es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 276
Suscriptores
+524 horas
+117 días
+3430 días
Archivo de publicaciones
ግንቦት ፳፱/29/ በዚችም ዕለት ከአንጾኪያ ገዳም አባ ስምዖን አረፈ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዮሐንስ የእናቱ ስም ማርታ ነው ስለ ርሱም ድንቆች ተአምራት ሆኑ። ይኸውም እናቱ ገና ሳትፀንሰው መጥ
ግንቦት ፳፱/29/
በዚችም ዕለት ከአንጾኪያ ገዳም አባ ስምዖን አረፈ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዮሐንስ የእናቱ ስም ማርታ ነው ስለ ርሱም ድንቆች ተአምራት ሆኑ። ይኸውም እናቱ ገና ሳትፀንሰው መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ እርሷ መጥቶ የዚህን የቅዱስ ስምዖንን መወለድ ነገራት ከእርሱም የሚሆነውን ገለጠላት። ተወልዶም ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ በአንጾኪያ ወደአለ ገዳም ሔደ። ራሱንም ወደ ምንኵስና ቀንበር ውስጥ አስገብቶ ታላቅ ገድልን ተጋደለ። መላእክትም አባ ጳኵሚስን እንደ አስተማሩት በየሌሊቱ ሁሉ እየተገለጡለት የምንኵስናን ገድል አስተማሩት። የማይጠፋ የምንኵስናንም የገድል አሠራር ገለጡለት። እርሱም አጽንቶ ሥጋ ከለበሱ ሁሉ አብዝቶ ተጋደለ መላእክትም ሁልጊዜ መንፈሳዊ ምግብ ያመጡለት ነበረና። ብዙ ከመጋደሉ የተነሣ ከደንጊያ ምሰሶ ላይ ወጥቶ በላይዋ ሰባት ዓመት ቆመ። ከዚህም ወደሌላ ተራራ ሒዶ በሠራው የደንጊያ በዓት ውስጥ እስከ ሃያ ዓመት ፍጻሜ ከእርሷ ሳይወጣ ሃያ ዓመት ኖረ። ከዚህ በኋላም ደግሞ ከታላቅ ተራራ ራስ ላይ ወጥቶ በላዩ አርባ አምስት ዓመት ኖረ። መላው ዕድሜውም ሰማንያ ስምንት ዓመታት ነው። ይኸውም በአባቱ ቤት ሰባት በአንጾኪያ ገዳም ዘጠኝ ዓመት በምሰሶ ላይ ሰባት ዓመት በደንጊያ ውስጥ ሃያ ዓመት ደግሞ በተራራ ላይ ቁሞ የኖረበት አርባ አምስት ዓመት በጠቅላላ ሰማንያ ስምንት ነው። ተአምራቱን ግን መቁጠር የሚችል የለም ከእርሳቸውም በገድሉ ተጽፎ አለ። ብዙ የሆኑ ድርሳናትንና ተግሣጽን ደረሰ እነርሱም ለሁሉ የሚጠቅሙ ናቸው። ይልቁንም ለመነኰሳት ከቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትም ብዙዎቹን ተረጐመ። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239

የመናፍስትን ውጊያና ሴራ ባለመረዳተና ባለማወቀ ልጄን ብዙ ጎዳኋት!! እናቶች በአዶናይ ንግግር ተቆጡ!! የተሳሳቱ የመተጫጨትና የጓደኝነት መንገዶች! https://youtu.be/CAdTGZxMTdU?si=bhUHM-JuyDKnDKSw

ግንቦት ፳፰ /28/ በዚችም ዕለት የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሥጋ ወደ ቆጵሮስ ደረሰ። ይህም እንዲህ ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ መንበረ ሢመቱ እንደማይደርስ ትንቢት እንደተናገረበት ወደ ቆጵሮስ ሳይደር
ግንቦት ፳፰ /28/
በዚችም ዕለት የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሥጋ ወደ ቆጵሮስ ደረሰ። ይህም እንዲህ ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ መንበረ ሢመቱ እንደማይደርስ ትንቢት እንደተናገረበት ወደ ቆጵሮስ ሳይደርስ በመርከብ ውስጥ ሳለ ግንቦት ዐሥራ ስድስት ቀን አረፈ። በአረፈም ጊዜም በመርከብ ጭነው ወደ ቆጵሮስ ከተማ አደረሱት። ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ መጡ ከሳቸውም ጋር ወንጌሎች መስቀሎች መብራቶችና ማዕጠንቶችም ይዘው ነበር የሐዋርያት ጉባኤ ከታላቂቱ ቤተ ክርስቲያን እስኪያደርሱት በዝማሬና በማኅሌት በሚገቡት ጸሎቶች ሁሉ እያመሰገኑ ሥጋውን ተሸከሙ። ካህናቱም መቃብሩን በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ሊያዘጋጁ ወደዱ። ቀድሞ ስለ ክፉ ሥራቸው ቅዱስ ኤጲፋንዮስ አውግዞአቸው የነበሩ ሁለት ዲያቆናት ተቃወሟቸው። ስለዚህም አርባ ቀን ተቀመጠ ነገር ግን ሽታው እንደ ሙታኖች ሽታ አልተለወጠም እንደ አንቀላፋ ሰው ሆነ እንጂ። ከዚህም በኋላ አንድ ደግ ዲያቆን ወደ ቅዱሱ ሥጋ ቀርቦ አባቴ ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ አንተ ባለሟልነት እንዳለህ እኔ አውቃለሁ። ብትፈቅድስ ክፉዎች ተቃዋሚዎችን ልታሸንፋቸው ትችላለህ አለ። የቅዱስ ኤጲፉንዮስንም እጅ ይዞ ምድሩን መታባት በዚያንም ጊዜ ሁለቱ ዲያቆናት በግምባራቸው ተደፉ። ለመሞትም ደረሱ ወደ ቤታቸውም ወስደዋቸው ሞቱ። ቅዱስ ኤጲፋንዮስንም ካህናቱ በሚጣፍጡ ሽቱዎች ገነዙት። በከበሩ ልብሶችም ጠቅልለው ከከበረ ደንጊያ በተሠራ ሣጥን ውስጥ ጨምረው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀበሩት። ቀድሞ በሕይወቱ ሳለ እንደሚሠራው ከሥጋው ድንቆች ተአምራት ተገለጡ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

መምህር ተስፋዬና እፎይ ወንድማችን የነገሩን መልካም ዜና!! በሱባኤ ወቅት የምንጠይቃቸው ነገሮች ምንድናቸው? ባሎችና ምስቶች ልታዳምጡት የሚገባ ወሳኝ መልዕክት!! https://youtu.be/1kXCaQFBHXc?si=SJ6sOmlnzBWX0Pks

«ጠላት ይፈር፣ ይቃጠል!» የአባታችን የመምህር ግርማ ወንድሙ አገልግሎት ቀጥሏል ቀጣይ ሰኔ 8/10/2017 ዓ.ም በአያት ቅዱስ ፋኑኤልና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት እና የፀበል
«ጠላት ይፈር፣ ይቃጠል!» የአባታችን የመምህር ግርማ ወንድሙ አገልግሎት ቀጥሏል ቀጣይ ሰኔ 8/10/2017 ዓ.ም በአያት ቅዱስ ፋኑኤልና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት እና የፀበል አገልግሎት ይከናወናል። ሁላችሁም ቤተሰቦቼ ተጋብዛችኋል። ስትጠይቁኝ ለነበራችሁ ሁሉ ይኼ መረጃ ይድረሳችሁ ላልሰሙት አሰሙ ሸር ማድረጋችሁን በጭራሽ እንዳትረሱ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ግንቦት ፳፯ /27/ በዚችም ዕለት የማርያና የማርታ ወንድም ጻድቅ አልዓዛር አረፈ። ይህንንም ጻድቅ ሰው በአራተኛ ቀን ከመቃብር ከአስነሣው በኋላ በዚሁ ሳምንት ውስጥ መድኃኒታችን መከራ ተቀብሎ ተሰቅ
ግንቦት ፳፯ /27/
በዚችም ዕለት የማርያና የማርታ ወንድም ጻድቅ አልዓዛር አረፈ። ይህንንም ጻድቅ ሰው በአራተኛ ቀን ከመቃብር ከአስነሣው በኋላ በዚሁ ሳምንት ውስጥ መድኃኒታችን መከራ ተቀብሎ ተሰቅሎ ሞተ። ከትንሣኤውም በኋላ አልዓዛር ከሐዋርያት ጋራ አንድ ሆነ። አጽናኝ መንፈስ ቅዱስም በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ ጸጋውን ተቀበለ። ሐዋርያትም በቆጵሮስ አገር ላይ በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። በሹመቱም አርባ ዓመት ኑሮ በሰላም በፍቅር አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#መስተፋቅር_ጥበብ_እንጂ_አጋንንታዊ_ሥራ_መሆኑን_በጭራሽ_አላውቅም_ነበር! ባለትዳሮች እጮኛሞች የግደታ ልታዳምጡት የሚገባ ትምህርት! በማስቲካ የተደገመ መተት! https://youtu.be/UR1ZGx_Isl4?si=r81G2in3uikbZTPD

#መታቹም_መርጌታ_አስመታቹም_መርጌታ_አሳዛኙ_የመጠላለፍና_የውድቀት_ህይወት!! ወንዶችን ሆዳቸውን እንዳረገዘች ሴት የሚነፋ አጋንንትና ሴራው!! #ethiopia https://youtu.be/-di4v77nPZE

+++ ተወዳጆች ሆይ! አንድ እንግዳ ወደ ቤታችን ሲመጣ ቤታችንን እንደምን እንደምናሰናዳው ሁላችንም እናውቀዋለን። ሁላችንም እንግዳችንን ደስ የሚያሰኘውን ነገር ለማድረግ የምንቸኩል አይደለንምን? ለእንግዳችን የሆነ ነገር ባናደርግለት፥ እንግዳችን በመምጣቱ ደስ ተሰኝተን እርሱን ደስ የሚያሰኝ ነገር ባናደርግለት፥ ግን ደግሞ በመምጣቱ ደስ እንደተሰኘን ብንነግረው እንግዳችን በፍጹም አያምነንም። በእንግዳችን መምጣት ደስ እንደተሰኘን ከቃላት ባለፈ በገቢር መግለጥ አለብንና። እንኪያስ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕይወታችን ከመጣ ደስ መሰኘታችንን በገቢር ልንገልጽ ያስፈልጋል። እንግዳችን ክርስቶስን የሚያስቆጣ ነገር ልንፈጽም አይገባንም። +++ እንግዳ ሲመጣ ቆሻሻ ልብስ አይለበስም። እንግዳ ሲመጣ የሚያስጸይፍ ነገር አይነገርም። ክርስቶስም በሕይወታችን ውስጥ እንዲኖር ስንፈልግም ቖሻሻ ልብሳችንን (ማንነታችንን) አውልቀን ልንጥል ያስፈልጋል፤ አስጸያፊ ነገራችንን ልንተው ያስፈልጋል። እንግዳ ሲመጣ ቤት ያፈራውን ሁሉ ይቀርብለታል። ክርስቶስ ወደ ቤታችን ሲመጣም የሚበላ ነገር ልናቀርብለት ይገባል። ለመሆኑ የክርስቶስ መብል ምንድነው? ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ጥያቄ ሲመልስልን እንዲህ ብሏል፦ "የእኔስ መብል የላከኝን ፍቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ ነው።" (ዮሐ.4፡34) +++ እንኪያስ ክርስቶስ የራበው ይኼው ነውና እንመግበው፤ ኢየሱስ የጠማው ይኼው ነውና እናጠጣው። እርሱም ይቀበለናል። እንዲት ኩባያ ቀዝቃዛ ውሃ ብንሰጠው እንኳን ይቀበለናል። ስለብዛቱ ሳይሆን ስለፍቅሩ ብሎ ይቀበለናል። እኛን ስለመውደዱ ይቀበለናል። የምንወደው ሰው የሰጠነውን የሚቀበለን ስለ መጠኑ አይደለም፤ ስጦታው የወዳጅ ስለሆነበት እንጂ። ሰው ወዳጁ ጌታም ሁለት ሳንቲም ብንሰጥ እንኳን ብዙ እንደሰጠን አድርጎ ይቀበለናል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስጦታችንን የሚቀበለው ድሃ ስለሆነ አይደለም። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የድሃውም የባለጸጋውም ስጦታ እኩል የሚቀበለው ስለ ልቡናቸን ኀልዮት (Intention) እንጂ ስለ ስጦታው ትልቅነት ወይም ዋጋ አይደለም። ስለዚህ ክርስቶስን እንደምንወደው ለመግለጽ የግድ የብዙ ወይም በውድ ዋጋ የተገዛን ስጦታ መስጠት አያስፈልገንም። ስጦታችን እርሱ ወደ እኛ ስለመጣ ደስ የመሰኘታችን መግለጫ ነውና ስለ ስጦታችን መጠን ልንመለከት አይገባም። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#ይኼንን_ቪዲዮ_እስካሁን_ካላያችሁና_ካላዳመጣችሁ_በእውነት_ብዙ_ተሸውዳችኋላ!! ወላጆች ልጆቻችሁን በዚህ መንገድ አሳድጉ እንጂ አትጫኗቸው!! #ethiopia https://youtu.be/9Y0Dkyea6HE

+++ የጻድቁ አባታችን አቡነ ሃብተ ማርያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን። እንኳን አደረሳችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያን ቤተሰቦቼ በያላችሁበት የጻድቁ ረድኤትና ምልጃው አይለያችሁ።
+++ የጻድቁ አባታችን አቡነ ሃብተ ማርያም ረድኤት በረከት  በሁላችን ላይ ይደርብን። እንኳን አደረሳችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያን ቤተሰቦቼ በያላችሁበት የጻድቁ ረድኤትና ምልጃው አይለያችሁ።

ቅዱስ አባታችን አቡነ ማትያስ ያስተላለፉት ድንቅ መልእክት፦ "የእግዚአብሔር ቤት በአምልኮተ እግዚአብሔርና በጸሎት ከመራነው ሁሉም ነገር ቀና ይሆናል ዓለማዊ መንገድ ከተደባለቀበት ግን አደገኛ ነው "
ቅዱስ አባታችን አቡነ ማትያስ ያስተላለፉት ድንቅ መልእክት፦ "የእግዚአብሔር ቤት በአምልኮተ እግዚአብሔርና በጸሎት ከመራነው ሁሉም ነገር ቀና ይሆናል ዓለማዊ መንገድ ከተደባለቀበት ግን አደገኛ ነው "ጋሻና ቅል ለየቅሉ ይሰለል።" እንደሚባለው መንፈሳዊነትና ፖለቲካን ለይተን መጎዝ ይኖርብናል።" "ሰላም የሚገኘው ከሰላማዊቷ ቤተክርስቲያን ነው ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተክርስቲያን ያልተገኘ ሰላም ከየት ሊገኝ ይችላል? የተሰጠን ሓላፊነት መንፈሳዊ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባትም ለአገራችን ሰላም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማበርከት በትጋት መሥራት ይኖርብናል።" "ጥላቻ፣ ዘረኝነት፣ ጎጠኝነት አይጠቅምም። እኛ መንፈሳዊያን ነን እግዚአብሔር ሲፈጥረን ንጹሐን አድርጎ ነው የፈጠረን። እኛ በራሳችን መንገድ በመጓዛችን ነው ወርደን ተጠባቂዎች የሆነው።" "ያሉት ቅዱስነታቸው እኛ ጠባቂዎች መሆናችንን አውቀን የጠባቂነት ሚናችንን ከጥላቻና ከዘረኝነት በራቀ መንገድ በመፈጸም ለሰይጣን ሳይሆን ለእግዚአብሔር ተመችተን መገኘት አለብን።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

እስከዛሬ ያልነገርኳችሁ የእኔ ታርክና የህይወት ፈተናዎች!! የአዳልሞቴና የወሰንገላ መናፍስቶች ከባዱ ፈተና! የመምህር ግርማ ትምህርትና ቪዲዮ ሕይወተን ቀይሮታል! https://youtu.be/Y5hByVntIls?si=nnruFHgOp3pnwajK

ይህቺ እህታችን ያደረገችው ነገር ከባድ ቢሆንም ብዙ ያስተምረናል!! በሱባኤ እውነተኛ መልስ እንዴት ይገኛል? #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/UsfvdpiN7wE

ብፁዕ አቡነ አብርሐም የምስጋና ደማቅ አቀባበል በባህር ዳር ከተማ ተደረገላቸው *** የ3 ዓመት የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅነት ታማኝ አገልግሎት አጠናቀው ወደ መንበረ ጽጽሳናቸው የተመለሱት ብ
+2
ብፁዕ አቡነ አብርሐም የምስጋና ደማቅ አቀባበል በባህር ዳር ከተማ ተደረገላቸው *** የ3 ዓመት የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅነት ታማኝ አገልግሎት አጠናቀው ወደ መንበረ ጽጽሳናቸው የተመለሱት ብፁዕ አቡነ አብርሐም ባህር ዳር ከተማ ሲገቡ ማኅበረ ካህናት እና ምዕመናንን ደማቅ አቀባበል አድርገዋል። እናመሰግናለን!!!

#የራሔል_የተራፊም_ጣኦትና_የእኛ_የጬሌ_መናፍስቶች_ጉዳት_በዘመናችን!! የሕይወት ዘመን የተዋሕዶ ምስጥር ዛሬ ተመለሰልኝ!! #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/rXU0wmO2otQ?si=IoujRfibprvVszfV

#ለዘጠኝ_ወራት_ዲዳና_የማይናገር_ሆኖ_የቆየው_ወጣት_መናገር_ጀመረ!! በድፍን ቅል የተመተተ የምስጥር መተትና ሴራው! ኦትዝምና የልጆቻችን የአጋንንት ፈተናዎች! https://youtu.be/Ti-R4u6-brQ

ግንቦት ፳፫ /23/ በዚች ቀን ሐዋርያ ቅዱስ ዮልዮስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ትውልዱ ከይሁዳ ነገድ ከእስራኤል ልጆች ከቤተ ገብርኤል ነው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መረጠው። ከሰባ ሁለ
ግንቦት ፳፫ /23/
በዚች ቀን ሐዋርያ ቅዱስ ዮልዮስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ትውልዱ ከይሁዳ ነገድ ከእስራኤል ልጆች ከቤተ ገብርኤል ነው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መረጠው። ከሰባ ሁለቱ አርድእትም የተቆጠረ ሆነ የመንፈስ ቅዱስንም ሀብት ከሐዋርያት ጋራ ተቀበለ ከእርሳቸውም ጋራ ታላቅ መከራ ደርሶበታል። ከዚህ በኋላ ሐዋርያት በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሹመው ከእንድራኒቆስ ጋራ በአገሮች ውስጥ እንዲሰብክ ላኩት። እንድራኒቆስም በአለፈው ዕለት በአረፈ ጊዜ ይህ ቅዱስ ዮልዮስ ገንዞ ቀበረው ። ከዚህ በኋላ ከርሱ እንዳይለይ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ በማግሥቱ ዛሬ አረፈ። እነሆ የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም እሊህን ሐዋርያት በሮሜ ክታቡ ዕንድራኒቆስንና ዮልዮስን ሰላም በሏቸው ሲል አስታውሷቸዋል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባቶቻችን ሐዋርያት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ይኼንን ጉድ ተመልከቱ!! ስንቱን ያፈዘዙበት ያደነዘዙበት የመናፍስቱ ሴራ ሲገለጥ!! https://youtu.be/CC1Fo0Z8TTQ

#እንዳታገባ_ወንዶችን_የሚያባርር_ገርግር_ዓይነጥላና_መተት_ዕድሜያችንን_በልቶታል!! ልባችንን ከዓለም ማውጣት የሚጠበቅብን ዛሬ አሁን ነው!! #ethiopia https://youtu.be/_hBdHzRweLc