es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 335 suscriptores, ocupando la posición 5 641 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 335 suscriptores.

Según los últimos datos del 15 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -80, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.23%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.47% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 409 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 605 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 16 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 335
Suscriptores
-124 horas
-117 días
-8030 días
Archivo de publicaciones
#እንኳን #ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_በዓል_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ፡፡ ጥቅምት 5 በዓለ ዕረፋቱ ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ ስለዚህም ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር የመጋቢት 27 ስቅለት ደግሞ ጥቅምት 27 ቀን እንዲከበር ተደረገ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ይህ ስርዓት ሆነ ይህንንም  ስርዓት አባቶታችን ሰሩልን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (አቦ፥ አቡዬ)፤ * እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤ * እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤ * ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤ * ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤ * በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤ * 60 አናብስትና 60አናብርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤ * ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት (ለአብነትም፤ ለቅዱስ #ላሊበላ፥ ለአቡነ #ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ #አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ) ፠፠፠ #ምድረ_ከብድ_፤ /ዝ_ምድር_ክቡድ_ውእቱ_/ ፤ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ምድረ ከብድ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረፉባት ቦታ ናት፤ ቀጥሎ ወደ ደብር ቅዱስ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ለጸሎት ሂደው ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለዓለማችን ምሕረትና በረከትን ከአምላካችን ለ100 ዓመታት በባሕር ውስጥ ሆነው ለምነዋል፤ *ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል፤ ቊራም በሰይጣን ተመስሎ መጥቶ ዓይናቸውም ቢያጠፋውም ከ7 ሱባዔያት በኋላ ሊቀ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል ዓይናቸውን መልሰውላቸዋል፡፡ *ወደ ዝቋላ በመመለስም አጋንንትም ከምድረ ዝቋላ አጥፍተዋል፤ ፠ እንደገና ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው በነበሩበት ጊዜ ታላላቆቹና በአንበሳ ዘባን ላይ የሚሄዱት #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ፣ #አባ_አንበስ_ዘደብረ_ሐዘሎ_አፋር)፣ #አባ_ብንያም_ዘግብፅ ከአባታችን ቡራኬ ለመቀበል መጡ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተሰውረው ነበርና፤ የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ አናብስት የ3ቱን አባቶች አናብስት በሉባቸው፤ በ7ኛው ቀን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተገልጠው የኾነውን ነገር በማየት የተበሉትን አናብስት እንዲመልሱ የራሳቸውን አናብስት አዘዟቸው መልሰውም እንደነበሩ በተዓምራት አስነስተው ሰጧቸው፤ በደመና ጠቅሰው ቅዱስ ፋኑኤል 3ት ሰማያዊ ኅብስትና 3ት ጽዋዕ ይዞ ለእንግዶቻቸው ይዘው ሠረገላ በሚባለው ዋሻ አመጡላቸውና ሰጥተው ሸኟቸው፤ እነዚህን ቅዱሳን በሸኙ በ7ኛው ቀን ወደ ተለያዩ ሃገራት ሄደው አስተምረዋል፡፡ ፠ እድሜያቸው ረዥም እንደመሆኑ፤ ቅዱሱ ንጉሥ አፄ ላሊበላን ጨምሮ ሌሎችም ቅዱሳን ወደ ርሳቸው እየመጡ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ፠#በግብፅ_300_ዓመታት_፥ #በኢትዮጵያ_ምድር_ላይ_262_ዓመታት (በዋነኛነት #በምድረ_ከብድና_በዝቋላ_ ቢኖሩም ሌሎችም የመሠረቷቸውና የኖሩባቸው ገዳማት አሉ፤ ለአብነትም ደቡብ ወሎ የሚገኘውን #ገዘዛ_አቦን_ መጥቀስ ይቻላል) ፠ በድምሩ 562 ዓመታት ከኖሩ በኋላ በንጉሥ ሕዝብናኝ(እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት፤ መጋቢት 5 ቀን ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙ ቃል ኪዳንን ጌታችን ሰጣቸው፥ 12 አክሊላትንም አቀዳጃቸው፤ የነበሩባት ምድረ ከብድ ገዳም ግን ራደች፥ ተንቀጠቀጠች፥ በብርሃንም ተጥለቀለች፤ ዝቅ እያለችም መንሸራተት ጀመረች፤ ጌታችንም አንቺ መሬት ሆይ ጽኚ ይህንን ኹሉ ስለቻልሽ ምድር ክቡድ /ኋላ ምድረ ከብድ/ ተብለሽ ተጠሪ አላት፤ የጻድቁም ነፍስ ከሥጋቸው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ተለየች፡፡ ፠ ይህችውም ምድረ ከብድ ጻድቁ የኖሩባትና የቀደሱባት፥ የመሠረቷትና ያነፅዋት፣ ሠራዊተ መላአክት የከተሙባት፣ ታላላቅ አበው መጥተው በረከት ከአባታችን የተቀበሉባት፣ አርምሞና ጸጥታ የማይለያት፤ አጸዷና ቅጥሯ ልቡናን የሚመስጥ፤ ከአ.አ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡ አምላከ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት፥ በረከትን ይክፈለን፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#አብርሃ_ወአጽብሃና_4ቱ ቅዱሳን ነገሥታት እስከ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከነገሡ ነገሥታት የሚለዩበት ነገር አለ ይኸውም፤ ክህነትን ከንግሥና፥ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ (እንደ
+1
#አብርሃ_ወአጽብሃና_4ቱ ቅዱሳን ነገሥታት እስከ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከነገሡ ነገሥታት የሚለዩበት ነገር አለ ይኸውም፤ ክህነትን ከንግሥና፥ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ (እንደ ካህኑ መልከጼዴቅ፣ አፄ ገብረመስቀል፣ አፄ ቴዎድሮስ ቀዳማዊ፣ …) እግዚአብሔርንም ሰውንም ያገለገሉ ናቸው፤ ከዚህም በተጨማሪ ቅድስናን ከሐናፄ ቤተመቅደስነት ጋር ደርበው የያዙም ጭምር ናቸው፡፡ በዚህም በንግሥናቸው ሀገርን በመልካም ሥራና በቅድስና ከማስተዳደራቸው በተጨማሪ ቅዱሳን ጻድቃን ሆነው እግዚአብሔርን በብዙ ድካም በመልካም ተጋድሏቸው ያገለገሉና አገልግሎታቸውም ሆነ ቅድስናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ የተመሰከረላቸው፤ ጽላት የተቀረጸላቸው፥ ገድል የተጻፈላቸው፤ (ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እጅግ ድንቅ የኾኑ) ቅዱሳን ናቸው፡፡ ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 364 ዓ/ም አጽብሐ ጥቅምት 4 ቀን 379 ዓ/ም በሞተ ሥጋ አርፈዋል፡፡ ክብረ በዓላቸው በትግራይ ባለ ውቅር ገዳማቸው፤ በአዲስ አበባ ደግሞ፤ * * በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ **በየካ ተራራ ዋሻ ተክለ ሐይማኖት **በአያት ቅዱስ ፋኑኤል ቤተክርስቲያን፡፡

#አቡነ_በርተሎሜዎስ_ዘደብረ_ዘመዳ፤ ፠ተወልደው ያደጉት በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሸዋ ቡልጋ፤ በጥራ መረዋ አካባቢ ነው፡፡ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ሚስት አጭተው ቢያጋቡትም፤ እንደ ድሜጥሮስ ንጽሕናውን ጠብቆ ለጥቂት ጊዜያት ከቆየ በኋላ ወግር ወደሚባል ተራራ ሂዶ 40 ቀን ሱባዔ ገባ፡፡ ሱባዔውን እንደጨረሰም ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባ፡፡ ፠ በደብረ ሊባኖስ ገዳምም ከታላቁ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የምናኔ ሕይወትን ተማሩ፡፡ ፠ምንኵስናን ከጓደኛቸው ከኤዎስጣቴዎስ ጋር አበአንድነት የተቀበሉትም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ ከትግራይ ወሰን እስከ አንገት ያለውን እንዲያስተምሩም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተልከዋል፡፡ ፠ ወደ እንፍራንዝ (ጣና) ከጌርሎስ ከአኖሬዎስ ልጅ ዘንድ ሄደው ሰነበቱና ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡ ፠ ክርስትናን ለማስፋት ተመርጠው ከተሾሙ ዓበይት ንቡራነ ዕድ አንዱ ሲሆኑ፤ የተሾሙበት ሃገረ ስብከታቸውም በቆባ፣ የጠጠርና የኮረም ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ነው፡፡ በተለይም በወሎና በአፋር ድንበር አካባቢ ወንጌልን በትጋት አስተምረዋል፡፡ ፠ 12ቱ ንቡራነ ዕድ ከያሉበት ሃገር ወደ ደብረ ሊባኖስ በመምጣጥ ወር ወር የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን አጽም ያጥኑ ነበር፤ የጻድቁ ዘቡነ በርተሎሜዎስ የማዕጠንት ተራቸውም በወርኃ ጳጕሜን ነበር፡፡ ፠ አፄ ዐምደ ጽዮን የአባቱን ሚስት በማግባቱ ቅዱሳኑና ግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ያዕቆብ በመቃወማቸው፤ በአፄ ዐምደ ጽዮንና በልጁ በአፄ ሰይፈ አርዕድ መሰደድ ደረሰባቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ከጳጳሰ ጋር ወደ ግብጽ መሰደድ ጀመሩ ነገር ግን፤ አቡነ ያዕቆብ ለአቡነ በርተሎሜዎስ ጽላተ ማርያምን ሰጥተው እንዲመለሱ አደረጓቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ጽላተ ማርያምን በደብረ ዘመዳ በክብር አስቀመጣት፡፡ ፠ በ14ኛው መቶ ክ/ዘ ጥቅምት አርፈው በደብረ ዘመዳ ገዳም ዐጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ #ደብረ_ዘመዳ_ማርያም_አቡነ_በርተሎሜዎስ_ገዳም (#ደብረ_ዠመዳ) ገዳሙ የሚገኘው ወሎ ላስታ ውስጥ ሲሆን የመሠረቷት አቡነ በርተሎሜዎስ ናቸው፡፡ በዚህ ገዳም እንደ አኵሱምና ደብረ ሊባኖስ ሰዐታትና ማኅሌት ሁልጊዜም ይቆምባታል፡፡ በዚህ ገዳም በርካታ ጥንታውያንና ድንቅ የሆነ ቅርሶች አሉ፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ የሳላት የእመቤታችን ስዕል የምትገኘውም በዚሁ ገዳም ሲሆን፤ መልኳ የሚቀያየርና ቅዱስ ዮሐንስ የሚባል ደግ ሰው ነው ወደዚህ ገዳም ያመጣት፡፡ ** ገዳሙ የሚጠበቀው በዋነኛነት እንደ ነብር ባሉ የዱር አራዊት ነው፡፡ ፠፠፠የደብረ ዘመዳ ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበረው በጥቅምት 4 በአቡነ በርተሎሜዎስ በዓለ ዕረፍታቸው ቀን ነው፡፡ ፠፠፠ ታላቁ ገዳም ደብረ ዘመዳ የሚገኘው፤ ሰሜን ወሎ ዋጃ ከተማ ከተደረሰ በኋላ የተወሰኑ ሰዓታት የእግር ጕዞ በመጓዝ ነወ፡፡ ከጻድቁ ከአቡነ በርተሎሜዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ አሜን፡፡ /ምንጭ፤ ገድለ አቡነ በርተሎሜዎስ የብራና፤ የአማርኛ የቤ/ክ መዝገበ ቃላት፣ ዶ.ር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ፣ ዝክረ ቅዱሳንና ከገድላት አንደበት የፊት ገጾች፡፡) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

እንኳን ደስ አላችሁ!!!! እሑድ ጥቅምት 3 ቀን 2017 ዓ.ም. (ዳግመኛ የማይገኝ ግብዣ፤ እንዳያመልጥዎ!!!) ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በኪደቱ እግሩ መጥቶ በጸለየበት እንጦጦ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ራጕኤል ወኤልያስ ቤ/ን ለመጀመሪያ ጊዜ (በአዲስ አበባ ጻድቁን በመዘከር 2ኛ ቤተ ክርስቲያን ሆኖ) ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ይከበራል፡፡ ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር፡፡ (እንጦጦ ከባለውለታዎቿ ቅዱሳን መካከል አንዱ የሆነውን አባ ጊዮርጊስን በ1417 ዓ.ም. ዕረፍቱ ሲሆን ልክ በ600 ዓመቱ በ2017 ዓ.ም. ልትዘክረው ተነሥታለች፡፡) ዋና ገዳማቸው የጋሥጫ ገዳም አባቶችና እናቶችም በአዲስ አበባ እንጦጦ #ዳቤ አዘጋጅተው ይጠብቁናል!! ጥቅምት 3 ቀን 1357 ዓ.ም.፤ ጽንሰቱ፤ ሐምሌ 7 ቀን 1358 ዓ.ም. ልደቱ፤ ሐምሌ 7 ቀን 1417 ዓ.ም. ዐረፍቱ ነው፡፡ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_፤ ፠ ከ40 በላይ መጻሕፍትን የደረሰና ብዙ መጻሕፍትን እያጻፈ ለመላው ገዳማት ያዳረሰ ጸሓፊና አታሚ፥ ፠ ቅዱስና ጻድቅ፥ ፠ ፈላስፋና ደራሲ፥ ፠ መናኝና ባሕታዊ፥ ፠ ሊቅና ተመራማሪ፥ ፠ ገጣሚና ባለቅኔ፥ ፠ የመጻሕፍት ተርጓሚና የዘመን አቈጣጠር (የአቡሻህር) ሊቅና ተንታኝ፥ ፠ አርክቴክትና መሐንዲስ ነው፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #ደብረ_ባሕርይ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_ወደብረ_ጎል_አባ_በጸሎተ_ሚካኤል_ገዳም፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ባሕርይ፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ከላላ፡፡ ወይም፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሐቤቴ (መርጡለ ማርያም) → ከላላ፡፡ ፪. #ደሴ_መስቀለ_ክርስቶስና_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገ ስብከት፥ ደሴ፥ ጦሳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ → ደሴ → ጦሳ፡፡ ፫. #አ.አ. #ፈረንሳይ #መድኀኔዓለም_ወአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_፤ አድራሻ፤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፥ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ ኢየሱስ ከፍ ብሎ፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (4 ኪሎ) → ፈረንሳይ ኢየሱስ፡፡ ፬. #ርዕሰ_አድባራት_ወገዳማት_እንጦጦ_ደብረ_ኀይል_ቅዱስ_ራጕኤል_ወኤልያስ_፤ አድራሻ፤ አዲስ አበባ ሃገረ ስብከት፥ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (4ኪሎ) → ሽሮሜዳ → ቊስቋም → ራጕኤል፡፡ / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches /

#አቡነ_በርተሎሜዎስ_ዘደብረ_ዘመዳ፤ ፠ተወልደው ያደጉት በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሸዋ ቡልጋ፤ በጥራ መረዋ አካባቢ ነው፡፡ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ሚስት አጭተው ቢያጋቡትም፤ እንደ ድሜጥሮስ ንጽሕናውን ጠብቆ ለጥቂት ጊዜያት ከቆየ በኋላ ወግር ወደሚባል ተራራ ሂዶ 40 ቀን ሱባዔ ገባ፡፡ ሱባዔውን እንደጨረሰም ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባ፡፡ ፠ በደብረ ሊባኖስ ገዳምም ከታላቁ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የምናኔ ሕይወትን ተማሩ፡፡ ፠ምንኵስናን ከጓደኛቸው ከኤዎስጣቴዎስ ጋር አበአንድነት የተቀበሉትም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ ከትግራይ ወሰን እስከ አንገት ያለውን እንዲያስተምሩም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተልከዋል፡፡ ፠ ወደ እንፍራንዝ (ጣና) ከጌርሎስ ከአኖሬዎስ ልጅ ዘንድ ሄደው ሰነበቱና ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡ ፠ ክርስትናን ለማስፋት ተመርጠው ከተሾሙ ዓበይት ንቡራነ ዕድ አንዱ ሲሆኑ፤ የተሾሙበት ሃገረ ስብከታቸውም በቆባ፣ የጠጠርና የኮረም ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ነው፡፡ በተለይም በወሎና በአፋር ድንበር አካባቢ ወንጌልን በትጋት አስተምረዋል፡፡ ፠ 12ቱ ንቡራነ ዕድ ከያሉበት ሃገር ወደ ደብረ ሊባኖስ በመምጣጥ ወር ወር የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን አጽም ያጥኑ ነበር፤ የጻድቁ ዘቡነ በርተሎሜዎስ የማዕጠንት ተራቸውም በወርኃ ጳጕሜን ነበር፡፡ ፠ አፄ ዐምደ ጽዮን የአባቱን ሚስት በማግባቱ ቅዱሳኑና ግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ያዕቆብ በመቃወማቸው፤ በአፄ ዐምደ ጽዮንና በልጁ በአፄ ሰይፈ አርዕድ መሰደድ ደረሰባቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ከጳጳሰ ጋር ወደ ግብጽ መሰደድ ጀመሩ ነገር ግን፤ አቡነ ያዕቆብ ለአቡነ በርተሎሜዎስ ጽላተ ማርያምን ሰጥተው እንዲመለሱ አደረጓቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ጽላተ ማርያምን በደብረ ዘመዳ በክብር አስቀመጣት፡፡ ፠ በ14ኛው መቶ ክ/ዘ ጥቅምት አርፈው በደብረ ዘመዳ ገዳም ዐጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ #ደብረ_ዘመዳ_ማርያም_አቡነ_በርተሎሜዎስ_ገዳም (#ደብረ_ዠመዳ) ገዳሙ የሚገኘው ወሎ ላስታ ውስጥ ሲሆን የመሠረቷት አቡነ በርተሎሜዎስ ናቸው፡፡ በዚህ ገዳም እንደ አኵሱምና ደብረ ሊባኖስ ሰዐታትና ማኅሌት ሁልጊዜም ይቆምባታል፡፡ በዚህ ገዳም በርካታ ጥንታውያንና ድንቅ የሆነ ቅርሶች አሉ፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ የሳላት የእመቤታችን ስዕል የምትገኘውም በዚሁ ገዳም ሲሆን፤ መልኳ የሚቀያየርና ቅዱስ ዮሐንስ የሚባል ደግ ሰው ነው ወደዚህ ገዳም ያመጣት፡፡ ** ገዳሙ የሚጠበቀው በዋነኛነት እንደ ነብር ባሉ የዱር አራዊት ነው፡፡ ፠፠፠የደብረ ዘመዳ ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበረው በጥቅምት 4 በአቡነ በርተሎሜዎስ በዓለ ዕረፍታቸው ቀን ነው፡፡ ፠፠፠ ታላቁ ገዳም ደብረ ዘመዳ የሚገኘው፤ ሰሜን ወሎ ዋጃ ከተማ ከተደረሰ በኋላ የተወሰኑ ሰዓታት የእግር ጕዞ በመጓዝ ነወ፡፡ ከጻድቁ ከአቡነ በርተሎሜዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ አሜን፡፡ /ምንጭ፤ ገድለ አቡነ በርተሎሜዎስ የብራና፤ የአማርኛ የቤ/ክ መዝገበ ቃላት፣ ዶ.ር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ፣ ዝክረ ቅዱሳንና ከገድላት አንደበት የፊት ገጾች፡፡) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

የጥቀምት 2 የማኅሌተ ጽጌ ወረቦች፤ በሊቀ ጕባኤ ደምፀ አንበርብር፣ በሊቀ ጠበብት ኤርምያስና በደብራችን ሊቃውንት፡፡ 1) 1 ጽጌ አስተርአየ 2) 2 ናሁ አስተርአየ 3) 3 እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ወረብ 4) 4) ንዒ ርግብየ ሐዋርያት (የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱ ቀለም) 5) 5 ክበበ ጌራ ወርቅ ወረብ 6) 6 ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት 7) 7 አርአዮሙ ለመምህራን 8) 8 ከማሃ ኃዘን ወተሰዶ ኃዘን ወረብ