es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 398 suscriptores, ocupando la posición 5 565 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 183 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 398 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 18, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.46%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.24% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 305 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 576 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 17.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 398
Suscriptores
+224 horas
+327 días
+1830 días
Archivo de publicaciones
‹‹ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡ ›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት ጥር 1 ፤ 7 እና 21 ሥርዓተ ፤ ፤ 2014 ዓ.ም በቀ.ደ.ሰላም መድኃኔዓለም ወደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ ጋብቻቹሁን የፈጸማችሁት የሰ.ት.ቤት ወንድምና እኅቶቻችን ፤ #አበራ ማሙዬ ከ ሰርካለም ደረጄ፤ #ሰሎሞን አጥሌ ከ እሥራኤል አስማማው ፣ #ቡሩክ አባቢ ከ እታበዛው ጉልች፤ የፈጸማቹሁትን ጋብቻ መድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ ያድርግላችሁ ፡፡ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ ÷ ያጣምራችሁ ÷ ያዋህዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኃላ ይከተላቹ፡፡ †<<ከተጋባቸሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ቅዱስ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ፡፡ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም እና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት

#ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ_በሥዕሉ_ላይ_አድሮ_ቅዱሳን_የሆኑ_ባስልዮስንና_ጎርጎርዮስን_በመርዳት_ከሃዲውን_ንጉሥ_ዑልያኖስን_የገደለበት_ዕለት_ነው፡፡ #ራሱን_የሸጠው_ቅዱስ_ጴጥሮስ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ #ከበሬ_ጋር_ተጠምደው_በማረስ_ሰማዕትነትን_የተቀበሉት_አቡነ_ሕፃን_ሞዐ_ልደታቸው_ነው፡፡ **ዳግመኛም በዚህ ዕለት፤ #ስብስትያኖስ_ሰባስትያኖስ_ሰማዕት_ጥር_25 ፠ በሕመም፥ በጭንቅ፥ በመከራ፥ በስቃይ፥ #በደዌ_ዳኛ፥ #በአልጋ_ቁራኛ_ላይ_ያላችሁ_ሁሉ በእምነት የሰማዕቱ የቅዱስ ስብስትያኖስን ስሙን ጥሩት፥ ገድሉን አድምጡ ተሻሹ፥ እምነቱን ተቀቡ፥ ቤተ ክርስቲያኑን ተሳለሙ #ፈዋሽ_ሰማዕት_ነው፡፡ #ፈትለ_ሥላሴ በመባል በሚጠራው ቤ.ክ. (ከአዲስ አበባ በሞጣ/በደብረ ድማኅ/ በኩል ወደ ባሕር ዳር ሲሄዱ አዴት ከተማ ከመድረስዎ በፊት ዠማ ወንዝ ለመድረስ ሲቃረቡ ያገኙታል)፡፡ ጥር 25 ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ይከበራል፡፡ እንዲሁም በጥንታውያን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት የብራና ገድሉ ስላለ አስነብቡ፥ ተሻሹ፤ ፍጹም ፈውስን ታገኛላችሁ፡፡ ፠ ሰባ(ስብ)ስትያኖስ ሰማዕት፤ በስዕሉ ላይ እንደምንመለከተው በጽኑ ሕማምና ስቃይ ሰማዕትነትን የተቀበለ ነው፡፡ በተለይም በሕመም፤ በጭንቅ መከራ፤ በስቃይ ውስጥ ኾኖ ያለ ሰው አምላከ ሰብስትያኖስ ብሎ ለጠራኝ እደርስለታለሁ ብሎ በማይታበል ቃሉ እግዚአብሔር አምላካችን ቃል ኪዳን የሰጠው ሰማዕት ሲኾን ለጠሩትም ፈጥኖ የሚደርስ ሰማዕት ነው፡፡ ፠ የስብስትያኖስ አባቱ የሮሙ ንጉሥ ሲሆን ሃይማኖቱ የቀናና እግዚአብሔርንም የሚወድ ስለነበር ልጁን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማረ ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማረ አሳደገው፡፡ አባቱም ከሞተ በኋላ ከሃዲያኑ ዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ ነገሡ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስንም አገረ ገዥ አድርገው ሾሙትና እንደ አባቱ እጅግ አድርገው አከበሩት፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ በጥበብና በማስተዋል የሚጓዝ ነው፡፡ በተጋድሎ ሕይወቱ የተመሰገነ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ የተለያዩ ተአምራትን ገለጠ፡፡ ድውያንን ይፈውሳል፤ በጸሎቱም የዕውራንን ዐይኖች ያበራል፡፡ በእንዲህም ዓይነት በተጋደሎ ሲኖር ዲዮቅልጥያኖስ እግዚአብሔርን ክዶ በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖችን እያሳረደ አብያተ ክርስቲያናትንም ማቃጠል ጀመረ፡፡ ይኸውም ከሃዲ አገረ ገዥ አድርጎ ሾሞትና በእጅጉ አክብሮት የነበረውን ቅዱስ ስብስትያኖስን አሁን ለጣዖት እንዲሰግድ ግድ አለው፡፡ ፠ ቅዱስ ስብስትያኖስ ግን የከሃዲውን ንጉሥ ትእዛዝ ቸል በማለት በፊቱ ቆሞ የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፤ ጣዖታቶቹንም ረገመበት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ቅዱስ ስብስትያኖስን ብዙ አሠቃየው፡፡ ከግንድ ጋር አሥሮ በብዙ ፍላጻዎች(ቀስቶች) ሰውነቱን አስነደፈው፤ በዚህም ጊዜ እንደሞተ አስበው ትተውት ሄዱ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን ለመውሰድ በሌሊት ቢመጡ በሕይወት አገኙትና ወስደው በደሴት መካከል አስቀመጡት፡፡ ፠ ዲዮቅልጥያኖስም የቅዱስ ስብስትያኖስን በሕይወት መኖር ሲሰማ ድጋሚ አስመጣውና በብረት ዘንጎች ሲያስደበድበው ዋለ፡፡ ለብዙ ቀናትም እንዲሁ በብረት ዘንግ ሲያስደበድበው ቆየ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም በጥር 25 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ተለየችና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ጌታችንም መታሰቢያውን ለሚያደርግና ስሙን ለሚጠራ የቸነፈር ሕመም፥ የሕመም ስቃይና መከራ እንዳይቀርበው ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም ካረፈ በኋላ ውሉዱስና ለምትባል ለአንዲት ቅድስት ሴት ተገለጠላትና ቅዱስ ሥጋው ያለበትን ነገራት፡፡ እርሷም ወደ ከበሩ ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ መቃብር ወስዳ ቀበረችው፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Telegram... https://t.me/medihanaelem www.finotehiwotsundayschool.com .Facebook... https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w http://tiktok.com/@finotehiwot #ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts

#ዜና_እረፍት የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው እህታችን ርግበ ገ/ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች ። ሥርዓተ ቀብርዋም በዛሬው እለት ጥር 21 ከቀኑ 6 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን
+1
#ዜና_እረፍት የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው እህታችን ርግበ ገ/ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች ። ሥርዓተ ቀብርዋም በዛሬው እለት ጥር 21 ከቀኑ 6 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በእህታችን ሥርዓተ ቀብር ላይ አጠቃላይ የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በሰዓቱ በመገኘት እህታችንን እንድንሰናበታት ይሁን። የእህታችንን ርግበ ዳዊት ነፍስ ይማርልን።

ገብርኤል ሆይ ! ለሚጠሩት ፈጽሞ ለሚራራ ርኅሩኅ እሣታዊ ነበልባል አንጀትህ ሰላም እላለሁ ፡፡ ገብርኤል ሆይ ! አንተ በሁሉ ዘንድ አሸናፊ ነህ፡፡ አንተ በእግዚአብሔር ዘንድ መሥዋዕትን የሚያሰረጉ የ
ገብርኤል ሆይ ! ለሚጠሩት ፈጽሞ ለሚራራ ርኅሩኅ እሣታዊ ነበልባል አንጀትህ ሰላም እላለሁ ፡፡ ገብርኤል ሆይ ! አንተ በሁሉ ዘንድ አሸናፊ ነህ፡፡ አንተ በእግዚአብሔር ዘንድ መሥዋዕትን የሚያሰረጉ የካህናት ሰማይ ሱራፌል ጓደኛ ነህ፡ ምናልባት ሚካኤል ቢተካከልህ እንጂ እንዳንተ ማን አለ፡፡ #orthodox_quotes

እንኳን አደረሳቹሁ #ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕረፍታ_ለማርያም_(ለሶልያና ) #እመቤታችን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያረፈችበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብረ_በዓል_ነው፡፡ #ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራ፤ #ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷት፤ #ሳታውቀው_አለፈች_ያንን_መራራ_ሞት፡፡ ፠ ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት በኋላ፤ ቅድስት ነፍሷን ከክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና አባቷ ወደተቀበሩበት ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲወስዷት አይሁድ አይተው፤ ልጇ ተነሳ፥ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች፥ አረገች እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባቸው/ ብለው ተነሱ፤ ለዚሁም ከመካከላቸውም ታውፊኒያ የተባለውን የጎበዝ አለቃ መረጡ፤ እርሱም የአልጋዋን ሸንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደነበረው አድርግለት ብላ አዘዘችው፤ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ከዚህ በኋላ ጌታችን ከመካከላቸው ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ ….. ሐዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር በኋላ በነሐሴ 14 ነው ----›እርሱን እዚህ ያንብቡ ----›https://t.me/medihanaelem/6840፤ ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር እንዲሉ፡፡››ረፍታ ለሶልያና(ለማርያም) ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ፡፡ #ሶልያና_የእመቤታችን_የማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡ *የእመቤታችንን ዕረፍት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ‹‹ሞትሰ ለመዊት ይደሉ፥ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ የተገባ ነው፥ የማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጽፏል፡፡ *እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ የላይ ቤት (የግምጃ ቤት ማርያም) አብነትና የታች ቤት(የበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላችኋል፡፡ መልካም ክብረ በዓል፡፡ **ክብረ በዓሉ በሃገራችንና በዓለማችን ክፍሎች ባሉ የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት የሚከብሩ ቢሆንም ግን፤ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓል፤ ከዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብረ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መከበሩን ልብ ይሏል:: /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts #Our_mother_Virgin_mary #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw...

፫. መሎጥ አምባ ጊዮርጊስ (አንድ መግቢያ እና መውጫ ያለው፤ ዐፄ ይኵኖ አምላክ ከመንገሡ በፊት በአያቱ መሐሪዉ አምላክ በግዞት የታሰረበት፤) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ዋድላ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ዋድላ፡፡ ፬. ደብረ ድማኅ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ድማኅ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር መንገድ (በሞጣ መስመር) → ደብረ ድማኅ፡፡ ፭. ሞጣ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ሞጣ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር መንገድ (በሞጣ መስመር) → ሞጣ፡፡ ፮. መሐል ዘጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም (ባህር ዳር) ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፯. ባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም (ባሕር ዳር) ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፰. ዋሻ ነጎድጓድ ጊዮርጊስ ገዳም፤ (በ16ኛው ክ/ዘመን በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመን የተመሠረተ፤ ፈዋሽ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ላሎ ምድር፤ (ከአ.አ. 293 ኪ.ሜ.) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ ላሎ → ወገሬ ከተማ → ዝንዝ (ጦጥ) (ዘብር)፡፡ ፱. ጎንደር እልፍኝ ጊዮርጊስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፤ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት፡፡ ፲. ጎንደር ቀዳሜ አድባራት አበራ ጊዮርጊስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ) (በጎንደር ከተማ ታቦቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርዶ የሚከበርበት) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፥ ኮሌጅ፡፡ ፲፩. ደሴ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ፡፡ ፲፪. ወራኢሉ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወራኢሉ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወራኢሉ፡፡ ፲፫. ግሸን ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል ወረዳ፥ ግሸን፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡ ፲፬. ጋሞ ጎፋ ካምባ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት፥ ካምቦ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ጋሞ ጎፋ (አርባ ምንጭ) → ካምቦ፡፡ ፲፭. ቆላድባ ኳሬና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደምቢያ ወረዳ (ማሩ ቀመስ)፥ ቆላ ድባ ከተማ ፤ (ከጎንደር ከተማ 35 ኪ.ሜ.) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር አዘዞ አውቶቡስ ተራ → ቆላድባ፡፡ ፲፮. ደብረ ታቦር ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡ ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር → ወረታ → ደብረ ታቦር፡፡ ፲፯. አገው ምድር ሳሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ አዊ ዞን ሃገረ ስብከት፥ አገው ምድር (አዊ) (ምዕራብ ጎጃም) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አዊ (በቡሬ፥ ባሕር ዳር መስመር)፡፡ ፲፰. ድሬደዋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ድሬደዋ ሃገረ ስብከት፥ ድሬደዋ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ድሬደዋ፡፡ ፲፱. ደብረ ሲና ጉርጅ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ሲያ ደብር፥ ዋዩ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ሆለታ/ኢንጪኒ/፡፡ ፳. ኢንጭኒ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ኢንጪኒ፤ (ከአ.አ. በሆለታ 65 ኪ.ሜ.) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ደነባ → ሲያ ደብር → በእግር፡፡ ፳፩. ኢንጭኒ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ኢንጪኒ፤ (ከአ.አ. በሆለታ 65 ኪ.ሜ.) ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ደነባ → ሲያ ደብር → በእግር፡፡ ፳፪. ቆሪቻ ኮቲቻ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጮቢ ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → በአምቦ መስመር (ጊንጪ) → ጮቢ → ቆሪቻ ኮቲቻ፡፡ ፳፫. ጊዶሌ የጋርዱላው (የዐድዋው) ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ ፳፬. ያበደማን ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ ፳፭. ደንደገብ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ ፳፮. አትርፎ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ የአድራሻ ምንጭ /ገዳማትና አድባራት ገጽ/ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ቅዱሳን #Saints #ክብረ_በዓላት #Feasts https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw...

እንኳን ለቅድሱ ጊዮርጊስ ስባረ ዓፅሙ (ዝርወተ አጽሙ ) በሰላም አደረሳቹሁ ፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን የታመነ ሰማዕት በመሆኑ ያረፈበት መሬትና ዕፅዋት ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እያሉ ያመሰገኑበት ነው፡፡ ------------ ....ነገሥታቱም ጊዮርጊስን ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ሙሉውን ታሪክ እዚህ ያንብቡ ----> https://t.me/medihanaelem/6273 ፠ እንደ ጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ባሉት ክብረ በዓሉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርዶና አድሮ ነው በዓሉ የሚከበረው፡፡ በጎንደር በጥር ወር የሚከበሩ በዓላት ወደ ጥምቀተ ባሕር በመውጣት የሚከበሩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ጥር 18 አበራ ጊዮርጊስ፤ ጥር 21 ሎዛ ማርያም፣ ጥር 22 ቅዱስ ዑራኤል (በዓታ ያለው)፤ ጥር 25 ቅዱስ መርቆሬዎስ (በተለይ በገጠሩ አካባቢ፡፡) እርሱ እንደ ንብ አውራ ፈረሱ እንደ አሞራ፤ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያን አደራ፡፡ ሰአል ለነ ጊዮርጊስ፤ ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ ዘሐረፀከ ዱድያኖስ፤ ወወገረከ ደብረ ይድራስ፤ ዘዘረወከ በነፋስ፡፡ ጥር ፲፰፤ በአዲስ አበባ የሚከበርባቸው #፲፯ #ገዳማትና አድባራት፡፡ ፩. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ (ከ186 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፥ በቶታል ገባ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ(ከፒያሳ) → ሳሪስ /ቃሊቲ/ → ሣሎ፤ ፪. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ፒያሳ፥ ዳግማዊ ምኒልክ አደባባይ፤ ታክሲ፤ ከማንኛውም አዲስ አበባ አቅጣጫ → ፒያሳ /ጊዮርጊስ/፤ ፫. (ቤተል) ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት (ጦር ኀይሎች) → ቤቴል፡ ፬. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ብረት ድልድይ፤ ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ (ከ4 ኪሎ) (ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ→ ብረት ድልድይ፡፡ ፭. ኮተቤ ሃገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፥ ቅድስት ማርያምና ቅድስት መግደላዊት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤ ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ (ከ4 ኪሎ) (ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ→ አንቆርጫ፡፡ ፮. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ኮተቤ/አባዶ/ካራ፡፡ ፯. ቦሌ ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ (በ2012ዓ.ም. የ24ት ሰፈር ወጣቶች ሰማዕት ኾኑት በክብር ያረፉበት ደብር) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፰. ቦሌ አየር ማረፊያ መንበረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አየር ማረፊያ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቦሌ አየር ማረፊያ፡፡ ፱. ቦሌ ሰሚት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሰሚት ኮንዶሚኒየም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ሰሚት ኮንዶሚኒየም፡፡ ፲. ቦሌ አራብሳ ዋሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አራብሳ፥ ዐደባባዩ ጋራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → አራብሳ (ኮንዶሚንየም /ዐደባባዩ ጋራ/)፡፡ ፲፩. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ/ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ኬላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ቱሉ ዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ (በ… መንገድ)፡፡ ፲፪. አያት 49 ጀልዱ ቅዱስ ጊዮርጊስና ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አያት ጠበል (አያት 49)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → አያት ጠበል → አያት 49፡፡ ፲፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ሐና፥ ማንጎ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ሐና /ማንጎ ሰፈር/፡፡ ፲፬. አስኮ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ዊንጌት) → አስኮ፡፡ ፲፭. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም፤ (በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፲፮. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ዊንጌት) → አስኮ አዲስ ሰፈር፡፡ ፲፯. ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ ጄነራል ዊንጌት ት/ቤት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → አስኮ/ዊንጌት/፡፡ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፳፮ #ጥንታውያን #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (በዘመነ አስተርእዮ የሚወጡ ታቦታት በአንዳንድ የሃገራችን ክፍሎች እንደ ጥምቀት በዓል ታቦታቱ ወደ ትምቀተ ባሕር በመውረድ ነው የሚያከብሩት) ፩. ብልባላ ጊዮርጊስ፤ (ከ1500 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያለው/ላሊበላ ከማነጹ 600 ዓመታት በፊት የታነጸ፥ ከ485 ዓ.ም እስከ 536 ዓ.ም. በንጉሥ አፄ ካሌብ ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍሎ የታነጸ)፡፡ አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሃገረ ስብከት፥ ብልባላ ወረዳ፥ ብልባላ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ብልባላ (በሰቆጣ መስመር) (ከላሊበላ 30 ኪ.ሜ.)፡፡ ፪. ደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ቤተ ጊዮርጊስ፤ አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሃገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡

የእርዳታ ጥሪ በቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለም ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት አገልጋይ የሆነችው እኀታችን ርግበ ወልደ ጊዮርጊስበደረሰባት የኩላሊት ህመም ምክንያት በአስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኝት እንዳለ
የእርዳታ ጥሪ በቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለም ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት አገልጋይ የሆነችው እኀታችን ርግበ ወልደ ጊዮርጊስበደረሰባት የኩላሊት ህመም ምክንያት በአስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኝት እንዳለባት የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አስታውቋል፡፡ በዚህ ሰዓትም የዲያሊስስ (dialysis) ሕክምና እያረገች ትገኛለች፡፡ የንቀለ ተከላ ሕክምና አስክትጀምር ድረስም በሳምንት ከ 6000 ብር በላይ እያወጣች ትገኛለች፡፡ ለሕክምናውም አቅም ስለሌላት የተቻላቹሁን ያክል እንድትረዷት በመድኀኔዓለም ስም እንጠይቃለን፡፡ 1000450996727 | አስኳል አረጋዊ ፣ መስታወት ይጥና ፣ ቢልልኝ ታከለ 0910299573 | 0934984689 | 09 11864443