ጫማዎች ናቸው። የቆለፍክበት ገንዘብ የደሃው ገንዘብ ነው። የማትፈጽማቸው የቸርነት ሥራዎች ሁሉ ኢፍትሐዊ ድርጊቶችህ ናቸው።" #ቅዱስ_ባስልዮስ
"አንድ ነዳይ አጥብቆ እየለመነህ በቸልታ ትተኸው ስትሔድ እግዚአብሔርን አጥብቀህ በምትለምን ጊዜ ቢተውህ የሚሰማህን አስብ።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
"ክርስቶስን በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ወድቆ በሚለምነው ነዳይ ውስጥ ካላገኘኸው ውስጥ ገብተህ በመንበሩ ላይ ባለው ጽዋ ላይ አታገኘውም።" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
"ወንድምህ ዕርቃኑን ወድቆ እያለቀሰ ነው ፣ አንተ ግን የሚያምር የወለል ንጣፍ ለመምረጥ ተቸግረህ ቆመሃል።" #ቅዱስ_አምብሮስ
"አባት ሆይ ወጪውን ሳናሰላ እንድንመጸውት አስተምረን።" #ቅዱስ_አግናጥዮስ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
እየተሰገደ የሚጸለይ ጸሎትና ማወቅ የሚገባችሁ ወሳኝ መረጃ!! ባለሥልጣናት የደበቁት የእናቶች ረሀብና ሰቆቃ ሲገለጥ!! መስገድ ካልጀመርክ ይኼ ይሆንብናል ንቁ! https://youtu.be/n6mqVJ5mPGw
ሁላችሁም ኦርቶዶክሳዊያን ይኼንን መልዕክት አዳምጣችሁ አሁኑኑ እራሳችሁን ፈትሹ!!
https://youtu.be/hsfUAs8awQQ?si=NMAVbGTxkcdoRVtk
ለ12 ዓመቱ ሕፃን የሕይወት አድን ጥሪ!
"ለወገን ደራሽ ወገን ነው!"
በአዋሽ ባንክ የኢምፔሪያል አካባቢ ቅርንጫፍ ሠራተኛ የሆኑት ወ/ሮ ጽጌ ገረመው የ12 ዓመት ልጃቸው በከባድ የአንጎል ዕጢ (Brain Tumor) በሽታ በመታመሙ ምክንያት አስቸኳይ ቀዶ ጥገና ያስፈልገዋል።
ለዚህም ሕክምና በጠቅላላ 6,000,000 (ስድስት ሚሊዮን) ብር በከፍተኛ ሁኔታ ያስፈልጋቸዋል። ይህ መጠን ከቤተሰቡ አቅም በላይ በመሆኑ ሁላችንም በቻልነው አቅም በመርዳት የሕፃኑን ሕይወት እንታደጋለን።
መርዳት ለምትፈልጉ፦
የባንክ አካውንት፦ 01347141556500 (አዋሽ ባንክ)
የአካውንቱ ስም፦ ጽጌ ገረመው (Tsigye Geremew)
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ፦ +251 912 030431
"ትንሽ የምንላት ለእኛ ናት እንጂ ለተቸገረ ወገናችን ትልቅ ናት።"
እባክዎ ይህን መረጃ ለሌሎች በማጋራት (Share በማድረግ) የበኩሎን ድርሻ ይወጡ። እግዚአብሔር ለሕፃኑ ምሕረቱን ይላክለት!
ዘመድኩን ያቀረባቸውን ጥያቄዎች እንዴት አያችሁ?? መንፈሳዊ ስንሆን መከራና ፈተና ከበዛባችሁ ይኼንን አስተካክሉ!! የአዕላፋት ዝማሬና ውዝግቡ ለምን ተፈጠረ? https://youtu.be/cdTpIpEdwuI
ታሕሳስ ፲፫ /13/
በዚችም ቀን ከላይኛው ግብጽ ቅዱስ አባት አብራኮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ዕድሜው ሃያ ዓመት ሲሆን መንኵሶ መልካም የሆነ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ።
ሰይጣንም ከእርሱ ጋር በመጣላት በተሸነፈና በደከመ ጊዜ በእርሱም ላይ ምንም ምን ማድረግ ባልተቻለው ጊዜ ፊት ለፊት ተገልጦ መጥቶ “እነሆ ከዚህ ዕድሜህ ሌላ ኀምሳ ዓመት ቀረህ አለው።” በዚህም ወደ ስንፍና ሊጥለው ወዶ ነው።
ሽማግሌውም እንዲህ ብሎ መለሰለት “አሳዘንከኝ እኔ ሌላ መቶ ዓመት እኖር ዘንድ ስለ አሰብኩ ቸል ብያለሁ አንተ እንዳልከውም ከሆነ ከቀድሞው እጅግ አብዝቼ እጋደል ዘንድ ይገባኛል።” ከዚህም በኋላ ተጋድሎውንና በገድል መጸመዱን አበዛ ሰባ ዓመታትም ከተጋደለ በኋላ በዚያች ዓመት አረፈ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
ገንዘባችን ሥራችን እንድባረክ የሚጸለይ የመዝሙረ ዳዊት ጸሎቶች! መዝሙረ ዳዊት ጸሎትና ማወቅ የሚገቡን ነገሮች! የስልብና መንፈሶችን ለማሸነፍ የሚጸለይ ጸሎቶች!!
https://youtu.be/gx8mo_rozl4?si=-3t9zOWYRsxbSyvD
የቡዳን መንፈስ ለማሸነፍና ለማራቅ አሁኑኑ ይኼንን ማድረጋችሁን አንዳትረሱ! ክፋታችንና ተንኮላችን ከአጋንንት በልጧልና እንንቃ! ጸሎትን ስናቆም እንዲህ ሆንን! https://youtu.be/GPPT08PeMkI
«ጸሎትህ ወዲያውኑ መልስ ባያገኝ ተስፋ አትቁረጥ፤ አንተ ከምታውቀው በላይ እግዚአብሔር ላንተ የሚያስብበት የተሻለ ጊዜ አለው።»
(አባ እንጦንስ)
ዘመድኩን የመምህር ግርማን ትምህርት ተደብቆ ተምሮ በለጠን እኮ ወጌን!! በሽታ በሕክሚና እንጂ በጸሎት አይድንም የምሉ አንደበቶች! #አጋንንት #ሰይጣን #ጸሎት https://youtu.be/KUHfJLMTp58
ዘመድኩን የመምህር ግርማን ትምህርት ተደብቆ ተምሮ በለጠን እኮ ወጌን!! በሽታ በሕክሚና እንጂ በጸሎት አይድንም የምሉ አንደበቶች! #አጋንንት #ሰይጣን #ጸሎት https://youtu.be/KUHfJLMTp58
ልፋት ብቻ ሆነብኝ ለምን አልሳካ አለኝ? እግዚአብሔር ፀሎቴን ለምን አይሰማም? ለከባድ የህይወት ፈተና የተሰጠ መልስ
https://youtu.be/OI1mHX8DeyM
ይኼንን የመዝሙረ ዳዊት ክፍል ጸልያችሁ የማይስተካከል ነገር የለም! የጥበቃና የፍርሃት መደምሰሻ መዝሙር!
https://youtu.be/FPASf8YodME?si=XB5ylOtRGVXRhVNb
ጌታችን ሆይ፥ እናትህን እንዴት መጥራት እንደሚገባን የሚያውቅ ማንም የለም።
“ድንግል” ቢሏት፥ ልጇ ቆሞ ይታያል፤
“ያገባች” እንዳይሏትም፥ ማንም በሩካቤ አላወቃትም።
ነገር ግን እናትህ እንዲህ ለመረዳት የምታስቸግር ከሆነች፥
አንተን መርምሮ ማወቅ የሚችል ማን ነው?
ምስጋና ላንተ ይሁን፤ የሁሉ ጌታ እንደመሆንህ ላንተ ሁሉ ነገር ቀላል ነውና።
እርሷ ብቻዋን እናትህ ናትና፤ ከሁሉም ጋር ደግሞ እህትህ ናት።
ላንተ እናት ነበረች፤ ላንተ እህት ነበረች።
ከዚህም በላይ፥ ከንጽሕት ሴቶች ጋር እጮኛህ ናት።
የእናትህ ውበት ሆይ፥ እነሆ በሁሉ ነገር አስጌጥካት።
አንተ ከመምጣትህ በፊት እንደ ተፈጥሮ ሥርዓት ታጭታ ነበርና፤
ቅዱስ ሆይ፥ አንተ ከመጣህ በኋላ ግን ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጭ ፀነሰች፤
በንጽሕና ብትወልድህም ድንግል ነበረች።
ማርያም ያገባች ሴትን ባሕርይ ሁሉ ባንተ አገኘች፤
ያለ ሩካቤ መፅነስን፥ ባልተለመደ መንገድ በጡቶቿ ወተትን አገኘች።
አንተ ደረቁን ምድር በድንገት የወተት ምንጭ አደረግህ።
ብትሸከምህ፥ ታላቁ ተራራህ ሸክሙን አቀለለ።
ብትመግብህ፥ ስለተራብህ ነው።
ልታጠጣህ ብትል፥ መጠማትን ስለወደድህ ነው።
ብታቅፍህ፥ የምሕረት ፍም እቅፏን ጠበቀላት (አልለበለባትም)።
እናትህ ድንቅ ናት፤ ጌታ ወደ እርስዋ ገብቶ ባሪያ ሆነ፤
መናገር እየቻለ ገብቶ በእርስዋ ዝም አለ፤
እንደ ነጎድጓድ እያንጐራጐረ ገብቶ ድምፁ ፀጥ አለ፤
የሁሉም እረኛ ሆኖ ገብቶ፥ በእርስዋ ውስጥ በግ ሆነ፤ እየጮኸም ወጣ።
የእናትህ ማኅፀን ሥርዓትን ገለበጠ፦
የሁሉ መሠረት (ባለጸጋው) ወደ እርሷ ገባ፥ ድሃ ሆኖ ወጣ።
ልዑል ሆኖ ገባ፥ ትሑት ሆኖ ወጣ።
ብሩህ ሆኖ ገባ፥ የተናቀን መልክ ለብሶ ወጣ።
ኃያል ተዋጊ ሆኖ ገባ፥ በማኅፀኗ ውስጥ ፍርሃትን ለበሰ።
የሁሉ መጋቢ ሆኖ ገባ፥ ረሃብን ገንዘብ አደረገ።
ለሁሉ የሚያጠጣ ሆኖ ገባ፥ ጥማትን ገንዘብ አደረገ።
ሁሉን የሚያለብስ እርሱ፥ ተገፎና ዕራቁቱን ሆኖ [ከማኅፀን] ወጣ።
(ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም እንዳመሰገናት)
ጠባቂ መላእክቶቻችን ከእኛ እንዳይርቁ ይኼንን ማድረጋችሁን እንዳትረሱ!! እርግማን በክርስትናና በእስልምና መነጽር ስታይ!! #ቅዱስ_ቁርባን! #ጸሎት #አጋንንት https://youtu.be/Iox7-1xljdU
በመምህር ተስፋዬና በሊቁ ስሙር አላምረው መካከል የተፈጠረው ምንድነው?? አራት አይና ሆኜ አጋንንትን ማውጣት ለምን አቃተኝ? #አጋንንት #መናፍስት #ክርስቶስ https://youtu.be/DtCeoz1E03k
«ያልተሰጠህን አትሻ»
+ የተሰጠህን ጸጋ እንዳታጣ ያልተሰጠህን አትሻ፡፡ ወደ ጸጋ ወደ ክብር ለመድረስ እግዚአብሔር ቢያበቃህ ያሳየህን እይ ያላሰየህን አያለሁ አትበል። አንድም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፣ በተሰጠህ ጸጋ ለእግዚአብሔር ተገዛ፡፡ ማር አብዝቶ መመገብ እንዳይመች እንደዚህም ሁሉ ያልተሰጠውን መሻት አይገባም አያስመስግንም፡፡ ነፍስ ያልተሰጣትን ጸጋ በመሻት እንዳትደክም ያልተሰጠህን ጸጋ አትሻ፡፡ የምታየው ማየት ቢኖር እውነተኛውን ምትሐት ሆኖ ታየዋለህ ፤ ሕሊና ያልሰጡትን ጸጋ በመሻት በማውጣት፣ በማውረድ የተሰጠውን ያጣል፡፡
+ ሰሎሞን መልካም ነገር ተናገረ "በሰጡት ጸጋ የማይኖር ሰው ቅጽር የሌላትን አገር ይመስላል" ብሎ ያን ማንም እየገባ እንዲዘረፈው እሱም የተሰጠውን ጸጋ ያጣል ፤ አንተ ብሩህ አእምሮ ሰውነትህን ያልተሰጣትን ጸጋ እንዳትሻ ከልክላት፡፡ ከቁመተ ሥጋ የወጣ አብዝቶ መገበርን ከአንተ አርቅ ያልተሰጠህን መሻት ከአንተ አርቅ፡፡ ባልተሰጠህና በተሰጠህ ጸጋ መካከል ትሕትናህን፣ ንጽሕናህን መጋረጃ አርጋቸው:: አንድም በተሰጠህ ጸጋ ላይ ያልተሰጠህን ጋርደው፡፡ በንጽሕና፣ በትሕትና፣ በልቡናህ የምታስበውን መንፈሳዊ ክብር ታገኛለህ::
ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
በመምህር ተስፋዬና በሊቁ ስሙር አላምረው መካከል የተፈጠረው ምንድነው? አራት አይና ሆኜ አጋንንትን ማውጣት ለምን አቃተኝ? አጋንንትን ማስለፍለፍ በጣም ተራ ነገር እኮ ነው!!
https://youtu.be/DtCeoz1E03k?si=q8d7Onr1FARK6vDX
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
