es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 279
Suscriptores
Sin datos24 horas
+57 días
+3230 días
Archivo de publicaciones
«ለሟርተኞች ይድረስ! ተሰርዟል! ተቋርጧል ላላችሁ!» በክፉው መንፈስ የጥፋት አሠራር ውስጥ በአንድ ወጥነት ሳይለወጥ ሁላችን ጋር የሚመጣው ፈተና፤ በመንፈሳዊነት በኩል ያለውን እውነታና ሰማያዊ ኃይል
+3
«ለሟርተኞች ይድረስ! ተሰርዟል! ተቋርጧል ላላችሁ!» በክፉው መንፈስ የጥፋት አሠራር ውስጥ በአንድ ወጥነት ሳይለወጥ ሁላችን ጋር የሚመጣው ፈተና፤ በመንፈሳዊነት በኩል ያለውን እውነታና ሰማያዊ ኃይል ከዓይናችን ፊት በመጋረድ ዓለምን ብቻ የማሳየት አካሄዱ ነው፡፡ ዓለም የዲያቢሎስ ናትና፤ ዲያቢሎስ ሁሌ ዓለምን ያሳያል፡፡ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ውስጥ ባደረገው የመንፈሳዊነት ትግል ውስጥ፤ ፈታኝም ወደርሱ ቀርቦ የዓለምን መንግሥታትና ክብራቸውን ሁሉ አሳየው፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል 4፥8) የዛኔ ወደ ክርስቶስ ከውጪ ቀርቦ የነበረው፤ ዛሬ ከውስጣችን ያለው ፈታኝ፤ እንደ ጌታችን ከውጪ ወደ ውስጥ ሳይሆን፤ ከውስጥ ወደ ውጪ ዓለምን እያሳየን፤ በሥጋ ትሩፋቶች በኩል የሚመጡትን ውጤቶች፣ ምቾቶች፣ ጥቅሞች፣ ደስታዎች፣ እረፍቶች፣ ድካሞች፣ ጎዶሎዎች፣ ግማሽ ነገሮች ላይ ትኩረት እንድናደርግ፤ የምድራዊ አኗኗር ጥገኝትን ከኑሮአችን ድጋፍ ሥር ሲያኖር ጊዜ፤ ከነጠላ በታች የተከለለ ቅብ ጸጉርን አሲይዞ፤ ከዕድለኝነት ጀርባ ያልተነገረ ሙሰኝነት ውስጥ ከትቶ፤ ጠበል ጻዲቅም አስካሪ መጠጥም የሚጠጣ ጊዜን እንዳናሳልፍ አድርጎ፤ በመንፈሳዊውና በዓለማዊው ዓለም መካከል እያገለባበጠን፥ ዓለምን ባሳየን አቅም ልክ ለገንዘብ፣ ለርዮተ ዓለም እውቀት፣ ለጥበብና ለዝና በተግባር እንድንሰግድ አሰገደደን፡፡ እንዲህ አልሆንም ወይ በእውነት! ሁለ በክፋት መመላለስ የእኛ የሰዎች ግልጽ ባሕሪይ ከሆነ እኮ ቆየን ከላይ ስንታይ ክርስቲያን እንመስላለን ውስጣችን ግን ባዶ ነው። እግዚአብሔር አምላክ ይሰውረን፣ ይማረን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

መንፈሳዊ ውግኣት ቀጻሊ እዩ፤ ክፈላለዩ ይኽእሉ እዮም ግን ፈጺሞም ኣይውድኡን እዮም። ብስጋ ክሳብ ዘለኻ፡ ነዞም ክሳብ ሞት ምሳኻ ዝቕጽሉ ውግኣት ትግዛእ ኢኻ። በዚ ድማ ቅዱስ ጴጥሮስ ሃዋርያ ".... ኣብዚ ዝጸናሕኩምሉ ዘመን ብፍርሒ ተመላለሱ፤"(1ጴጥ 1፡17) ይብል። "ፍርሒ" ክብል ከሎ ፍርሒ ኣጋንንቲ ማለት ኣይኮነን፣ እንታይ ደኣ ናብ ጥንቃቐን ኩሉ ግዜ ኣብ ጥንቃቐን ዝመርሕ ዓይነት ፍርሒ ማለቱ እዩ። ንውልቀ ሰባት እቲ ኲናት ክሳብ ሞት ይቕጽል፡ እንተ ንዓለም ግን እቲ ኲናት ንዘልኣለም ክሳብ መወዳእታ ኩሉ ዘመናት ይቕጽል። ዲያብሎስ ካብ ቤት ማእሰርቱ ምስ ተፈትሐ እውን ንህዝብታት ከታልል ክወጽእ እዩ (ራእ 20፡7,8)። "ኣብ ዳሕረዋይ ዘመን ገለ ካብ እምነት ክወጹ እዮም" (1ጢሞ 4፡1)፡ ከምኡ'ውን፡ "ዘመናት ሓደጋ ክመጽእ እዩ" (2ጢሞ 3፡1)። ቅድሚ ምጽኣት ክርስቶስ ቅድም ውድቀት ክመጽእ እዩ (2ተሰ. 2፡3)፡ ዲያብሎስ ድማ ዝከኣሎ ክገብርን ናብ ምድሪ ክወርድን እዩ፡ " ሓጺር ግዜ ከም ዘለዎ ስለ ዝፈልጥ፡ ብዓብዪ ቁጥዐ።" ." (ራእ 12፡12)። እዚ ቀጻሊ ውግእ ዲያብሎስ ኣብ ቅዱሳን ግዜ ዝያዳ ክኸብድ ይኽእል እዩ። ዲያብሎስ ዝኾነ መንፈሳዊ ስራሕ ክንጅምር ከለና ኣዝዩ የሕርቕ እሞ እቲ ግዳይ ከይሃድም ኩሉ ዓቕሙ ይጥቀመሉ። በዚ ኸምዚ፡ መንፈሳዊ ዕዮ ምስ እንጅምር፡ ውግኣቱን መሳርሕታቱን ብዙሕ መሰናኽልታቱን ክጥቀመሉ ይጅምር። መንፈሳዊ ስራሕ ንጅምር፡ ንሱ ድማ ተቓውሞ ይጅምር። እዚ ንመንግስቱ ኣብ ሓደጋ ከም ዘእቱ ፈሊጥና ምስ ኣምላኽ ዝዀነ ይኹን ርክብ ክሳዕ ዘሎና ምቹእ ኣይኰነን። እነሆ ገለ ድንቂ ቃላት ካብ "ገነት ኣቦታት"፡ "ደወል ፍርቂ ለይቲ ንጸሎት ክድወል ከሎ ንመነኮሳት ንጸሎት የበራብሮ ጥራይ ዘይኮነስ ሰይጣውንቲ ውን ንመነኮሳት ክቃለሱን ከይጽልዩን ይለዓዓሉ።" ..."ከምዚ ድማ ቅዱስ ኤቫግሮስ "ቅዱስ ጸሎት ምስ ጀመርካ ንዝኾነ ክወርደካ ድሉው ኩን" በለ።

Lolli hafuuraa itti fufiinsa qaba; garaagarummaa qabaachuu danda’u garuu gonkumaa hin dhumne. Hanga foon keessa jirtutti lola hanga du'aatti si waliin itti fufu kanaaf bitamta. Akkasitti qulqulluu Pheexiroos ergamaan ".... yeroo as turtan hundumaa sodaadhaan of gaggeeffadhaa;"(1Phex 1:17) jedha. "Sodaa" jechuun sodaa seexanaa jechuu osoo hin taane, gosa sodaa of eeggannoo fi yeroo hunda of eeggannoo gochuutti nama geessu jechuu isaati. Namoota dhuunfaaf waraanni hanga du’aatti itti fufa, addunyaaf garuu waraanni bara baraan hanga dhuma baroota hundaatti itti fufa. Seexanni mana hidhaa isaa keessaa yeroo hiikamullee saboota gowwoomsuuf ni ba’a (Mul. 20:7,8). "Bara boodaatti gariin amantii irraa ni fagaatu" (1Xim. 4:1), akkasumas, "yeroon balaan ni dhufa" (2Xim. 3:1). Dhufaatii Kiristoos dura, dursee kufaatiin ni dhufa (2Tas. 2:3), seexannis waan danda'u hunda ni godhee gara lafaatti ni gad bu'a, " yeroo gabaabaa akka qabu waan beekuuf dheekkamsa guddaa qaba." ." (Mul 12:12). Lolli seexanaa itti fufee jiru kun yeroo qulqulluutti daran cimaa ta’uu danda’a. Seexanni hojii hafuuraa kamiyyuu yeroo jalqabnu baay'ee aaree akka adamsichi isa hin miliqneef meeshaa isaa hundaatti fayyadama. Kanaaf, hojii hafuuraa yommuu jalqabnu, lola isaa, meeshaalee isaa fi gufuuwwan hedduutti fayyadamuu jalqaba. Hojii hafuuraa jalqabna, inni immoo mormii jalqaba. Kun mootummaa isaa balaadhaaf saaxiluu isaa beekee hamma nuti Waaqayyoo wajjin walitti dhufeenya kamiyyuu qabnutti mijataa miti. Jechoonni dinqisiisoo "Jannata Abbootii" irraa kunooti, ​​"Halkan walakkaa salaataaf bilbilli yommuu bilbilamu monoksoonni akka kadhatan dammaqsuu qofa osoo hin taane seexannis monoksota loluuf kadhannaa akka hin salaanne dhorkuuf ka'u." ..."Akkasitti qulqulluun Evagriyos "Yeroo kadhannaa qulqulluu jalqabdu waan si mudatu hundaaf qophaa'i" jedhe.

Spiritual wars are continuous; they may vary but never end. As long as you are in the flesh, you are subject to these wars which continue with you until death. Thus, St. Peter the apostle says, ".... conduct yourselves throughout the time of your stay here in fear;"(1 Pet 1:17). By "fear" he does not mean the dread of devils, but he means the kind of fear which leads to precaution and always being on guard. For individuals, the war continues till death, but as for the world, the war continues for ever until the end of all ages. Even when the devil is loosed out from his prison, he shall go out to deceive the nations (Rev. 20:7,8). "In the latter times, some shall depart from the faith" (1 Tim. 4:1), and, "perilous times shall come" (2 Tim. 3:1). Before the coming of Christ, there shall come a falling away first (2 Thess. 2:3), and the devil will do his best and will come down to earth, " having great wrath, because he knows that he has a short time." (Rev 12:12). This continuing war of the devil may become more severe during holy times. The devil gets very annoyed when we start any spiritual work and uses all his means lest the prey should escape him. Thus, when we start spiritual work, he starts using his wars, devices, and many obstacles. We start spiritual work, and he begins resistance. He is not comfortable as long as we have any relationship with God, knowing that this endangers his kingdom. Here are some wonderful words from "The Paradise of the Fathers", "When the bell rings in the middle of night for prayers, it does not only awake the monks to pray but the devils are also aroused to fight monks and prevent them from praying..."And thus, St.Evagrius said, "When you begin a holy prayer, be ready for whatever may befall you."

መንፈሳዊ ጦርነቶች ቀጣይ ናቸው; ሊለያዩ ይችላሉ ነገር ግን አያልቁም። በሥጋ እስካላችሁ ድረስ እስከ ሞት ድረስ ከእናንተ ጋር ለሚሆኑ ጦርነቶች ተገዙ። ስለዚህም ሐዋርያው ​​ቅዱስ ጴጥሮስ “....በዚህ በምትኖሩበት ዘመን ሁሉ በፍርሃት ኑሩ” (1ጴጥ. 1፡17) ይላል። "ፍርሃት" ሲል የሰይጣንን መፍራት ሳይሆን ወደ ጥንቃቄ የሚያመራውን እና ሁል ጊዜም ነቅቶ የሚጠብቅ አይነት ፍርሃት ማለት ነው። ለግለሰቦች፣ ጦርነቱ እስከ ሞት ድረስ ይቀጥላል፣ ነገር ግን ዓለምን በተመለከተ፣ ጦርነቱ እስከ ዘመናት ሁሉ ፍጻሜ ድረስ ለዘላለም ይቀጥላል። ዲያብሎስ ከእስር ቤት በተፈታ ጊዜ አሕዛብን ሊያታልል ይወጣል (ራዕ. 20፡7፣8)። “በኋለኛው ዘመን አንዳንዶች ሃይማኖትን ይክዳሉ” (1 ጢሞ. 4፡1) እና፣ “የሚያስጨንቅ ዘመን ይመጣል” (2ጢሞ. 3፡1)። ከክርስቶስ መምጣት በፊት መጀመሪያ ውድቀት ይመጣል (2ኛ ተሰ. 2፡3) ዲያብሎስም የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል ወደ ምድርም ይወርዳል፣ “እጅግ አጭር ጊዜ እንዳለው ስለሚያውቅ በታላቅ ቁጣ ይወርዳል። ." (ራእይ 12:12) ይህ ቀጣይነት ያለው የዲያብሎስ ጦርነት በተቀደሰ ጊዜ የበለጠ ከባድ ሊሆን ይችላል። ማንኛውንም መንፈሳዊ ሥራ ስንጀምር ዲያብሎስ በጣም ይናደዳል እናም አዳኙ እንዳያመልጥ ሁሉንም አቅሙን ይጠቀማል። ስለዚህም መንፈሳዊ ሥራ ስንጀምር ጦርነቱን፣ መሣሪያዎቹን እና ብዙ መሰናክሎችን መጠቀም ይጀምራል። እኛ መንፈሳዊ ሥራ እንጀምራለን, እርሱም ተቃውሞ ይጀምራል. ይህ መንግሥቱን አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን እያወቅን ከእግዚአብሔር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እስካለን ድረስ አልተመቸም። "የአባቶች ገነት" ከሚለው ድንቅ ቃል እነሆ "በእኩለ ሌሊት ለጸሎት ደወል ሲደወል መነኮሳትን ለመጸለይ የሚቀሰቅሰው ብቻ ሳይሆን ሰይጣኖችም መነኮሳትን ለመታገል እና እንዳይጸልዩ ይከላከላሉ. ..."እንዲሁም ቅዱስ ኢቫግሪየስ "ቅዱስ ጸሎት ስትጀምር ለሚደርስብህ ሁሉ ተዘጋጅ" አለ:: #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ያሳዝናል! ልጆቹ ሲያልቁ፣ ሲገደሉ ዝም፣ ጭጭ የምል ጳጳስና አገልጋይ ወዮ! ወዮ || የብጹዕ አቡነ ሉቃስ የተግሳጽ መልእክት #ሸር ይደረግ #ethiopia 😰😭 https://youtu.be/hsXhjdnU1Wg?si=haZgQkYU2BXEhdut

🛑ሩካቤ ሥጋ እና የጸሎት ሕይወት | ከሩካቤ ሥጋ በፊት መጸለይ | ቅድመ ሩካቤ ሥጋ ዝግጅት #በማለዳ_ንቁ_2023 ቀሲስ ሄኖክ ወልደ ማሪያም #ethiopia 😰 https://youtu.be/SmvTCZoOE58 https://www.tiktok.com/@iam_haile/video/7338350619557727493?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7322748943480522246

ውድ ቤተሰቦቼ! በTikTok ትምህርቶችን ለመከታተል፣ ለመወያየት እና ጥያቄ ለማቅረብ ወደ ትክቶክ ደግሞ ይምጡና ይቀላቀሉን! https://www.tiktok.com/@iam_haile/video/7338348034507508997?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7322748943480522246

ብዙ ሰዎች ማመን ያቃታቸው መራራው እውነት || መፅሐፍ ቅዱስን በእርግጫ ያሉት ፖስተሮች ጉድ || ተሀድሶዎች የሌሊት ወፍ ናቸው! በማለዳ ንቁ 2024 🙏🙏😭🙄 https://youtu.be/WdkrWy-Dqmo

«ባልታጠቡ ጋኖች ላይ ወይኑ አይሞላም፡፡ ከክፋት ባልጸዳ ልብ ላይ ሰማያዊ ጥበብ አይኖርም፡፡ ከምቀኝት ባልወጣ አስተሳሰብ ላይ ብልጽግና አይመጣም፡፡ ከተንኮል ባልተለየ እቅድ ላይ ስኬት አይኖርም፡፡ ንስሐ ባልገባ ክርስትና ላይ የአምላክ ንጹሕ ሥራዎች አይጸኑም፥ ኃጢአት እያጎመዘዘ ያናውጣቸዋልና፡፡ የአዲሱ አቁማዳ ባሕሪይ አዲሱን የወይን ጠጅ ይቀበላል፡፡ አዲሱም የወይን ጠጅ አዲሱ አቁማዳ ይስማማዋል፡፡ ሁለቱ እርስ በእርስ ይጠባበቃሉ፡፡ ንስሐ የገባ ሕይወትና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ በእርግጥም እርስ በእርሳቸው ይጠባበቃሉ፡፡ ሕግ በሰው ትከበራለች፥ ሰውየውም በሕጊቱ ይከብራል፡፡ ወንጌል በምዕመን ትገለጻለች፥ ምዕመንም በወንጌል ይገለጻል፡፡ እኛ አላወቅን እንደሆነ እንጂ፤ እርስ በእርስ የምንጠባበቀው ከዲያቢሎስ ሥራዎች ጋር ነው፡፡ ውሸት ተነግራ ለመደመጥ እኛን ትጠብቃለች፥ እኛም ውሸታችን እንዳትገለጥ ሸፍነን እንጠብቃታለን፡፡ ንፉግነት በኛ ለመታየት ተርታዋን ትጠብቃለች፥ እኛም ሐብታችን እንዳይሳሳ ንፉግነትን እንጠብቃታለን፡፡ ስድብ ከኛ ለመውጣት ስትቁነጠነጥ ትውላለች፥ እኛም በአስፈላጊ ቦታ የምንመዠርጣቸው ብዙ ስድቦች አሉን፡፡ ቅናት በምናየው ነገር ላይ ለመገኘት ወረፋ ስትይዝ፥ በቅርብ ወዳጆቻችን ከፍታ እየተበሳጨን እንደምናገለግላት አስቀድማ አውቃ ነው፡፡ አዎ .. እርስ በእርስ የምንጠባበቀው ከክፉ መናፍስት ጋር ነው፡፡ እውነትን ሸሽተን፣ ትዕግስትን ንቀን፣ ጸጋን አዋርደን፣ ፍቅርን ጠልተን፣ እርጋታን አጥተን፣ ድሎትን ናፍቀን፣ ዝሙትን መርጠን፤ ከሕልውናችን ሥር አገዛዙን እየሰደደ አዙሪቱን እንዲያጠብቅብን ጠበቃ የቆምነው ለዲያቢሎስ መንፈስ ነው፡፡ ስለዚህ ጠላት ልክ ነዋ! ለምን ታሰቃየኛለህ ትለው ዘንድ አትችልም፡፡ ፈቃዱን፣ ስሜቱን፣ ጠባዩንና ሥርዓቱን እስከጠበክለት ድረስ፤ እርሱ ደግሞ አንተን በክፋት ይጠብቅብህ ዘንድ መብት አለው፡፡ በጎነትን ሳታስቀድም፣ ርኅራኄን ሳትወደው፣ ምቀኝነትን ሳትተወው፣ ጉቦን ሳትጠየፈው .. በጠቅላላው ኃጢአትን ሳትናዘዘው፤ "ከክፉ ሁሉ አድነኝ" እንጂ ብለህ መጸለይ መንፈሳዊ ስላቅ ይሆንብሃል፡፡ ከተኩላው በረት ሰተት ብለህ ገብተህ ከተኩላ አስጥለኝ እንደምን ትላለህ?» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«በኃጢአት ድምፆች የሰነበተ ጆሮ ቃለ እግዚአብሔርን ጸንቶ መስማት አይሆንለትም፡፡ በኃጢአት ቃላት የከረመ አንደበት ጽድቅን በርትቶ ማውራት አይሳካለትም፡፡ በኃጢአት ትዕይንቶች የተከበበ ዓይን ሃይማኖታዊ ምልከታው ሊዘልቅለት አይችልም፡፡ በኃጢአት አሳቦች የተዳከመ አእምሮ በመንፈሳዊ ቦታ ላይ ንቁ ሆኖ አይቆይም፡፡ ምክንያቱም በአረጃው አቁማዳ አዲሱ ወይን አይሞላም፡፡» "ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም" (የዮሐንስ ወንጌል 3፥20 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

Diabolic wars fight all; no one escapes from them. When we speak of these wars, we mean the wars waged by the devil and all his forces and supporters. Since the days of Adam and Eve and their son Cain the devil has been fighting, trying his best to throw men under the condemnation of eternal death. He overthrew prophets, apostles, and persons who had the Spirit of the Lord such as David and Samson who repented, and King Saul whom God refused and the Spirit of the Lord departed from, " and a distressing spirit from the LORD troubled him."(1 Sam. 16:14). So, do not think that diabolic wars are directed only at beginners or sinners. Satan fights all, including those who may be growing in grace, he fights them even more. Thus, everyone must be on guard and not think themselves above certain wars. Let us remember how David the prophet was fought by adultery and fell into that sin in spite of having the Spirit of the Lord and in spite of having been the anointed of the Lord... the devil seeks any prey. St. Peter described him using some grave words, " ... your adversary the devil walks about like a roaring lion, seeking whom he may devour."(1 Pet 5:8).He wanders about continually to catch his prey. When the Lord asked him (in the story of Job), "From where do you come?" , he answered plainly, "from going to and fro on the earth and from walking up and down on it" (Job 1:7, 2:2). Of course the purpose of this wandering is seeking any prey to overthrow. The devil does not get desperate however strong the person whom he fights is. It is even said of sin, "For she has cast down many wounded, And all who were slain by her were strong men." (Prov 7:26). The devil did not even hesitate to fight the twelve disciples of Christ. The Lord spoke to St. Peter the apostle about this, "Satan has asked for you, that he may sift you as wheat , But I have prayed for you, that your faith should not fail " (Luke 22:31, 32 ). We also remember Elijah, the great prophet whom God lifted to the heavens, of whom St. James the apostle said, "Elijah was a man with a nature like ours " (James 5:17) (H.H. Pope Shenouda III) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ብዙ ሟርተኞች ሊያስተምሩና ልገስጹ ይችላሉ || የዘመኑ ታላቁ መርዶ የመለካዊነት ጥግ "ቅዱስ አብይ" ተብሎ ተቀደሰለት በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia 😰🙄 https://youtu.be/rphXdpvZYV8

«ሰዎች ወህኒ ሳይወርዱ ቤት ውስጥ እያሉ ነጻነትና ሰላም፣ ደስታና እፎይታ አጥተው የታሰሩበት ጊዜ በኛ ዘመናዊ ትውልድ ላይ ተባብሶአል፡፡ ምክንያቱም በቤተሰቦች መካከል የቤት ዕቃ እንጂ የእግዚአብሔር
«ሰዎች ወህኒ ሳይወርዱ ቤት ውስጥ እያሉ ነጻነትና ሰላም፣ ደስታና እፎይታ አጥተው የታሰሩበት ጊዜ በኛ ዘመናዊ ትውልድ ላይ ተባብሶአል፡፡ ምክንያቱም በቤተሰቦች መካከል የቤት ዕቃ እንጂ የእግዚአብሔር ሰላም የለም። ሰላም ሲጠፋ፤ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ፣ ኩርፊያ፣ ጸብ፣ ብቸኝነት በቤቱ እንዲነግሥ ይጠበቃል፡፡ እንደ ቤተሰብ ሳይሆን እንደ ባላንጣ ለመኖር ሰዎች ይገደዳሉ፡፡ ስለዚህ ሰዎች ቤት ገብቶ ሰላም ባጣ ሁኔታ ከመቆየት ውጪ በየመጠጥ ቤቱ ማምሸትን አማራጭ ያደርጋሉ፡፡ ጌታችን ለሐዋሪያቱ "ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ" የሚል ቃል እንዳሰተላለፈላቸው በሉቃስ 10፥5 ላይ እናገኛለን፡፡ የሰላም አምላክ የሰላምን ዋጋ ያውቃል፡፡ ይሄ መለኮታዊ ሰላም ያጠረው ቤት፤ በፍጹም ሰላማዊ መሆን አይችልም፡፡ ለብርጭቆና ለሲኒ የተመቸ ቦታ ሰጥተን ስናበቃ፤ ለእግዚአብሔር የሚሆንን ቦታ ከቤታችን ስላጣን በተቀደሰ ኑሮ ምክያትነት የሚመጣውን ሰላም ለማጣጣም እንዳንታደል መናፍስት የቤተሰባችንን መንፈሳዊ መስመር አቅጥነውብናል፡፡ እንደዚህ ሲሆን ታዲያ ቤቱ በራሱ ነገር ተሸካሚ ይሆናል።» <<እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል፥ አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።>> (1ኛ ዮሐንስ 4፤16) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ዶክተር ሆኖ እንዴት ጸበል ይሄዳል ይሉኝ ነበር || አንደ ታቦት አንደ ጣዖት መሆንን እናቁም || ሰውነታችንን፣ ጫማችንን የሚያሸቱና የሚያገሙ መንፈሶች 😭😰🙄 https://youtu.be/0ues_aslv9c

◈ ቤትህ ውስጥ ከፍተህ የረሳኸው ባንቧ ቢኖርና ድንገት ሌሊት ከእንቅልፍህ ስትነቃ መሬቱ እንዳለ በውኃ ተጥለቅልቆ ብታገኝ በቅድሚያ ምን ታደርጋለህ? የፈሰሰውን ውኃ ለመጥረግ ወይስ የሚፈሰውን ቧንቧ
◈ ቤትህ ውስጥ ከፍተህ የረሳኸው ባንቧ ቢኖርና ድንገት ሌሊት ከእንቅልፍህ ስትነቃ መሬቱ እንዳለ በውኃ ተጥለቅልቆ ብታገኝ በቅድሚያ ምን ታደርጋለህ? የፈሰሰውን ውኃ ለመጥረግ ወይስ የሚፈሰውን ቧንቧ ለመዝጋት ነው የምትቸኩለው? ◈ ቧንቧውን ሳትዘጋ መሬት ላይ ያለውን ውኃ ለማፈስ ብትሞክር ትርፉ ድካም ነው። ቀኑን ሙሉ ስትዝቅ ብትውል ቤትህ የሞላውን ውኃ አታጎድልም። እናስ? ቧንቧውን ዝጋዋ! ◈ በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ መፍትሔ በማታገኝበት ነገር ላይ ጊዜህን አታባክን። ለዚህ የሚዳርገኝ መነሻው ምክንያት ምንድን ነው? ብለህ ራስህን ጠይቅ። አእምሮህ ውስጥ የሞሉትን ክፋቶች ከመቁጠር በላይ እነዚያ ክፋቶች የገቡበትን አንድ ቀዳዳ ወይም ሽንቁር ለማወቅ ጣር። እርሱን ያወቅኸው ቀን ለችግርህ ትልቁን መፍትሔ አብረህ ታገኛለህ። ያን ቀዳዳ ከዘጋህ ወይም ምንጩን ካደረቅኸው የቀረው ቀስ እያለ ተኖ መጥፋቱ አይቀርም። ከመውደቅህ በላይ የውድቀትህ ምክንያት ያስጨንቅህ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube