HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 277
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
+2930 días
Archivo de publicaciones
#እንዲህ_እያላችሁ_ስገዱ!
"በአብ ስም አመልካለሁ፣ በወልድ ስም እታመናለሁ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም እባረካለሁ። በጉልበቴ ተንበርክከ እየሰገድኩ።"
(ሰይፈ ስላሴ ጸሎት ቁጥር 66)
🙏 ይሄን ጸሎት በስግደት ቁጥሩን ከ28 ጀምራችሁ መስገድ ነው ቤተሰቦቼ። በርቱ 🙏🙏
◈ የጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን፣ ቃልኪዳናቸው፦ ከስጋ በሽታ (ከቸነፈር፣ ከወረርሽኝ)፣ ከነፍስ ቁስል (ከኃጢአት) ይሰውረን። 🙏🙏🙏 ሀገራችን ኢትዮጵያን ከክፉ ይሰውሩልን 🇪🇹
👇👇👇👇
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑እየጸለይን፣ እየሰገድን፣ እየጾመን ለምን መናፍስት አልያዝ አሉን https://youtu.be/dMWV4z60maU?si=bT5P89fLjXodraoJ
🛑የሕይወት ለውጥ በመንፈሳዊ ሕይወት ወቅት https://youtu.be/JFKeC0djGLQ?si=fSFRTQOeq4bU4SDC
+ ራስህን ነጻ ማውጣት ትፈልጋለህ? +
◈ በውጭው ካሉት ይልቅ በአንተ ውስጥ የሚገኙት ፍትወታት ጠንካራ ጠላቶችህ ናቸው። ልክ ያልተሠራለት ምኞት ከባቢሎን እሳት ይልቅ ያቃጥላል። አልጠግብ ባይነትም ከጥፉት ውኃ ይልቅ ያሰጥማል። ያልተገራ ፍላጎት ማንነትን አስጥሎ የሰይጣን ባሪያ ያደርጋል። ራስን መግዛት የሰው ልጆች ጌጥ ነው። ዮሴፍ ግብጽን ከፈርዖን ሁለተኛ ሆኖ ከገዛበት ታላቅ ሥልጣን ይልቅ፣ በጌታው ሚስት ፊት ያሳየው ራስን መግዛት ይበልጥ ይደነቃል። ጠቢቡ "በመንፈሱ ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስዱ (ከሚገዙ) ይበልጣል" እንዳለ። (ምሳ 16፥32)
◈ ራስህን ነጻ ማውጣት ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ ከውስጥህ ጀምር። ሁል ጊዜ ካልበላሁ የሚለው ሆድህ ስስት አስለምዶ በወንድምህ ላይ ጨካኝ እንዳያደርግህ ለሰውነትህ ጾም አስተምረው። "ነገ እሞታለሁና ልብላ ልጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍናህን (Pig philosophy) ተውና አንተ በፈቃድህ እየተራብህ (እየጾምህ) ያለ ፈቃዱ የተራበው ወንድምህን በምጽዋት አጥግበው።
◈ ጌታ ወደ እስራኤል የተመለሰው ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ነበር። (ማቴ 2፥20) አንተ ውስጥ ያለውን ሄሮድስ የተባለ ክፉ ምኞት እንዲሞት ካላደረግኸው በቀር የተሰደደው ክርስቶስ ወደ አንተ ሊመለስ አይችልም። ይህ ክርስቶስን ከልብህ የሚያሳድድብህን ሄሮድስ እንዴት ልትገድለው ትችላለህ? እርሱንስ ወግተህ የምትጥልበት የብረት ካስማ ምን ይሆን? ለዚህስ ከጾም እና ከጸሎት የሚበረታ ምንም ዓይነት የጦር ዕቃ አታገኝም። በል እነዚህን ይዘህ ዝመትበት።
በዲያቆን አቤል ካሳሁን
👇👇👇👇
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🙏🙏🙏🙏
ከንፈር ለከንፈር መሳሳም ኃጢአት ነውን?
ሩካቤ ሥጋ እና የጸሎት ሕይወት https://youtu.be/WhXjes1JOgM?si=DnhQx08gacnjh6k_
🙏🙏🙏
"የአንድ ሀገር ሕመም የሚጀምረው ከልጅነት ነው"
https://youtu.be/PAdH8Il4qx8?si=ZatawCz2_WQOhB6d
◈ በስብእና ከተማ ከተነቀፉ ክፋቶች የተከወኑ ደግነቶች ሚዛን ይደፋሉ፡፡ ከተሰደቡ ጥፋቶች የተፈፀሙ ልማቶች ይጠቅማሉ፡፡ እንኪያስ ለእጃችን ከመጠቆም የተሻለን መደገፍ ብናሰልጥነው፡፡ የኔ ትንሽ ሥራ ምን ይለውጣል ለምን እንላለን?...የሻማ አንዳንዶች የዓለምን ጥቁረት እንደሚያበሩ እንወቅ (ለዚህም ምስክሩ ፲፪ቱ ብፁዓን ናቸው)፤ ያወቅነውንም በማውረድ አንድ መስኮት እንክፈት፡፡ ያኔ..... የ፵ዓመቱ ቀጠሮ በ፵ኛ ቀኑ ይደርስ ይሆናል፡፡
🙏 ቤተሰቦቼ የበረከት ሥራው ቀጥሏል ሁለችሁም በአቅማችሁ ለማገዝ የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ። እንተጋገዝ! የበረከት እና የሰላም መንገድ ይሄ ነውና!! ያዘኑ ነብሶችን የአንድ ቀን ድካማቸውን እንጋራ በእውነት። የሰዎችን ሀዘን እንጋራ። ብርሃን እንሁንላቸው።
Telegram፡ https://t.me/haile_gebriel_tube_bot
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
◈ በቀን መጨረሻ ዝና፣ ውበት፣ ሥልጣን፣ ሐብት ትርጉም የላቸውም፡፡ የኑሮአችን የመገባደጃ ትውስታ ፍቅር ናት፡፡ በልጽገን ለብቻችን ከበላነው ቡፌ ይልቅ በድህነት በአንድ ሳህን የቆረጠምናት ቆሎ ሆድ ትወጥራለች፡፡ ግዴለም ሰውን እናፍቅር! ሁሉ ሰውን እናፍቅርና ሙሉ ሰውን እንሁን፡፡ መጽሐፉም እንዳለ፦ የጐመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል።" (ምሳ. 15፡17)
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑 እጸልያለሁ፣ እሰግዳለሁ ነገር ግን መዳን እና መፈወስ አልቻልኩም ምን ላድርግ። https://youtu.be/UBAiTU-stEo?si=plfndrinSP_KAiK1
◈ በስካር የሚፈጸም ሩካቤ ሥጋ ችግሩና መርገሙ /ከሩካቤ ሥጋ በፊት ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡ ነገሮች/
ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ
፩.መጠጥ/ስካር
◈ ተወዳጆች ሆይ እንኳን ሰክረን ሩካቤ ሥጋ ልንፈጽም ስካር ለብቻው ኀጢአትና የኀጢአት መንገድ ነው፡፡ ዛሬ ሰክረው በስካር መንፈስ በመርከስ የሠሩት ስሕተት የእድሜ ልክ ጸጸት የሆነባቸው ብዙዎች ናቸው፡፡ በስካር መንፈስ በመክነፍ ክብራቸውን ያጡ፣ ከትዳራቸው ያፈነገጡ፣ ፈጣሪን በክፉ ድርጊታቸው ያስቆጡ ብዙ ናቸው፡፡ መጠጥን በራሳቸውና በጓደኛቸው ግፊት ጀምረው በሕይወታቸው የማይድን ቁስል ተሸክመው ሕይወታቸውን አጥተው የሚኖሩ ቁጥራቸው ብዙ ነው፡፡
◈ ባለትዳሮች የትዳራቸው መሠረት እንዳይናወጥ ቡራኬያቸው ወደ መርገም እንዳይለወጥ ከፈለጉ ከመጠጥ መራቅ አለባቸው፡፡ በተለይ በተለይ ሩካቤ ሊፈጽሙ ባሰቡበት ጊዜ ከምንም ዓይነት መጠጥ መታቀብ አለባቸው፡፡ እንደው መጠጡ ልምድ ቢሆንባቸው እንኳን ሰክሮ ሩካቤን መፈጸም የለባቸውም፡፡ ለምሳሌ በማዳበርያ የተዘራ ስንዴና ያለ ማዳበርያ የተዘራ ስንዴ ከምርት ብዛት ሳይሆን ከጤንነት አንጻር ጥቅማቸው እኩል አይደለም፡፡ በማዳበርያ ታግዞ የተዘራ ስንዴ የተፈጥሮ ስላልሆነ የጐንዮሽ ጉዳት አለው፡፡ ይህም በማዳበርያ ውስጥ ያለው ምርት የሚያበዛው ጐጂ ንጥረ ነገር ለጤና ጠንቅ ከመሆኑም ባሻገር እንደ ካንሰር ያሉት በሽታዎች በሰውነታችን ውስጥ እንዲፈጠሩ ሚናቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ምክንያቱም በመሬቱ ውስጥ ያለው ማዳበርያ ከእህሉ ጋር በመዋሃድ አድጐ ስንመገበው የማዳበርያው ጐጂ ንጥረ ነገር በእህሉ አማካኝነት ወደ ሰውነታቸው ውስጥ ይገባል፡፡ የዚህ ጐጂ ንጥረ ነገር ጥርቅም ጤናን በማቃወስ የማይፈወስ በሽታን ሊያመጣ ይችላል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ ጠጥተን/ሰክረን ሩካቤ ሥጋ ስንፈጽም በመጠጡ ውስጥ ያለው ከፍተኛ የአልኮል ንጥረ ነገር ከዘራችን ጋር በመዋሐድ ወደ ሴቷ ማሕፀን በመግባት ከፅንስ ይቀላቀላል፡፡
◈ አስቡት ይህ ፅንስ የአልኮል ጐጂ ንጥረ ነገር /ኬሚካል/ ስለተዋሐደው ለፅንሱ ትልቅ ጠንቅ ይሆናል፡፡ የእርግማን ትውልድን የምናመጣው አንዱም በስካር ሩካቤ ነው፡፡ ውስኪና የውስኪ ዘሮችን ብንመለከት የአልኮል መጠናቸው 40% ነው፡፡ ታዲያ በስካር ተፀንሶ የሚወለደው ልጅ በባሕርይው አስቸጋሪ፣ የማይታዘዝ፣ ሥርዐት አልበኛ የሆነ፣ ወጣ ፈንገጥ ያለ ጠባይ ያለው ይሆናል፡፡ የቅርብ ጊዜ ጥናቶችም እንደሚያመለክቱት በመጠጥ ስካር ተፀንሰው የሚወለዱት ልጆች ወደ ፊት ሰካራም የመሆን ዕድላቸው እጅግ በጣም ሰፊ እንደሚሆን ይጠቁማል፡፡ በፅንስ ጊዜ የሰከረ ተወልዶ አድጎ ሰካራም ቢሆን አይደንቅም፡፡
◈ ይሁዳን ብንመለከት ጌታችንን በሠላሳ ብር እንደሚሸጠው ለሞት አሳልፎ እንደሚሰጠው ትንቢት ቢነገርበትም ይሁዳ የተወለደበትን የፅንስ ሂደት ብንመለከት በስካር ነው። በስካር የተወለደ ጌታችንን ያስገደለ ይሁዳ ፅንሰቱ በስካር መርገምን የተመላ ነበር። ዛሬም ልጆቻችን በስካር መንፈስ እየተጸነሱ በኃጢአት እየተልከሰከሱ ጌታን የሚክዱ የሚሆኑት በእኛው ጥፋት ነው።
◈ ሌላው በመጠጥ ስካር በምንፈጽመው ሩካቤ መቼም ፅንሱ የእግዚአብሔር ሳይሆን የሰይጣን የክፋት ቡራኬ ስለሚደርሰው የፈጣሪ ሳይሆን ወደ ፊት የሰይጣን ጉዳይ አስፈጻሚ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ሌላው ሰክሮ ሩካቤ ሥጋን መፈጸም የሚያመጣውና የሚያስለምደው ብዙ ነገር አለ፡፡ አንደኛው ልቅ የሆነ ሩካቤ ሥጋን አንድንፈጽም ያደርገናል፡፡ ይህ ደግሞ ሥርዐት አልባ ሩካቤ ሥጋን በማስከተል ከፈጣሪ ያጣላል፡፡ ስለዚህ ሩካቤ ሥጋ የምንፈጽም ቀን በተቻለን መጠን የትኛውንም አልኮል ነክ መጠጥ ባንጠጣ ይመረጣል፡፡
፪. ጫትና አደንዛዥ ዕጾች ወዘተ
◈ እነዚህ ባዕድ ነገሮች ሰውነታችን ውስጥ ሲገቡ ውስጣቸው ያለው ንጥረ ነገር ለጊዜው የሚያስደስት ቢሆንም በፅንሱ ላይ ይዞት የሚመጣው ተያያዥ ጉዳት ከፍተኛ ነው፡፡ ጫትና አደንዛዥ ዕፆች በተለይ የሚወለደው ልጅ ላይ ከፍተኛ የሆነ የአእምሮና የባሕርይ ችግር ያስከትላሉ፡፡ ያልተባረከ ዘር የሚባለውም እንደዚህ ያለው ነው፡፡ በሩካቤያችን ለልጆች ቡራኬን ሳይሆን መአትና እርግማንን የምናወርሰው እኛው ነን፡፡ እኛ ሳንባረክ የተባረከ ትውልድ መፈለጋችን ምናልባትም በራሳችን ላይ ማፌዝና የማይገባንን ነገር መጠበቅ ነው፡፡ ይህም እንክርዳድ ዘርቶ ስንዴን ለማጨድ እንደመጠበቅ ነውና ከእነዚህ ነገሮች ልንጠበቅ እና ልንላቀቅ ይገባል፡፡
፫.ውኃ
◈ ይሄ ከጥንት ጀምሮ መንፈሳውያን አባቶቻችን ሲጠቀሙበት የነበረው የተፈጥሮ ዘዴ ነው፡፡ ባል እና ሚስት ሩካቤ ሥጋ ከመፈጸማቸው በፊት አስቀድመው ምግብ ተመግበው ንጹሕ ውኃ ቢጠጡ መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም ንጹሕ ዘራቸው በተለያየ የምግብ እና የመጠጥ ንጥረ ነገሮች እንዳይበላሽ፣ እንዳይበከል ነው፡፡ የዚህ ጥቅሙ የጠጣነው ውኃ ከሰውነታችን በመዋሐድ በሰውነታችን ያለው ዘር ንጹሕ እንዲሆን ይረዳዋል፡፡ ይህንን አድርገን ሩካቤ ሥጋ ብንፈጽም የሚወለዱት ልጆችም በሽተኛ፣ አቅመ ደካማ፣ ንቃተ ኅሊና የሌላቸው አይሆኑም፡፡ ይህም የሚሆነው ሩካቤ ሥጋ ከመፈጸማቸው ቢያንስ ከሠላሳ ደቂቃ በፊት ቢሆን ይመረጣል፡፡
‹‹ትዳርና ሕገ ሩካቤ ችግሩ እና መፍትሔው›› ከሚለው በቅርቡ ከታተመው መጽሐፌ የተወሰደ!
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
◈ ትሕትና ምንድር ነው?
◈ ትሕትና ምንድር ነው? ብዙ ጊዜ በእኛ ዘንድ የተናቀ ልብስ መልበስ፣ አንገት መስበር፣ ዝግ ብሎ ማውራት እና ‹እኔ በደለኛ የማይገባ ሰው ነኝ› እያሉ ደጋግሞ መናገር እንደ ትሑት ያስቆጥር ይሆናል፡፡ ነገር ግን የትሕትና ትርጉም ከዚህም በላይ ነው፡፡ በርግጥ ከላይ የዘረዘርናቸው ነገሮች የአንድ ትሑት ሰው ከፊል መገለጫ ጠባያት ተደርገው ሊወሰዱ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህን በማድረግ ብቻ ትሑት መሆን ቢቻል ኖሮ፤ በዓለም ላይ ያለው የትዕቢተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንስ ይመስለኛል፡፡ ስለዚህ ትሕትናን በተጠቀሱት ውጫዊ ምግባራት ብቻ የምንረዳው ከሆነ ከእውነተኛ ትርጉሙና ማንነቱ እንዳናሳንሰው ስጋት አለኝ፡፡
◈ ትሕትና በእኛ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለ እውነተኛ ኑሮ ነው፡፡ አንድ ክርስቲያን ስለ ትሕትና ሲያስብ እነዚህን ሁለት ነገሮች አብሮ በትኩረት ሊያሰላስል ይገባዋል፡፡ እነርሱም አንደኛ ተፈጥሮውን (መሬታዊ፣ ትቢያ መሆኑን) አለመዘንጋት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ተቀባይነቱን ለዘወትር ማስታወስ ነው፡፡ ሰው በጫማው እየረገጠ የሚራመደው አፈር እንደሆነ ሲያስብ ደካማነቱን ይረዳል፡፡ ስለዚህም በነገሮች ሁሉ ‹አቤቱ እኛ አፈር እንደ ሆንን አስብ› እያለ ረድዔተ እግዚአብሔርን የሚማጸን ትሑት ይሆናል፡፡ (መዝ 103፡14) ተቀባይነቱንም ሁል ጊዜ የሚያስታውስ ከሆነ ለሌሎች በሚያደርጋቸው በጎ ሥራዎች አይኩራራም፡፡ ብልጫም አይሰማውም፡፡ ምክንያቱም የራሱን ሳይሆን ከአምላኩ ከተሰጠው ላይ ቀንሶ የሚያካፍል ምስኪን ምጽዋተኛ ስለሆነ፡፡ ሐዋርያውስ ቢሆን በቆሮንቶስ መልእክቱ በታላቅ ቃል ‹አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጎሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለምንድር ነው?› ሲል የሚገስጸው ስለዚሁ አይደለምን? (1ኛቆሮ 4፡7)፡፡
◈ ሶርያዊው አባት ማር ይስሐቅ ስለ ትሕትና ትርጉም አንድ ቁም ነገር ያካፍለናል፡፡ ምን አለ? ‹ውድቀትና ኃጢአቱን እያነሣ ራሱን የሚወቅስና የሚያዋርድ ጥሩ ቢያደርግም ትሑት ተብሎ ግን አይጠራም፡፡ ትሑት ሰው ራሱን ማሳመንና ኅሊናውም ይህን ሐሳብ እንዲይዝ መጫን አይጠበቅበትም፡፡ እንዲሁ ራሱን ምንም አድርጎ ይቆጥራል እንጂ› ሲል አስተማረ፡፡ እንደ ማር ይስሐቅ ትምህርት ከሆነ ትሑት ለመሆን ሲባል ራስን ማስጨነቅ ወደ ትሕትና ጫፍ ለመድረስ ሯጭ(ተጋዳይ) መሆንን የሚያሳይ እንጂ ‹ትሑት› አያሰኝም፡፡ እውነተኞቹ ትሑታን ሌላ የሚጋፋ እና ትግል የሚጠይቅ አንዳች የበላይነት (የእኔነት) ስሜት ሳይሰማቸው እንዲሁ ራሳቸውን የሰው ሁሉ መጨረሻ አድርገው የሚቆጥሩ ናቸው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ባሕታዊም ‹ትሑት ሰው የሚባለው ራሱን የሚሰድብና የሚያዋርድ ሳይሆን፤ ከሌሎች ሰዎች በሚደርስበት ስድብና ትችት ፊት ፍቅሩ ሳይቀንስበት መቆም የሚችል ሰው ነው› በማለት ያስተማረው ይህን የፍጹማኑን ትሕትና ለማሳየት ነው፡፡
◈ አባ መቃርዮስ እንደተናገረ የትሕትና ተቃራኒ የሆነች ትዕቢት የኃጢአቶች ሁሉ ራስ (እናት) ናት፡፡ ታዲያ ትዕቢት ለኃጢአቶች ሁሉ እናት ከሆነች ትሕትና ለጽድቅ ሥራዎች ሁሉ ራስ ብትሆን ምን የሚያስደንቅ ነገር አለ?!፡፡ ለዚህም ነው እኮ ቅዱሳን አበው ትሕትናን ‹እጸ ሕይወት›/‹የሕይወት ዛፍ› እያሉ የሚጠሯት፡፡ አዳም በገነት አንድ ሺ ዓመት ከኖረ በኋላ ወደማታልፈው መንግሥት (መንግሥተ ሰማያት) ለመግባት የሚታደስባትን እጸ ሕይወት አምላኩ በገነት ዛፎች መካከል ፈጥሮለት ነበር፡፡ እርሱም ትእዛዘ እግዚአብሔርን ጠብቆ ሺ ዘመን ቢቆይ ኖሮ፤ ላይወድቅ ላይጎሰቁል በእጸ ሕይወት ታድሶ መንግሥተ እግዚአብሔርን ይወርስ ነበር፡፡ ከእጸ ሕይወት በኋላ መውደቅ የለምና፡፡ እንዲሁ ትሕትናም እጸ ሕይወት ነች፡፡ ትሕትናን ገንዘብ ካደረጉ በኋላ ውድቀት እና ከእግዚአብሔር መለየት የለም፡፡
◈ ትሕትና በጎ ሥራዎች ሁሉ የሚጠበቁባት አጥር ቅጥር ነች፡፡ ከእግዚአብሔር የምናገኛቸው ጸጋዎችም ያለ ትሕትና ሊጸኑ፣ ሊሰነብቱ አይችሉም፡፡ ቅዱሳን በጽኑዕ ተጋድሎ እና በፈጣሪ ቸርነት የገነቡትን የጸጋ ግንብ ሰይጣን እንዳያፈርስባቸው ፈጣሪያቸው የሚከላከልላቸው ትሑታን የሚሆኑበትን ደዌ ወይም አንዳች ነገር በእነርሱ ላይ በማምጣት ነው፡፡ ባለ ብዙ ጸጋ የነበረው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን የእግዚአብሔር አሠራር ሲያስረዳን ‹በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ…ተሰጠኝ ይኸውም እንዳልታበይ ነው› በማለት ግልጽ አድርጎ ይናገራል፡፡ (2ኛ ቆሮ 12፡7) በሰውነቱ ጥላ እና በልብሱ እራፊ ሙት የሚቀሰቅሰው፣ ሕሙም የሚፈውሰው ሐዋርያ እንደ ስንጥር በሚወጋ ራስ ምታት መያዙ፤ ተአምር ሲያደርግ በተመለከቱት ሰዎች በስህተት እንዳይመለክና ልብን ሰቅዞ በሚይዝ አጉል ውዳሴ እንዳይጠለፍ አድርጎታል፡፡ በርግጥም የገባሬ ተአምራት የቅዱስ ጳውሎስን ሕመም ያዩ ሰዎች በእርሱ ድካም ውስጥ የሚሠራ የእግዚአብሔርን ኃይል በግልጽ ተረድተዋል፡፡
◈ እግዚአብሔር በጎውን ዋጋ የሚሰጠን መልካም ስላደረግን ይመስላችኋል? አይደለም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ መልካም የሚያደርጉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች ከእግዚአብሔር በጎውን ዋጋ ላይቀበሉ ይችላሉ፡፡ ለምን? ከአምላክ ዘንድ በጎ ዋጋ የሚያሰጠው መልካም ማድረግ ሳይሆን፤ መልካሙን ነገር በትሕትና ማድረግ በመሆኑ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክም ከተነሡ ውዝግቦች (ክህደቶች) መካከል አንዱ የሆነው የ‹Pelagius controversy› ለዚህ ጉዳይ ተጠቃሽ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህም የአየርላንድ መነኩሴ በሆነ ፔላጊዮስ የተጠነሰሰ ሲሆን፤ አጠቃላይ ምልከታውም ‹ሰው ብቻውን በሚያደርገው በጎ ሥራ ይድናል› የሚል በረድዔተ እግዚአብሔር መደገፍንና ትሕትናን አውልቆ የሚጥል የክህደት ትምህርት ነበር፡፡ በእውነትም የማታልፍ የማትለወጥ የእግዚአብሔርን ርስት፣ ፈራሽ በስባሽ በሆነው ሰውነቴ ብቻ ሠርቼ ገንዘብ አደርጋለሁ ከማለት በላይ ተሻለ ክህደት ከወዴት ሊመጣ ይችላል?
◈ እስኪ ጽሑፋችንን በቅዱስ መቃርስ ምሳሌ እንዝጋው፡፡ አባ መቃሪ በአንድ ወቅት ስለ ትሕትና ሲያስተምር ‹አንድ ባለጠጋ የነበረ ንጉሥ ያለውን ሀብት በአደራ መልክ ከአንድ ደሃ ዘንድ ቢያኖር፤ ያ ደሃ በእነዚያ ብሮች እና ወርቆች ሊመካ ይችላልን? እንደ ራሱ ንብረትስ በመቁጠር የባለቤትነት ስሜት ሊሰማው ይገባል?› ሲል ይጠይቃል፡፡ በዚህ ቅዱስ አባት ምሳሌ መሠረት ያ ባለጠጋ ንጉሥ እግዚአብሔር ነው፡፡ አደራ ተቀባዩ ነዳይ ደግሞ እኛ ነን፡፡ አደራውም በእጃችን ያሉ በጎ ነገሮች ሁሉ ናቸው፡፡ ያሉንን መልካም ነገሮች እንደ ራስ ንብረት መቁጠርና በሌላው ላይ መኩራራት አደራ ተቀባይነትን እንደ መርሳት ነው፡፡ ሰው ባልፈጠረው በጎነት እንዴት ይኩራራል?
በትሑታኑ ቅዱሳን ጸሎት ይጠብቀን!
በዲያቆን አቤል ካሳሁን
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
