HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 271
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+2130 días
Archivo de publicaciones
፩. ሕልም፦ ኮብራ እባብ በረንዳ ላይ ቀና ብሎ ሲያይ መፍራትና መደበቅ።
ፍቺ፦ በቤትና በሰላም ላይ የተቃጣ የትዕቢትና የማስፈራራት (የዛር/ዓይነጥላ) መንፈስ ውጊያ በመሆኑ በጸሎት መቆምን ይጠይቃል።
፪. ሕልም፦ በሰመመን ውስጥ የመታነቂያ ገመድ በግራ በኩል ተንጠልጥሎ ማየት።
ፍቺ፦ ሰይጣን ተስፋ ለማስቆረጥና የጭንቀት መንፈስ ለመልቀቅ የሚጠቀምበት የሽንገላ ውጊያ ስለሆነ አለመፍራትና በመስቀል መታጠርን ያሳስባል።
፫. ሕልም፦ ብዙ ጉንዳኖችን አራግፎ አንዷ ቀርታ ስትነክስ ማየት።
ፍቺ፦ ትናንሽ ፈተናዎችን ቢወጡም፣ ገና ያልተፈታ አንድ ሥር የሰደደ መንፈሳዊ ዕዳ ወይም ስውር ጠላት መኖሩን የሚጠቁም የማንቂያ ደወል ነው።
፬. ሕልም፦ የሰራሁትን እንጀራና ወጥ ሌላ ሰው ሲወስደው ማየት።
ፍቺ፦ "ለፍቶ ለሌላ" የመሆን ውጊያ ወይም በረከትን የሚቀማ የምቀኝነት መንፈስ መኖሩን የሚያሳይ ጥንቃቄ ነው።
፭. ሕልም፦ ውሻ ሲጮህብኝ አድሮ ጠዋት በሥራ ቦታ ሰዎች ሲጠምዱኝ ማየት።
ፍቺ፦ በሕልም የታየው የጠላት ጩኸት በገሃድ በሰዎች ልብ አድሮ ሰላምን ለመንሳት መነሳቱን የሚያሳይ የንቃት ምልክት ነው።
፮. ሕልም፦ ውሻ ሲልስና ሲያጫውት ማየት፣ ድመት ደጋግሞ ማየት።
ፍቺ፦ ጠላት "ወዳጅ መስሎ" ተላምዶ ለመቀመጥና በስውር ምቀኝነት ለመከታተል የሚጠቀምበት የሽንገላ መንገድ ነው።
፯. ሕልም፦ የሚያስፈራ ሰው ጉንጭን ሲስም ሮጦ በፎጣ ማበስ።
ፍቺ፦ ርኩስ መንፈስ ቁርኝት ሊፈጥር ቢሞክርም፣ ነፍስህ ግን በንቃት ተቃውማ ርኩሰቱን ያስወገደች መሆኑን የሚያሳይ የድል ምልክት ነው።
፰. ሕልም፦ እርጥብ (ጥሬ) ሥጋ ማየት ወይም መያዝ።
ፍቺ፦ የሕሊና ወቀሳ፣ የነፍስ ቁስል (ኃጢአት) ወይም በሐሜት የሚመጣ የቃላት ውጊያን የሚያሳይ የማንቂያ መልእክት ነው።
፩. ሕልም፦ ሰላማዊ ዝናብ ዘንቦ ንጹሕ ውኃ በቤት ውስጥ በእግር በኩል ሲገባና የእመቤታችን ሥዕል ውኃ በውኃ ሆኖ ሳይበላሽ ማየት።
ፍቺ፦ በቤትና በኑሮ መሠረት ላይ የሚፈስ አዲስ መለኮታዊ ጸጋና የተረጋገጠ የእመቤታችን ጥበቃ ምልክት ነው።
፪. ሕልም፦ ሦስት ጋቢ ደርቦ መልበስና ሦስት ቁልፎችን መቀበል።
ፍቺ፦ በሥላሴ አምላክነት የታጠረ እጥፍ ድርብ ክብር (ሞገስ) እና የተቆለፉ የሕይወት በሮች የሚከፈቱበት መንፈሳዊ ሥልጣን (መፍትሔ) የማግኘት ምልክት ነው።
፫. ሕልም፦ ከፀሐይ መውጫ ንስር ወጥቶ "በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ተጠመቅ" የሚል ድምፅ መስማት፣ ዝናብና ፀሐይ በአንድነት ማየት።
ፍቺ፦ በሰማዕቱ አማላጅነት የሚገኝ የነፍስ መታደስ፣ የጠላት ውድቀትና ወደ መድኃኔዓለም ፈውስ የሚመራ መለኮታዊ ጥሪ ነው።
፬. ሕልም፦ ራሴንና ፀጉሬን በዋና ገንዳ ውስጥ ብቻዬን ታጥቤ ወጥቼ ፎጣ መልበስ።
ፍቺ፦ ከቆየ መንፈሳዊ ሸክም (ገርጋሪ) ተላቆ በአዲስ ንጽሕና የመሸፈንና ለተባረከ ትዳር የመዘጋጀት የምሥራች ነው።
፭. ሕልም፦ በብርሃን የተከበበ ፬ ቁጥርና የጌታችን ሥዕል ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ሲጓዙ ማየት።
ፍቺ፦ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገርን፣ በወንጌል ቃል መመራትንና መለኮታዊ ጉብኝትን የሚያሳይ ታላቅ የጸጋ ሕልም ነው።
፮. ሕልም፦ ነጭ የለበሱ ሴቶች የማኅበር ፅዋ ይዘው፣ የኢትዮጵያ ባንዲራ ጥበብ ያለበት ልብስ ለብሰው ወደ ግቢ መግባታቸው።
ፍቺ፦ ቤትሽ የቅዱሳን ማደሪያና የሰላም ስፍራ እንዲሆን መመረጡን፣ በቃል ኪዳን መከለሉን የሚያሳይ የበረከት ምልክት ነው።
፯. ሕልም፦ ዘቢብ መብላት።
ፍቺ፦ በሥራ ላይ የሚገኝ ድንቅ ፍሬ፣ የሕሊና ዕረፍትና መንፈሳዊ ደስታን የሚያበስር ሲሳይ ነው።
፰. ሕልም፦ ድልድይ መሻገር።
ፍቺ፦ ከአስቸጋሪ የሕይወት ምዕራፍ ወደ ስኬትና ዕረፍት መሸጋገርን፣ በጠላት ላይ ድል መንሳትን የሚያሳይ ተስፋ ነው።
2ኛ መንፈሳዊ ሕልምና ፍቺዎቻቸው! ሕልማችሁን ጻፉልኝ መልሱን በዚሁ እነግራችኋለሁ!! https://www.youtube.com/live/0R_00dEaJjA?si=odwVtx7SCBboosTo
መምህር ተስፋዬ ያሳሰራቸው ደብተራዎች ከተፈቱ በኋላ ይኼንን ተናገሩ!! ለጥያቄዎቻችን ሁሉ ይኼ መልስ ነውና ተረዱ!! #መምህር_ግርማ_ወንድሙ #ክርስቶስ #ጸሎት https://youtu.be/hSpivYaZgFU?si=2dsbZIiI_MIk-fCs
መንፈሳዊ ሕልምና ፍቺዎቻቸው! ሕልማችሁን ጻፉልኝ መልሱን በዚሁ እንግራችኋለሁ! Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://youtu.be/-E4DQuQLet4
መምህር ተስፋዬ ጸበል ቦታ የገጠመው አሳዛኝ ታርክና እኛስ ምን እናድርግ? አያቷ በገዳም ትጸልይላታለች ልጅቷ ጠንቋይ ቤት ትካድማለች! #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ https://youtu.be/F5lqEmCxLRc
እንዲህ አይነት ድርጊቶች የስንቱን ትዳርና ኑሮ አበላሽቶ ይሆን ያሳዝናል!! የሴት ዛር ዓይነጥላ በሴቶች ላይ የሚያስከትለው መዘዝ!! //እንተዋወቃለን ወይ// https://youtu.be/0N-hm2l8rxM
ያለ ውሸት መኖር የማይችሉ ጉዶች ወይ ዘንድሮ የማንሰማው የለም!! https://youtu.be/iiZZQ2WF2QI?si=udmXzkpTd0rqrFGY
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ *የካቲት 11*»
(የማቴዎስ ወንጌል 26፡ 37-45)
=> ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር። ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው። ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ። አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ። ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው። ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ ጸለየና። አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ። ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው። ደግሞም ትቶአቸው ሄደ፥ ሦስተኛም ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ። ከዚያ ወዲያ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ። እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ እነሆ፥ ሰዓቲቱ ቀርባለች የሰው ልጅም በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።
መልካም ቀን ይሁንላችሁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
የሁለተኛው ቀን ቅዳሴ በላይቭ ይኼው ተከታተሉ ከመንበረ ፓትሪያርክ ቅድስት ማሪያም ገዳም https://youtu.be/NLEny-zKzMs
ጸሎታችን ቶሎ መልስ እንዲያገኝ ይኼንን 3 ነገሮች አሁኑኑ አድርጉ!! እጾማለሁ የምል ሁሉ ይኼንን መስማት አለበት!! የዘርፈ የሰሞኑን አነጋጋሪው ድርግት!!https://youtu.be/pmCJ7V4Znw4?si=frl_rkyvqV_1Ghji
ቅዳሴ ላይቭ ለመከታተል በዚህ ልንክ ግቡ፡ https://www.youtube.com/live/53cxq33I4qE?si=UjercaQ8VUqgk3HU
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
ማቴዎስ 22:34-40
ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ምላሽ እንዳሳጣቸው በሰሙ ጊዜ በአንድነት ወደ እሱ ተሰበሰቡ። ከመካከላቸውም አንድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ጠየቀው። “መምህር ሆይ፥ ከኦሪት ማንኛይቱ ትእዛዝ ትበልጣለች?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው፥ “አምላክህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹም ነፍስህ፥ በፍጹም ኀይልህ ውደደው። ታላቂቱና የመጀመሪያይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። የምትመስላት ሁለተኛይቱም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለው ናት።
«የዕለቱ መልእክታት»
- ሮሜ 12:1-17
- 2 ጴጥሮስ 1:10-16
- ሐዋ፡ሥራ 25:13-ፍጻሜ
ኑሯችሁ ላይ የምትጨምሯቸው 7ቱ መንፈሳዊ መሰላሎች!! በኑሯችንና በእምነታችን ይኼንን ከጨመራችሁ እመኑኝ ትለወጣላችሁ!! በዓብይ ጾም ይኼንን አድርጉ! #ጸሎት https://youtu.be/sA5LweuicAg?si=CGR8lhNDDxM36yn_
እንኳን ለታላቁ የዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት፣ የመጀመሪያው ሳምንት "ዘወረደ" ተብሎ ይጠራል።
፩. "ዘወረደ" ማለት ምን ማለት ነው?
ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም "ወረደ" ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት መውረዱን፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው መሆኑን (ምስጢረ ሥጋዌን) የሚያመለክት ነው።
አምላክ ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሳ ራሱን ዝቅ አድርጎ ወደ ምድር መምጣቱን የምናስብበት ሳምንት ነው።
"ዘወረደ" አምላክ ራሱን ዝቅ ያደረገበት ነውና እኛም በዚህ ሳምንት በትሕትና እራሳችንን ዝቅ አድርገን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን የምንማርበት ሳምንት ነው።
፪. የዐቢይ ጾም ስምንቱ ሳምንታት (እሑዶች)
1), ዘወረደ (የአሁኑ ሳምንት)
2), ቅድስት (ስለ ሰንበት ቅድስና የሚነገርበት)
3), ምኩራብ (ጌታ በምኩራብ ማስተማሩ)
4), መጻጉ (የታመመው ሰው መፈወስ)
5), ደብረ ዘይት (ጌታ ዳግም እንደሚመጣ የተነገረበት)
6), ገብር ኄር (ታማኝ አገልጋይ)
7), ኒቆዲሞስ (ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ መምጣቱ)
8), ሆሳዕና (ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም በክብር መግባቱ)
መልካም የዐቢይ ጾም !!!
ጸሎታችሁንና ስግደታችሁን እንዲህ ካደረጋችሁ የማታሸንፉት የለም!! ዲያብሎስን በማታለል እንዴት እናሸንፍ! በስግደት ወቅት የዲያብሎስ ፈተናዎች! #ስግደት #ንቁ https://youtu.be/Y8OGxkqvsgY
#_ታላቅ_የበረከት_ጥሪ_ለጎሮ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተ_ክርስቲያን!
ሼር በማድረግ የበረከቱን ጥሪ ለሌሎች አዳርሱ!
❤ የወለላይቱ እመቤት የኪዳነ ምህረት ልጆች በያላችሁበት የእመቤታችን ጸሎት እና ጸጋ በረከት አይለያችሁ። የተአምረኛዋ እና የስዕለት ሰሚዋ የጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ያልተከፈለ የመሬት 5 ሚሊዮን ብር ዕዳ አለባት። እንዲሁም ቦታዋ ጠባብ ስለሆነች 5 ሚሊዮን ብር ሊገዛ የታቀደ መሬት አለ።
❤ ስለዚህ እነዚህን ሁለቱን ታሳቢ በማድረግ ዛሬ የካቲት 7 ቅዳሜ እለት በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ማምሻ 12 ሰዓት በዩትዩብ፣ በፌስቡክ፣ በቲክቶክ በቀጥታ ስርጭት ወይም በ Live የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ስላለን የዚህን ታላቅ በረከት እንዳቅማችሁ ለመሳተፍ በሰዓቱ በላይቭ ጠብቁን!
❤ በተለይ ትምህርቴን የሰማችሁ፣ በትምህርቱ የተጠቀማችሁ የተለወጣችሁ፣ ጠበል ተጠምቃችሁ የተፈወሳችሁ፣ ዝክሩን በልታችሁ የቃል ኪዳኑን በረከት ያገኛችሁ ወዘተ ተማሪዎቼ እና ወዳጆቼ የኪዳነ ምህረትን የመሬት ዕዳ ለመክፈል እና መሬት ለመግዛት እንዳቅማችሁ ለመተባበር እንደማታሳፍሩኝ አውቃለሁ!
ኪዳነ ምህረት ለበረከት በቀጥታ ስርጭት ታገናኘን!
"ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" የሐዋ 20፥35
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
