es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 280
Suscriptores
Sin datos24 horas
+117 días
+3830 días
Archivo de publicaciones
"የማይቀርበት ጉባኤ! ስትጠይቁኝ ልነበራችሁ!" ቀጣይ የፊታችን ቅዳሜ እና እሑድ ኅዳር 28 እና 29/2017 ዓ. ም አገልግሎታችን ከአባቴ መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ ጋር በአያት ቅዱስ
"የማይቀርበት ጉባኤ! ስትጠይቁኝ ልነበራችሁ!" ቀጣይ የፊታችን ቅዳሜ እና እሑድ ኅዳር 28 እና 29/2017 ዓ. ም አገልግሎታችን ከአባቴ መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ ጋር በአያት ቅዱስ ፋኑኤል ቤተ ክርስቲያን የምናገለግል መሆኑን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን! => የቤተክርስቲያኑ አድራሻ፦ ከመገናኛ ወደ መሪ ሲኤሚሲ አያት በሚለው ይሳፈሩ አያት አደባባይ ሲደርሱ ተራራ ው ላይ ቤተ ክርስቲያንዋ ትታያለች ወይም ቅዱስ ፋኑኤል ቤተ ክርስቲያን አቅጣጫው ብለው ይጠይቁ። ሁለተኛ አማራጭ በመሪ በኩል መሄድ ይችላሉ መኪና ቤተክርስቲያኑ አጥር ጊቢ ውስጥ እንደሚያስገባ ወይም በአያት ዞን ስምንት በኩል ማቆም እንደምትችሉ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን! የማይቀርበትን ቀን አንቀርም! የመጽሐፍ ቅዱስ በተለይ የሐዲስ ኪዳን መጻፍ ሆነ የቤተ ክርስቲያን ከመነሻው የሆነ የሁሉ ሥርዓቶቿ ዋና ግብ፥ ሰውን ከሙላቱ ፍፁም ህትመት ማድረስ፤ አስቀድሞ ወደ ታሰበለት ሕያው ሐሳብ ፍጻሜ ማምጣት፤ ወደ ተሰጠም የመለኮት ልጅነት ማግባት ነው፡፡ እንጂ ከዘመናት ወዲህ ለተዘፈቅንባቸው ተቋማዊ ሙግቶችና ሥነ ቃላዊ ክርክሮች ማብቃት በጭራሽ አይደለም፡፡ ወደ ቀደመው ነገር እንሒድ፡፡ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

"ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ
"ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

+ ተክለሃይማኖት ሆይ + ከፀሐይ እና ከጨረቃ ሥነ ፀዳል ይልቅ + በክርስቶስ ሥነ ጸዳል ለተዋበው ፊትህ ሠላም እላለሁ + ቅዱስ አባት ሆይ + ትምህርትህ የተስፋፋ + ትሩፋትህ የተትረፈረፈ + ዮሐንስ
+ ተክለሃይማኖት ሆይ + ከፀሐይ እና ከጨረቃ ሥነ ፀዳል ይልቅ + በክርስቶስ ሥነ ጸዳል ለተዋበው ፊትህ ሠላም እላለሁ + ቅዱስ አባት ሆይ + ትምህርትህ የተስፋፋ + ትሩፋትህ የተትረፈረፈ + ዮሐንስ የተባልክ አንተ ተክለሃይማኖት ነህ + ስለዚህ የዓለም ሥራው ብዙ ስለሆነ + ንጹሑ የትዕዛዛዝ ቃል ከድካም ያሳርፈኝ + ከማዕሠረ ኃጢአት ይፍታኝ። /መልክአ ተክለሐይማኖት/ 🙏🏾 የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤት በረከታቸው አይለየን 🙏🏾 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ከሙዝቃ በላይ የሚፈውስ የሚያድን ነገር የለም! | የቲክቶክ ተከታይ ለማግኘት ማስጠንቆል! | ተሳስቶ እንዳያሳስት የተሰጠ መልስ! #ethiopia #ebstv 😱 https://youtu.be/1Iw25OuVfVo

🍂 #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ ከላይ ባለ በሰማይ ከታች ባለ በምድር በብዙ ወገን ለእርዳታ ፈጥነህ አደራረስህ የኤፍራታ ርግብ እነደ ተባለችው እመቤትህ ማርያም ነው። በመሆኑም በእናትህ ቴዎብስታ ስም እን
🍂 #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ ከላይ ባለ በሰማይ ከታች ባለ በምድር በብዙ ወገን ለእርዳታ ፈጥነህ አደራረስህ የኤፍራታ ርግብ እነደ ተባለችው እመቤትህ ማርያም ነው። በመሆኑም በእናትህ ቴዎብስታ ስም እንደ ስምህ መንታነት የባለሟልነት ስምህን ትሰጠኝ ዘንድ እማልድሀለው። (መልክዐ ቅዱስ ጊዮርጊስ) የሰማዕቱ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት አየለየን🙏 ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይሰውረን 🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ያላገባችሁ ማዳመጥ ያለባችሁ!! ለብሰው ያበዱ ያሳብዳሉ! የጉድ ሀገር! ለሴቶች እህቶች የተላለፈ መልዕክት በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia #ebstv 😭😱🔥 https://youtu.be/ltT7aoO4nEs

የእውነተኛ አምልኮት ኃይልና በረከቶቹ!! የእርግማን ትውልድ ምልክቶችና ፈተናዎች! ከሰማያዊ አምልኮት መራቅና ጥፋቱ! የመምህር ተስፋዬ ከባባድ ገጠመኞች!! 😱😭 https://youtu.be/uiiZ9IKQG08

«ነጻነታችንን አናስወስደው!» => እግዚአብሔር በፍጥረት ጊዜ ለሁላችንም ከሰጠን መሠረታዊ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነጻ ነት ነው። በዚህ ስጦታ አማካኝነት ሰጪውን እግዚአብሔርን ምን ያህል ቸር እንደ ኾነ እናጣጥምበታለን። በተለይ በሐዲስ ኪዳን ያገኘነውን ነጻነት በተመለከተ ዮስጢኖስ እንዲህ ይላል “በእውነታው አንድ ነጻነት ብቻ ነው ያለው። ይኸውም ከኃጢአት፣ ከክፋትና ከዲያብሎስ ነጻ ያደረገን የክርስቶስ ቅዱስ ነጻነት ነው። በዚህ ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን። ሌሎች ነጻነቶች በሙሉ እውነት የሚመስሉ፣ የተሳሳቱ፣ በእርግጥም በአጠቃላይ ባርነቶች ናቸው" አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ተለይቶ የወደደውን ለማድረግ በመፈለጉና አንዳንዴም ተሳክቶለት በማድረጉ ምክንያት የተሰጠውን ስጦታ ተጠቅሟል ማለት አይደለም። ነጻነታችንን መልካም የኾነውን ለመምረጥ ብቻ የማንጠቀም ከኾነ እንጎዳበታለን። እግዚአብሔር ነጻነትን የሰጠን ከልባችን እርሱን ፈልገን እንድናመልከው ስለሚፈልግ ነው። ክርስቲያን ማለት ክርስቶስን የሚመርጥና ፈቃዱን በማድረግ ደስ የሚሰኝ ማለት ነው። ከእውነተኛው ነጻነት እውነተኛ ደስታ ይመነጫል፤ ይህ ደስታ ደግሞ የእኛ ብቻ ሳይኾን የሰማይ መላእክትም ደስታ ነው። => ፍጹም የኾነውን ነጻነት የምናገኘው በፍቅረ እግዚአብሔርና በፍቅረ ቢጽ ውስጥ ነው። ፍቅር የሌለው ሰው ነጻነት የለውም። እግዚአብሔርንና ሰውን የምንወድ ከኾነ ፍጹሙን ነጻነት ገንዘብ አድርገናል ማለት ነው። በዚህ ውስጥ ደግሞ ፍጹም የኾነ እኩልነት አለ። ስሎዋን እንዲህ ይላል “ሁሉም ሰው ንጉሥ፣ አባት፣ አለቃ መኾን አይችልም። ነገር ግን በማንኛውም የሥልጣን ደረጃ ውስጥ ኾኖ እግዚአብሔርን መውደድና ማስደሰት ይችላል፤ ይህ ብቻ ጠቃሚ ነውና። ማንም እግዚአብሔርን በምድር ላይ አብልጦ ቢወድ፣ በእግዚአብሔር መንግሥት በታላቅ ክብር ይኾናል።" እንግዲህ በእውነተኛው ነጻነት ውስጥ መኖር ማለት እግዚአብሔርን በማፍቀርና በማስደሰት መኖር ማለት ነው። በነጻነት ውስጥ አለን ማለት በዚህ መልካም ነገር ውስጥ አለን ማለት ነው። => ተወዳጆች ሆይ! ይህን ቅዱሱን ነጻነት ክፉ ምኞታችን አላጠፋብንምን? የዚህ ዓለም ኃላፊ ነገሮች እጅግ በጣም ደስ የሚያሰኙን ራሳችንን ለኃጢአት ባርያ በማድረጋችን ምክንያት ከቅዱሱ ነጻነች ስለ ራቅን መኾኑን መዘንጋት የለብንም። ሐሳባችን ከመልካምነት ሲወጣ አእምሯችን ለአጋንንት ባርያ ወደ መኾን መውረዱን እናስተውል! ቶሎ ብለንም ውስጣችንን እንመርምር፥ ስለ ፍቅር ብሎ ፈጥሮን በፍቅሩ የሚያኖረንን አምላክ የሰጠንን ነጻነት ፍሬ በማፍራት እናስደስተው! ለዚህ ዓለም ማንኛውም ኃላፊ ነገር ውስጣችንን ባርያ በማድረግ ነጻነታችንን አናበላሽ። እስከ ዛሬ ድረስ የፈጸምናቸው ክፉ ሥራዎች እጅግ መብዛታቸውን አስበን ፈጣሪያችንን በአንብዓ ንስሓ ማረን እንበለው። => ቅዱስ ማርቆስ “መንፈሳዊ ሕይወትን የሚኖር ትሑት ሰው፥ ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚያነብበት ጊዜ፥ ሁሉንም ነገር ከራሱ ሕይወት ጋር ያገናኛል እንጂ ከሌሎች አይደለም።" ይላል። (St. Mark the Ascetic, Sermon, 1.6)። ስለዚህ ነጻነትን ጠብቆና ቀድሶ ለመኖርን የራስን ሕይወት መመርመር ያስፈልጋል። የራሳችንን ሕይወት ሳንቀድስ ስለ ሌላው ብቻ በማወራት የምንኖር ከኾነ በአጋንንት ወጥመድ ውስጥ መጠመዳችንን ልብ እንበል! ለዚህም ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “ብርሃን የሌላቸው ቀጥ ብለው መሄድ እንደማይችሉ የቅዱሳት መጻሕፍትን ጨረር ያላዩ በጨለማ ስለሚጓዙ ኃጢአትን ይሠራሉ።" በመኾኑም ነጻነታችንን በቅዱሳት መጻሕፍት መመሪያ ውስጥ እናድርገው። በራሳችን ምድራዊ ፍላጎት ምክንያት እግዚአብሔር የሰጠንን ልዩ ስጦታ በሰይጣን አናስወስደው! እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀን፥ በብዙ የኃጢአት ዱላ ተደብድቦ የደነዘዘውን ልቡናችንን ይፈውስል፤ የሐሳቡንም ብርሃን በልባችን ያብራልን፤ በፈቃዳችን ከታሠርንበትን የኃጢአት ባሪነት በቸርነቱ ያላቅቀን፤ ቅዱስ ቃሉንም ወደ መረዳትና በገቢራዊ ሕይወት ወደ መኖር ልዕልና ያሣርገን አሜን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

+ ህዳር #ጽዮን 🍂 21 ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤ በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ አዳራሽዋን አስቡ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ። (መዝ 48 ፥ 12) + እንድ
+ ህዳር #ጽዮን 🍂 21 ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤ በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ አዳራሽዋን አስቡ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ። (መዝ 48 ፥ 12) + እንድንከባት፣ እንድናቅፋት፣ በዙሪያዋ ተሰብስበን እንድንመካባት፣ በብርታቶቿ ተማምነን ልባችንን እንድናሳርፍባት፣ ጽዮን አንባችንን፣ ጽዮን መታመኛችንን፣ ጽዮን መመኪያችንን የሰጠን አምላክ ይክበር ይመስገን!!! 🙏......ለአመቱ በሰላም በጤና ያድርሰን....🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የአዕምሮ ዘገምተኛ ነሽ ተብላ የሆነውን ተመልከቱ!! | የዘመናችን ሌብነትና ድብቁ የመናፍስቱ ሴራ! | በጸሎት ባሏን ፓራላይዝ ያደረገች ጎበዝ! #ebstv 😱😱 https://youtu.be/Q6H4i_F54wk

"እውነተኛ ጿሚ ራሱን ከክፉ ምግባራት የከለከለ፤ ከንቱ የሆኑ ንግግሮችን ከመናገር የተቆጠበ፣ ሐሰትን የማይናገር፣ ሐሜተኛ ያልሆነ፣ በማንም ላይ የማይፈርድ፣ ሽንገላን የማይወድና እኒህንም ከመሰሉ ነገሮች ራሱን የተጠበቀ፣ የማይቆጣ፣ የማይበሳጭ፣ ተንኮለኛ ያልሆነ፣ ቂመኛ ያልሆነና፣ እነዚህን ከመሳሰሉ ክፋቶች ሁሉ የራቀ ሰው ነው፡፡ ሕሊናህ ኃጢአትን ከማሰብ ይጡም፣ አእምሮህም ኃጢአትን ከማስታወስ ይከልከል፡፡ ክፉን ከመመኘት ሁሉ ጡም፡፡ ዐይኖችህ ከንቱ የሆኑ ነገሮችን ከመመልከት፣ ጆሮህም ከንቱ ከሆኑ ዘፈኖችና ከሐሜተኞች ሹክሹክታዎች ጠብቅ፡፡ አንደበትህ ከሐሜት፣ በሌላው ላይ ከመፍረድ፣ ከስድብ፣ ከውሸት፣ ከማታለል፣ ከሽንገላ ንግግሮች እንዲሁም ከማይጠቅሙና አጸያፊ ከሆኑ ቃላት ይጡሙ፡፡ እጆችህም ሰውን ከመግደልና የሌላውን ንብረት ከመዝረፍ ይጡሙ፡፡ እግሮችህም ኃጢአትን ለመፈጸም ከመሄድ ይጡሙ፡፡ ከክፉ ተመለስ መልካምንም ፈጽም፡፡" (ቅዱስ ኤፍሬም) መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

"በጎነት በጸሎት ይመሰረታል። ጸሎት ቁጣን ይጠብቃል። ጸሎት ቁጣን ያስወግዳል። ጸሎት የትዕቢትን እና የምቀኝነትን ስሜት ይከላከላል። ጸሎት መንፈስ ቅዱስን ወደ ነፍስ ይስባል፤ እናም ሰውን ወደ መንግሥተ ሰማያት ያነሳል።" (ቅዱስ ኤፍሬም ዞሶሪያ) "ዛፍ በፍሬው ይታወቃል ሰውም በሥራው። መልካም ሥራ ፈጽሞ አይጠፋም በጎነትን የሚዘራ ወዳጅነትን ያጭዳል ቸርነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል።" (ቅዱስ ባስልዮስ) "ከእግዚአብሔር ጋር መዋደድ ከሁሉ የላቀ ፍቅር ነው። እርሱን መፈለግ ታልቅ ጀብድ ነው። እሱን ማግኘት ትልቁ የሰው ልጅ ስኬት ነው።" (ቅዱስ አውግስጢኖስ) "ክፉ ክፉን ከቶ አያወጥም ማንም ክፉ ቢያደርግብህ መልካም ብታደርግለት መልካም ሥራህ ክፉዎቹን ያጠፋል።" (ቅዱስ ጲሜን) "እኛ አማልክት እንሆን ዘንድ ቃል ሰው ሆነ። የማይታየውን የአብን ሃሳብ እንድንቀበል በአካል ራሱን ገለጠ የማይሞተውን እንወርስ ዘንድ የሰውን ትዕቢት ታገሰ።" (ቅዱስ አትናቴዎስ) "ትልቁ የበጎ አድራጎት ተግባር ሌሎችን ከልብ ይቅር ማለት ነው።" (ቅዱስ ዞሲማስ) "ይህ ሕይወት ለንስሐ ተሰጥቷችኋል እባካችሁ በከንቱ ማሳደድ አታባክኑት።" (ቅዱስ ይስሐቅ ሶሪያዊ) "በሕይወት ጉዳዮች ላይ ብዙ አታንጸባርቁ። ስለ ምንም ነገር አትጨነቁ። ሸክማሁን ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ ጣሉ እርሱም ይደግፋችኋል።" (ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ) "የውስጥ እንቅስቃሴህን ከእግዚአብሔር ጋር ለማድረግ በሙሉ ሃይልህ ታገል ይሄኔ ውጫዊ ፍላጎቶችህን ታሸንፋለህ።" (ቅዱስ አርሳኒዮስ) "በሰው ፊት ሙሉ በሙሉ የተናቅን ብንሆን፤ በእግዚአብሔር ፊት በመከበራችን ደስ ይበለን። (ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር) መልካም ቀን ለሁላችን ይሁን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ከዩኒቨርስቲ ያስጫርኩት እኔ ነኝ!! | መምህር ተስፋዬን በጭራሽ አታዳምጡት ይላሉ!! | መንፈሳዊ መጽሐፍትን እንዴት እናንብብ? #ethiopia #ebstv 😱😭 https://youtu.be/1uA9mI6Lc1Q

ወላጆች እባካችሁ ልጆቻችሁን ጠብቁ!! || በደብተሯ የተደገመ ከባዱ የመተት መንፈስ | ዕውቀቷንና ዕድሏን በመተት ነጠቋት! ቅባዕ ቅዱስና አወዛጋቢው አረዳድ! https://youtu.be/pZ2sqYs3DB8

የሚያነቁና የሚያበረቱ ድንቅ ትምህርቶች! የስማችን ኃይልና የዲያብሎስ ውጊያ ይህቺ ናት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ! || የዝሙት ቪዲዮ መመልከት ጉዳቶቹ! 😭😱 https://youtu.be/MZ2BVJ175dc?si=AaYLpbrK3TxsEGYW

"የአሳማ ፍልስፍና (Pig Philosophy)" => አስተውል! በውጭው ካሉት ይልቅ በአንተ ውስጥ የሚገኙት ፍትወታት ጠንካራ ጠላቶችህ ናቸው። ልክ ያልተሠራለት ምኞት ከባቢሎን እሳት ይልቅ ያቃጥላል።
"የአሳማ ፍልስፍና (Pig Philosophy)" => አስተውል! በውጭው ካሉት ይልቅ በአንተ ውስጥ የሚገኙት ፍትወታት ጠንካራ ጠላቶችህ ናቸው። ልክ ያልተሠራለት ምኞት ከባቢሎን እሳት ይልቅ ያቃጥላል። አልጠግብ ባይነትም ከጥፉት ውኃ ይልቅ ያሰጥማል። ያልተገራ ፍላጎት ማንነትን አስጥሎ የሰይጣን ባሪያ ያደርጋል። ራስን መግዛት የሰው ልጆች ጌጥ ነው። ዮሴፍ ግብጽን ከፈርዖን ሁለተኛ ሆኖ ከገዛበት ታላቅ ሥልጣን ይልቅ፣ በጌታው ሚስት ፊት ያሳየው ራስን መግዛት ይበልጥ ይደነቃል። ጠቢቡ "በመንፈሱ ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስዱ (ከሚገዙ) ይበልጣል" እንዳለ። (ምሳ 16፥32) => ራስህን ነጻ ማውጣት ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ ከውስጥህ ጀምር። ሁል ጊዜ ካልበላሁ የሚለው ሆድህ ስስት አስለምዶ በወንድምህ ላይ ጨካኝ እንዳያደርግህ ለሰውነትህ ጾም አስተምረው። "ነገ እሞታለሁና ልብላ ልጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍናህን (Pig philosophy) ተውና አንተ በፈቃድህ እየተራብህ (እየጾምህ) ያለ ፈቃዱ የተራበው ወንድምህን በምጽዋት አጥግበው። => ጌታ ወደ ገሊላ የተመለሰው ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ነበር። (ማቴ 2፥20) አንተ ውስጥ ያለውን ሄሮድስ የተባለ ክፉ ምኞት እንዲሞት ካላደረግኸው በቀር የተሰደደው ክርስቶስ ወደ አንተ ሊመለስ አይችልም። ይህ ክርስቶስን ከልብህ የሚያሳድድብህን ሄሮድስ እንዴት ልትገድለው ትችላለህ? እርሱንስ ወግተህ የምትጥልበት የብረት ካስማ ምን ይሆን? ለዚህስ ከጾም እና ከጸሎት የሚበረታ ምንም ዓይነት የጦር ዕቃ አታገኝም። በል እነዚህን ይዘህ ዝመትበት። መልካም የነቢያት ጾም ይሁንልን! ይሁንላችሁ ውድ ቤተሰቦቼ!! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

🔥እኛ በጭፈራ ስንጮህ መንፈሳዊና ሥጋው ጠላት ዲያብሎስ ቀደመን! ልጆቻችንን ለዳንኪራው ዓለም ገበርን! #ethiopia #ebstv #orthodox 💥😱😭 https://youtu.be/ba7bT_5eOqc

🔥 ያለ ክርስቶስ የሚኖሩ መሪዎችና እብደቱ!! #ethiopia #africa #orthodox #tewahdo https://youtu.be/AooEhrh5yKg

አጋንንት ከሰው በመውጣቱ ለምትናደዱ! || ሰው እንዴት ለአጋንንት ጥብቅና ይቆማል! || የሰይጣን የድብልቆሽ ጊዜና ሰዓት | ዲያብሎስ ባሕሪይን ሲዋረስ 😱💥🚩🔥 https://youtu.be/7rOIZ_ySi0E