HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 269
Suscriptores
+224 horas
+177 días
+2930 días
Archivo de publicaciones
በመምህር ተስፋዬና በማዕበል ፈጠነ መካከል የተፈጠረው ምንድነው? ባሏ ደብተራ መሆኑን ሳታውቅ ብዙ መከራ ያስተናገደች! በመስተፋቅር ማግባቷን አውቃ ዲያብሎስን እንዲህ አሸነፈችው!
https://youtu.be/J22HfFN8iAE?si=GlFLf4-D5yIobBQ9
በቅዱሳን ስዕላት ዙሪያ የማያዳግም መልስ በዲያቆን ዘማሪያም ለሁላችንም! ሥዕለ አድህኖ ምን ማለት ነው? ለቅዱሳን ስዕላት የሚደረግ አክብሮትና ስግደት? https://youtu.be/Qu09qVDFX9E?si=DHr-kbGVvDS-lL0A
መምህር ግርማ ሲያስተምሩ ስህተት ሌሎቹ ሲያስተምሩ ትክክል ለምን?? ሀበሻዎች ኮተታችን ብዙ ነው ደግሞም ማህተብ አስረናል!! #ጸሎት #ስግደት https://youtu.be/nHVZ_4gtSac?si=4fM3ZtuWJGiFZP78
የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ የማስጠንቀቂያ መልዕክት! በቀን በትንሹ 50 ሚሊዬን ኦርቶዶክሳዊያን በግዕዝ ውዳሴ ማሪያምን ይጸልያሉ! ጣኦትን ሰባብሮ እግዚአብሔርን ያገኘና ያተረፈ ጀግና!
https://youtu.be/62BwU858fkk?si=joIXCtKtJVdpYaUm
መምህር ተስፋዬ በድንገት SURPRISE ተደረገ ምን ይሆን ጉዳዩ!! የጸሎተ ማሪያም ወሳኝ ጥቅሞችና በረከቶች!! ህይወትን የሚቀይሩ ድንቅ ትምህርቶች! #ጸሎት https://youtu.be/lMxgjXV24Rw
ቢኒያም ሽታዬ መምህር ተስፋዬን ይኼን ያህል የጠመደው ለምን ይመስላችኋል!? በጸሎት ሰዓት ቅዱሳንን ለምን እንሳደባለን መፍትሔው ምንድነው? https://youtu.be/sgITbc4BRk0?si=2VClz8ozNQIm15ov
በጸሎታችሁ ወቅት ይኼንን መረዳትና ማወቅ ግዴታ አለባችሁ!! ይኼ የብዙዎች ጥያቄና ሁላችንም ልንረዳው የሚገባ ጉዳይ ነው!! 7ቱ በጸሎት የሚገኙ ሀብቶች!! https://youtu.be/FXsi6iI7o8o
«የዮሐንስ ወንጌል 17፡1-26 እናንብብ»
- ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤ ቃልህንም ጠብቀዋል። የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ፤ የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ። እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤ ስለ ዓለም አልለምንም ስለ ሰጠኸኝ እንጂ፤ የአንተ ናቸውና፤ የእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው የአንተውም የእኔ ነው፤ እኔም ስለ እነርሱ ከብሬአለሁ።
- ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው። ከእነርሱ ጋር በዓለም ሳለሁ የሰጠኸኝን በስምህ እኔ እጠብቃቸው ነበር፤ ጠበቅኋቸውም መጽሐፉም እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም። አሁንም ወደ አንተ እመጣለሁ፤ በእነርሱም ዘንድ ደስታዬ የተፈጸመ እንዲሆንላቸው ይህን በዓለም እናገራለሁ። እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው። ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም። እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም። በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው፤ እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ።
- ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ እኔ ባለሁበት የሰጠኸኝ እነርሱ ደግሞ ከእኔ ጋር ይሆኑ ዘንድ እወዳለሁ። ጻድቅ አባት ሆይ፥ ዓለም አላወቀህም፥ እኔ ግን አወቅሁህ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ አወቁ፤ እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህን አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
መሸሽና ማምለጥ መፍትሔ የሆነው በዚህ ምክንያት ነውና አዳምጡ!! ለምን የዝሙት መንፈስ ባሪያ ሆንን? ሦስቱ የኃጢአት መሰረቶች ሁላችንም መጠንቀቅ የሚገባን!! https://youtu.be/JckfjYEqf58
እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ! ምን ይባላል ይኼ በእውነት እግዚአብሔር ልጆቻችንን ይጠብቅልን።
ከ585,882 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መሀል ያለፉት 48,920፣ የወደቁት ደግሞ 536,962 ሆነዋል። በሌላ አገላለፅ 91.6% ተማሪዎች ወድቀው 8.4% ብቻ አልፈዋል ነው።
ግማሽ ሚሊዮን ተማሪ ወድቋል ብሎ ርፓርት በእውነት እግዚአብሔር ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን። 😱
በመምህር ግርማ ትምህርት የጠላትን ሴራ ተረድቼ ቤተሰቦቼን ማዳን ችያለሁ!! የማይጸልዩ ባልና ምስት የሚያሳዩት ልዩ ልዩ ባሕሪዎች! የቅዳሴ ብዙዎቻችን የማናውቀው ምስጥር!!
https://youtu.be/DGaiQJhQ9Lo?si=Ciwlt5yoehtQW6U3
ይድረስ! የእመቤታችንን ስዕለ አድህኖ ለቀደደችው እህታችንና ቤተሰቦቿ!! ማወቅ የሚገቡን የመናፍቅ መንፈስ ሴራና ጥፋት! የአዳልሞቴ የዛር መንፈስ ጣጣና ሴራ!! https://youtu.be/WEtzl-EJQ7M
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» መስከረም 3
(የማቴዎስ ወንጌል 18፡18-23)
"... እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ወደ እርሱ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው። ኢየሱስ እንዲህ አለው። እስከ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም። ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ባሮቹን ሊቈጣጠር የወደደን ንጉሥ ትመስላለች።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
🚩 ሳታገቢ ብትቆርቢ ዕድሜ ልክሽን ድንግል ሆነሽ ትቀሪያለሽ ስለዚህ አትቁረቢ!! ወደ እግዚአብሔር ቤት ሄደን ባዶ ሆነን ለምን እንመለሳለን?
https://youtu.be/ISjzVagoUAY?si=OQTqlofXqgPYuo-F
በ2018 ማቆም የሚገቡን ለዲያብሎስ በር የሚከፍቱ ክፉ ልማዶች!! እውቀታችንና ጸጋችን ተደብቆ እንዳይቀር ይኼንን አድርጉ!! ይኼ ሁሉ መከራ ለምን ደረሰብን?? https://youtu.be/0BhHHkVr7iE
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! መስከረም 2 2018»
(የማርቆስ ወንጌል 6፡14-30)
"... ስሙም ተገልጦአልና ንጉሡ ሄሮድስ በሰማ ጊዜ። መጥምቁ ዮሐንስ ከሙታን ተነሥቶአል ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል አለ። ሌሎችም። ኤልያስ ነው አሉ፤ ሌሎችም። ከነቢያት እንደ አንዱ ነቢይ ነው አሉ። ሄሮድስ ግን ሰምቶ። እኔ ራሱን ያስቈረጥሁት ዮሐንስ ይህ ነው እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል አለ። ሄሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን አግብቶ ነበርና በእርስዋ ምክንያት ራሱ ልኮ ዮሐንስን አስይዞ በወኅኒ አሳስሮት ነበር፤ ዮሐንስ ሄሮድስን። የወንድምህ ሚስት ለአንተ ልትሆን አልተፈቀደም ይለው ነበርና። ሄሮድያዳ ግን ተቃውማው ልትገድለው ትፈልግ ነበር አልቻለችም፤ ሄሮድስ ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር፤ በደስታም ይሰማው ነበር። ሄሮድስም በተወለደበት ቀን ለመኳንንቱና ለሻለቆቹ ለገሊላም ሹማምንት ግብር ባደረገ ጊዜ ምቹ ቀን ሆነላትና የሄሮድያዳ ልጅ ገብታ ስትዘፍን ሄሮድስንና ከእርሱ ጋር የተቀመጡትን ደስ አሰኘቻቸው። ንጉሡም ብላቴናይቱን። የምትወጂውን ሁሉ ለምኚኝ እሰጥሽማለሁ አላት፤ የመንግሥቴ እኩሌታ ስንኳ ቢሆን የምትለምኚውን ሁሉ እሰጥሻለሁ ብሎ ማለላት። ወጥታም ለእናትዋ። ምን ልለምነው? አለች። እርስዋም። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ አለች። ወዲያውም ፈጥና ወደ ንጉሡ ገብታ። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን ልትሰጠኝ እወዳለሁ ብላ ለመነችው። ንጉሡም እጅግ አዝኖ ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ስለ ተቀመጡት ሊነሣት አልወደደም። ወዲያውም ንጉሡ ባለ ወግ ልኮ ራሱን እንዲያመጣ አዘዘው። ሄዶም በወኅኒ ራሱን ቈረጠ፥ ራሱንም በወጭት አምጥቶ ለብላቴናይቱ ሰጣት፥ ብላቴናይቱም ለእናትዋ ሰጠች። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው መጡ በድኑንም ወስደው ቀበሩት። ሐዋርያትም ወደ ኢየሱስ ተሰብስበው ያደረጉትንና ያስተማሩትን ሁሉ ነገሩት..."
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.youtube.com/@estifo2239
መስከረም ፪ /2/በዚች ዕለት የካህኑ የዘካርያስ ልጅ የከበረ የመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዕረፍቱ ሆነ። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ፤ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ንጉሥ ሄሮድስን የወንድምሕን ሚስት ልታገባ አልተፈቀደልህም እያለ ይዘልፈው ነበር። ዳግመኛም ንጉሡን ሌላ ያደርገው ስለነበረው ክፉ ነገር ይገሥጸው ነበር። ደግሞም ቅዱስ ዮሐንስ በተግሣጽ ላይ ተግሣጽን በጨመረ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ዮሐንስን ተቀየመውና በግዞት ቤት አኖረው። በመጨረሻም በሄሮድያዳ ልጅ ጥያቄ መሰረት ንጉሡ የከበረች የቅዱስ ዮሐንስን አንገት በዚች ዕለት እንዲቆርጡት አዘዘ። አንገቱ ግን ክንፍ አውጥታ ትሰብክ ነበረ። ደቀ መዛሙርቱም በሰሙ ጊዜ መጥተው በድኑን ወስደው ቀበሩት። እርሱም ፦ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለ፦ ”የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ አለ።" ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
ዘመን ማን ነው? ዘመን ማለት እኛ ነን..ስንከፋ የሚከፋ ደግ ስንሆን ደግ የሚሆን የእኛው ነጸብራቅ ነው ዘመን። ለዚህ ነው አበው በአንጋረ ፈላስፋ "ዘመን ማለት አንተ ነህ፡፡ አንተ ሰላማዊ ስትሆን ሰላማዊ ትሆናለች፡፡ አንተ የከፋህ እንደሆነ ትከፋለች፡፡" በማለት የተናገሩት።
እናም ዘመን እኛ እኛም ዘመን ነንና ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳለው በዕሜያችን ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰብን ራሳችንን እንዲህ ብልን እንጠይቅ፡- “ቀናት እየሮጡ ነው፣ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፣ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፤ ታዲያ ምን በጎ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፤ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ (ዘመኔ) መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፤ ታዲያ ዕድሜዬ (ዘመኔ) ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውን የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንደ አቅሜ እያደረግኩ ነውን?” በማለት ልቡናችንን እንጠይቅ።"
“አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።” ሰቆ.ኤር 5፥21
"...ለሚመጣው ዘመን ለራሳቸው መልካም መሠረት የሚሆንላቸውን መዝገብ እየሰበሰቡ፥ መልካምን እንዲያደርጉ በበጎም ሥራ ባለ ጠጎች እንዲሆኑ፥ ሊረዱና ሊያካፍሉም የተዘጋጁ እንዲሆኑ ምከራቸው።" (1ጢሞ.6:18-19)
እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ። ሁላችሁም መልካም ምኞታችሁን በኮሜንት ግለጹ።
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
