es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 389 suscriptores, ocupando la posición 5 582 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 199 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 389 suscriptores.

Según los últimos datos del 02 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 23, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.38%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.20% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 290 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 569 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 17.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 03 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 389
Suscriptores
-324 horas
+207 días
+2330 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 2028ኛ ዓመት የልደት በዓል አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ #ፎቶው_ላይ_የምትመለከቷቸው_አብያተ_ክርስቲያናት፤ 1)፠፠ #መናገሻ_ጋራ_ልደታ_ለማርያም፤ በአፄ ይስሐቅ ዘመን የተመሠረተች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመስቀላቸው የባረኳት፣ ግማደ መስቀሉ ያረፈባት፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተጠቀሰች ገዳም፡፡ 2)፠፠ #ጎንደር_መካነ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም_ቤተ_ክርስቲያን፡፡ * ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዷ የኾነች፤ አጸዷ ውጡ ውጡ የማያሰኝ ፍጹም መንፈስን፣ ነፍስንና ሥጋን የመመሰጥ ኃይል ያለው ቦታ ነው፡፡ * በስዕለት ሰሚነቷ የአፄ ዮስጦስንም ስዕለት ስለሰማቻቸው፤ አድረሺኝ (ቢያደርሰኝ ቢያደርሳችሁ እየተባለ ዛሬ ሞላው ጎንደር በፍልሰታ ማብቂያ የአድርሺኝ ስዕለቱን እንዲያወጣ መሠረት የኾነች ቤተ ክርስቲያን፡፡ * የ4ቱ ጕኤያት (መጻሕፍተ ትርጓሜያት፤ ብሉያት፣ ሐዲሳት፣ ሊቃወንትና መነኮሳት) ማስመስከሪያ የነበረች፤ አሁንም ይህንን ጕባኤ ለማስጀመር በሒደት ላይ የምትገኝ፡፡ * የታች ቤት ትርጓሜ ጀማሪና መምህር የኾኑት ሊቁ ዐራት ዐይና መምህር ኤስድሮስ ጕባኤ ከፍተው አትሮኖስ ዘርግተው ወንበር ተክለው ያስተማሩባት፤ ውዳሴ ማርያም ዘኀሙስ ‹‹ዳዊት ከቤተ ልሔም ውኃ ምንጭ ይጠጣ ዘንድ ፈለገ… የሚለውን ሲያትቱ ይህችው የቤተ ልሔም ውኃ እንደ ጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ማርያም ጠበል ነች፤ ያቺ የቤተ ልሔም ውኃ ጽምአ ዳዊትን ታረካ ነበርና (አርክታለች)፤ ይህች የልደታ ጠበል ምዕመናንን ከጤና ጽምእ ታረካለችና ትፈውሳለችና፤…. እያሉ ያነሷት፡፡ ዛሬም ድረስ ይህች የልደታ ጠበል በፈዋሽነቷ የታወቀችና ብዙ ሕሙማንን የሚፈወሱባት ናት፡፡ * በርካታ ለሃራችንና ለዓለማችን ትላልቅ ሥራን የሠሩ ሊቃውንትን ያፈራች፡፡ * የጎንደር ልደታ በደርቡሽ ጎንደር ስትቃጠልና ስትፈራርስ የመጀመሪያ ቤተ ክርስቲያኗም ፈርሷል (የመጀመሪያው ፎቶ የሚያሳየው ደርቡሾች ካፈረሱት የተረፉት አምዶችን ነው)፡፡ 3) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ማኅደረ_ስብሐት_ልደታ_ለማርያም፤ በ1916ዓ.ም. የተመሠረተች፡፡ 4) ፠፠ #መቀሌ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 5) ፠፠ #አዲስ_አበባ_ደብረ_ዕንቊ_ልደታ_ለማርያም_ቤ.ክ. 6) ፠፠ #ሚዛን_አማን_ቅድስት_ልደታ__ቤ.ክ. 7) ፠፠ኢሉባቦር__ጮራ__ደብረ__ብርሃን__ቅዱስ__ሚካኤል__ወልደታ__ቤ.ክ. /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ꔰ ወስብሐት ለእግዚአብሔርꔰ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

ꔰ ꔰꔰእንኳን ለእመቤታችን 2028ኛ ዓመት በዓለ ልደት አደረሳችሁꔰ ꔰꔰ ꔰ #ልደታ_ለማርያም ꔰ ꔰ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? ꔰ ፠ #የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓልና_የእመቤታችን_በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል›› ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ /ዮሐ. 10፥22/ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል፤ ‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ. 111፥7 በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33ት በዓላት አሏት፡፡ ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘው ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› ይላል፡፡ 1ኛ ዜና 29፥29 ፠ #የእመቤታችን_የልደቷ_ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሐና››ና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሐና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሐና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሐና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠ #እመቤታችን_የት_ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሐሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሐሳቦች የሚያነሱ ሲሆን፤ አንደኛዉ ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች›› የሚል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ሐሳብ ደግሞ ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሐና የክሩሲድ ቤ/ክ በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፊንቄ በስተምስራቅ ይገኛል፡፡ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ›› መኃ. 4፥7 የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምሥጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡ ፠ #የልደታ_ለማርያም_በዓል_መቸ_ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡ በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤ በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡ በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡ የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ #የድንግል_ማርያም_ልደት_ለምን_ይከበራል? * ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅ/ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› በማለት ተነግሯል (ሉቃ 1-14)፤ ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ፥ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ፤ የድንግል ማርያም ልደትማ ምንኛ የሚያስደስት ይሆን!?፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ * የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል * እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፤ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ሕልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ፤ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ * ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት ‹‹መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››፤ ‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››፤ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ››፤ …. ብለዉ የተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ደስታችንም ነዉ፡፡ (መዝ. 86፥1፣ ኢሳ. 11፥1፣ መኃ. 4፥7) * በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል፤ ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል፡፡ ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ግን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠ #የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር ሐናና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳውያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ፈንድሻ የሚጥሉ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ꔰ የድልበር መካነ ጎልጎታ #መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እምነት ተስፋ ፍቅር ሰንበት ት/ቤት በ600 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ለሚያስገነባው ሁለገብ ህንጻ በቀን 27/08/2013 የመሠረት ድንጋይ ጣለ::
ꔰ የድልበር መካነ ጎልጎታ #መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እምነት ተስፋ ፍቅር ሰንበት ት/ቤት በ600 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ለሚያስገነባው ሁለገብ ህንጻ በቀን 27/08/2013 የመሠረት ድንጋይ ጣለ:: ꔰ የመሠረት ድንጋዩን የጣሉት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ኃ/ማርያም ሲሆኑ ለእርሳቸው ረጅም የአገልግሎት ዘመንን ያድልልን እያልን ሰ.ት.ቤቱ ለቀጣይ ስራው #በጸሎት ፣ #በሃሳብ እንዲሁም በሚያደርጓቸው #ገቢ_ማሰባሰቢያዎች አግዘን በእግዚአብሔር ፈቃድ ለፍጻሜ እንድናበቃው ይሁን ፡፡ ለእምነት ተስፋ ፍቅር ሰንበት ት/ቤት ወንድም እና እኀቶቻችን ትጋትን አብዝቶ ይስጥልን !

የመስቀል አደባባይ ከመመረቁ በፊት ለምንም አገልግሎት እንደማይውል ወሳኔ መሰጠቱን ሚድያዎች እየዘገቡ ይገኛሉ!

የቦታው ታሪካዊ እና ትውፊታዊ ባለቤት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ናት !
የቦታው ታሪካዊ እና ትውፊታዊ ባለቤት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ናት !

፠ ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ሲያርፍ የ70 ዓመት አረጋዊ ነበረ፡፡ ከ30 ዓመታት በላይ በዘለቀ መዋዕለ ስብከቱ ለዓለም ሁሉ የምስራች የሚሆን የወንጌልን ቃል ከመጻፉ ባሻገር ከሐዋርያዊ ተልዕኳቸው የተነሣ ብርሃናተ ዓለም ከተባሉ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በብዙ አህጉረ ስብከት ተዘዋውሮ በማስተማሩና ይልቁንም የጥንት ግሪክ ሥልጣኔ ተስፋፍቶባትና የሮማ ሥርወ መንግሥት ቁልፍ የፓለቲካና የንግድ መዲና በነበረችው እስክንድርያ በሰማዕትነት እስካረፈባት ቅጽበት ድረስ በአንደበቱም በሕይወቱም በክብሩና በመከራው ሁሉ በማስተማር አይሁድን ከይሁዲነት ወደ ክርስቲያንነት ፥ አረማውያንን ከአምልኮ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሰ እንዲሁም በጸሎታቸው የሚጠብቁ፥ በትሩፋታቸው የጽድቅን ዋጋ የሚያሰጡ የባሕታውያን አባት አባ ጳውሊን፣ የመነኰሳት አባት አባ እንጦንስን፣ አባ ጳኩሚስ እና አባ ሰራብዮንን፤ መናፍቃንን ተከራክረው የረቱ ፥ ሃይማኖትን ያቀኑ ቅዱስ እለእስክንድሮስን ፥ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊን ፥ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያን፥ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪትና ቅዱስ ዲዮስቆሮስን የመሳሰሉ ኦሮቶዶክሳውያን ሊቃውንትንና እስከ ዛሬም መከራ ሳይበግራቸው፥ ሞትና ግርፋታቸውን እንደ ክብር ቈጥረው፥ በሃይማኖታቸው ፀንተው የሚኖሩ የጸኑ ምእመናንን ያፈራች አንፀባራቂ ስም ያላት ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን ያቋቋመ ሐዋርያ በመሆኑ ዳግመኛም ከ4ኛ ክ/ዘ/ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን እስከ አቡነ ቄርሎስ 20ኛ ክ/ዘ/ ድረስ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በክህነት የመገቡ 111 ጳጳሳት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ያቋቋማት የዚህችው ቤተክርስቲያን ፍሬዎች በመሆናቸውና ትምህርታችን ከትምህርታቸው ፥ ሥርዐታችን ከሥርዓታቸው የተስማማ ፥ የተግባባ በመሆኑ “ማርቆስ አባታችን ፥ እስክንድርያ እናታችን” ማለት በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ የተለመደ ነበር፥ ታሪክ ነውና ዛሬም ቢሆን ቤተክርስቲያናችን ሙሉ በሙሉ ከግብጽ ቤተክርስቲያን ጥገኝነት ተላቃ በኢትዮጵያውያን ጳጳሳት ብትመራም ይህ እውነታ ግን የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ፠ በፎቶ የምትመለከቷቸው አብያተ ክርስቲያናት፤ * ሰላ ድንጋይ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአፄ ምኒልክና የተሠራና የአቡነ ማቴዎስ መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ በልዩ አሠራር በ42 ቆመ ብእሲ (ዐምድ) የታነጸ፡፡ * መናገሻ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአቡነ ማቴዎስ የተሠራና መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ ውጭው ክብ ውስጡ ግን ከሌሎች ክብ አብያተ ክርስቲያናት ልዩና ድንቅ በሆነ አሠራርና ሥዕላት የተሞላ፡፡ * ጎጃም ደብረ ማርቆስ፤ * መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ፤ አፄ ኀይለ ሥላሴ ከቤተ መንግሥታቸው ላይ ቦታ ቀንሰው ያነጹት ቤ.ክ.፡፡ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ቅዱስ_ማርቆስ_ወንጌላዊ_ሚያዝያ_፴ ማርቆስ የሚለው ስም 3ት ፍቺዎች አሉት ንብ፣ አንበሳና ካህን:: ሀ) *ንብ የሚለው ፍቺ የተሰጠው ንብ አበባ ካለው ተክል ሁሉ ቀስማ ማር እንድትሠራ እርሱም ቀድሞ ከጌታ ኋላም ከጌታ የተማርኩት ይበቃኛል ሳይል ከሐዋርያት ተምሮ ደገኛይቱን ወንጌልን በማስተማሩና በመጻፉ ነው፤ ለ) *አንበሳ መባሉ አንበሳ እንስሳት አራዊትን በክርኑ እንዲሰብር፤ በግብጽ ይመለኩ የነበሩ በእንስሳ አምሳል የተሠሩ ጣዖታትን በወንጌል ቃል ኃይልነት በማጥፋቱ ነው፡፡ ሐ. *ካህን የሚለው ትርጕም ደግሞ በሐዋ. 14፥13 “ወአምጽኡ ማሬ ዘድዮስ” ተብሎ ከተመዘገበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ የተወረሰ ነው:: ፠ ማርቆስ ከመባሉ በፊት ዮሐንስ ይባል የነበረ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድዕት ነው፤ ሐዋ. 12፥12፡፡ አባቱ አርስጦቦሎስ እናቱ ማርያም ይባላሉ፡፡ እናቱ ማርያም በጌታ ትምህርት አምነው ሲከተሉትና ሲያገለግሉት ከነበሩት ደጋግ ሴቶች አንዷ ስትሆን ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ቤቷን ለወንጌል አገልግሎት ሰጥታ ሐዋርያት በዚያ ተሰብስበው ለጸሎት ይተጉ ነበር፥ ጌታ ባረገ በ10ኛው ቀን (በተነሣ በ50ኛው ቀን) ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ሳሉ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትም በዚሁ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ውስጥ ነው፡፡ ሐዋ. 2፥1 ፤ 12፥12፡፡ ፠ የራሱን ሀገረ ስብከት ይዞ ማስተማር ከመጀመሩ በፊት ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያትን እየተከተለ ይማር ፥ በተልእኮም ይራዳቸው ነበር:: ከቅዱስ ጳውሎስ መጠራት በኋላ ጳውሎስንና አጎቱ በርናባስን ተከትሎ በአንጾኪያ ፤ ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትሎ በሮም አስተምሯል፤ እነርሱም በመልእክቶቻቸው “ማርቆስ ሰላም ይላችኋል” እያሉ አንስተውታል:: ሐዋ. 12፥25፣ ቈላ. 4፥10፣ 1ኛ ጴጥ. 5፥13 ፠ በሮም ተልእኮው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ ከፍጹምነት መድረሱን ዐውቆ ጵጵስና ሾሞ ከሀገረ ስብከቱ ግብጽን ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጠው፡፡ እርሱም ሊያስተምር ሄዶ ወደከተማ ሊገባ ሲቃረብ የጫማው ጠፍር ተበጥሶበት አንያኖስ ወደሚባል ጫማ ሰፊ ሄደና ስፋልኝ ብሎ ሰጠው። አንያኖስ ጫማውን ተቀብሎ ሲሰፋ መስፊያው እጁን ወግቶት “ኢስ ታኦስ” ብሎ ጮኸ “አሐዱ እግዚአብሔር” ማለት ነው፤ የጠራኸውን ታውቀዋለህን? አለው፥ ሲሉ ሰምቼ እንጂ ያስተማረኝስ የለም አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ፈቃደኛነቱን አይቶ አስተማረው አንያኖስም ከነቤተሰቦቹ አምኖ ተጠመቀ:: ፠ ከዚህ በኋላ አንያኖስን አስከትሎ በከተማ እየተዘዋወረ ያስተምር ጀመረ፤ ሕዝቡም ትምህርቱን ሰምተው ፥ ተአምራቱን አይተው አመኑ፥ ተጠመቁ፤ አብያተ ጣዖታቱንም አፈራርሰው አብያተ ክርስቲያናትን ሠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የጣዖታቱ አገልጋዮች የለመዱት ቢቀርባቸው በጠላትነት ተነሡበት:: ምእመናኑ ተሰብስበው አባታችን እንድትለየን አንሻም፤ ነገር ግን ገነውተ ጣዖታቱ በጠላትነት ተነሥተውብሀልና ቁጣቸው እስኪበርድ ጥቂት ጊዜ ወደ ሌላ ሥፍራ ሄደህ ቆይ አሉት:: አንያኖስን ኤጲስቆጶስ ልጆቹን ቄስና ዲያቆን አድርጎ ሾሞላቸው፤ በባርቃና በሌሎች 5 አውራጃዎች እየሰበከ ቅዱስ ጴጥሮስን ለመጠየቅ ወደሮም ሄደ፤ በዚያ ሆኖ በስብከቱ ያመኑ የእስክንድርያ ምእመናን የተማሩትን እንዳይዘነጉ የማርቆስ ወንጌል ተብሎ የሚታወቀውን ወንጌል በሮማይስጥ ቋንቋ ጽፎ ልኮላቸዋል:: ዘመኑ ጌታ ካረገ 11ኛው ሲፈጸም 12ኛው ሲጀመር ፥ ቀላውዴዎስ ቄሳር በነገሠ በ4ኛው ዓመት /45-46ዓ.ም. ባለው ጊዜ/ ነው:: ፠ ከጥቂት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ግብጽ ተመለሰ፥ ምእመናኑ በቊጥር በዝተው፥ በእምነት ጐልምሰው አግኝቷተቸው ደስ ብሎት እያስተማራቸው አብሯቸው ጥቂት ጊዜ ቆየ:: በዓለ ትንሣኤን በሚያከብሩበት ቀን አምልኮ ጣዖት ከስሞ አምልኮተ እግዚአብሔር በመስፋፋቱ ምቀኝነት ያደረባቸው ጣዖታውያን ሊጣሉት መጡ፤ ምእመናኑ አባታችን ሽሽ አሉት፤ እንግዲህስ በጌታዬና በአምላኬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ወንጌል ክብር መከራ ልቀበል እንጂ ልሸሽ አይገባኝም፥ አልሸሽም አለ፡፡ እንደ ላም በአንገቱ ገመድ አስረው በረሀ ለበረሀ ሲጐትቱት ዋሉ ፥ ሥጋው በእሾህ በጋሬጣ ተቀረደደ፡፡ ወደጌታ ቢያመለክት፤ ስለተቀበልኸው መከራ ክብርህን ከ12ቱ ደቀመዛሙርቴ ክብር አንድ አድርጌልሀለሁ፤ በስምህ የተማፀነኝንም እምርልሀለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገብቶለት ነፍሱን በቃለ አቅርንት፥ በይባቤ መላእክት አሳርጓታል:: በሞቱ ያልረኩት ጣዖታውያኑ ከሞተም በኋላ ሥጋውን ለማቃጠል ሽተው እንጨት ሰበሰቡ የሚያቀጣጥልላቸውን ዝፍትም በከመሩት እንጨት ላይ አርከፈከፉ፤ ጌታ ግን ይህን እንዲያደርጉ ዕድል አልሰጣቸውም ድንገት ታላቅ ነጐድጓድ ሆነ፥ የተከማቹበት ሥፍራ ተናወጸ፥ የፀሐይም ብርሃን ተሠወረባቸው፤ በዚህ ጊዜ ምን መጣብን ብለው ማቃጠሉን ትተው ሸሽተዋል፡፡ ኋላ ግን ምእመናን በመብረቅ ጸዳል ተከብቦ አግኝተው በክብር ሥጋውን በአሌክሳንድርያ ቀብረውታል:: ፠ በዚህ ቦታ ተቀብሮ ለብዙ ዘመን ከቆየ በኋላ በ820 ዓ.ም ሁለት የቬኑስ ነጋድያን አጽሙን በድብቅ ከተቀበረበት አስወጥተው ወደ ቬነስ ወሰዱት፤ በዚህ ከተማ በሚገኘው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አኑረውት ቦታው የበላይ ቅዱስ ሆኖ በክብር ይኖር ነበር። ስለሆነም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰጣት በየጊዜው ከመጠየቅ አልቦዘነችም ነበር፡፡ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም የሮማው ርዕሰ ሊቀ ጳጳስ ጳውሎስ 6ኛ ስለፈቀዱ፤ ቅዱሱ ባረፈ በ1900 ፥ በተወሰደ በ1140 ዓመት አጽሙ ሰኔ 17 ቀን 1960 ዓ.ም. ፈልሶ ወደ ጥንተ ቦታው ለመመለስ በቃ፡፡ ሲመለስም ጃንሆይም በስፍራው ተገኝተዋል፡፡

በእውነትስ ለቀጨኔ ምዕመናን ልጆችን ለማስተማር ቦታ ቶሎ መስጠት ይህ ሁሉ የሚያለፋ ጉዳይ ነበር?? ሳይሳሳ ለቤተክርስቲያን ገንዘቡን ጉልበቱን ለሚሰጥ ለቀጨኔ ምእመናን ለልጆቹ መማርያ የሚሆን ቦታ የደብራችን አስተዳደር ሳይጠየቅ ሊሰጥ አይገባውም ነበር?? ሰንበት ተማሪዎች ተደራጅተው ካልተቀመጡስ ምን አይነት ልማት ይሰራ ይሆን?? ሳንጠይቅ ሊሰጡን ሲገባቸው ነገር ግን በሰ/ት/ቤቱ ቋሚ የመማርያ እና የአገልግሎት ጥያቄ ምክንያት ከደብሩ አስተዳደር ሰ/ት/ቤቱ ላይ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉ ይገኛሉ #ለአብነትም_ያህል  ከኀዳር 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለሰ/ት/ቤቱ አገልግሎት በሰበካ ጉባኤ የተፈቀደውን በጀት መከልከል  በሰንበት ት/ት ቤቱ የስራ አመራር አባላት ላይ እና የሰ/ት/ቤቱ አባላት ላይ በየመኖርያ ቤታቸው በመሄድ ቤተሰቦቻቸውን ልጆቻችሁን ተዉ በሏቸው በማለት ማስፈራራት  ፖሊስ ጣቢያ ክስ በመክፈት (እስካሁን ድረስ ያልተዘጋ ክስ)  በሰ/ት/ቤቱ አባላት እና በደብሩ ማኅበረ ካህናት በኩል መግባባት እንዳይኖር የሀሰት ወሬዎችን እና ሀሜቶችን በመንዛት እንድንለያይ ማድረግ  ከሀገረ ስብከቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎች እንዳይፈጸሙ የተለያዩ ምክንያቶች በመፍጠር ጉዳዩን ማንጓተት  የዘንድሮውን ዓመት የነዳያንን የማስፈሰክ አገልግሎት እንዲሰናከል ማድረግ ...ምንም እንኳን በሰ/ት/ቤቱ ጥረት ነዳያንን ብናስፈስክም ( ሙሉውን የዚህን ዓመት የነዳያንን የማስፈሰክ ሪፖርት ይዘንላችሁ እንቀርባለን) የተከበራችሁ የአጥቢያችን ወጣቶችና ምእመናን ሰ/ት/ቤቱ ይህ ሁሉ ነገር እየደረሰበት ያለው ለተተኪ ተውልድ በመጨነቅ እንደሆነ የምታውቁት ነገር ነው ፡፡ እናንተም የቤተክርስቲያን ጕዳይ ጉዳያችን ነው ብላችሁ ለትውልዱ ተጨንቃችሁ በቅርበት እና በንቃት ስለምትከታተሉን እናመሰግናችኋለን፡፡ ሰንበት ት/ት ቤታችንም ከእናንተ ከምዕመናን ጋር በመተባበር ሂደቱን በጥበብና በማስተዋል በማስኬድ ከሀገረ ስብከቱ ለ4ኛ ጊዜ የተወሰነው ውሳኔ ወደ ተግባር የማስቀየር ሃላፊነት አሁንም የሁላችንም ነው፡፡ ስለዚህ ከፊተኛው ይልቅ በርተተን ከመድኃኔዓለም ጋር የልጆቻችንን መማርያ ቦታ አሰጥተን ቤተክርስቲያንን እና ሀገርን የሚረከብ ትውልድ ማፍሪያ ትልቅ ተቋም ለማድረግ ጠንክረን ልንሰራ ይገባናል፡፡ አፈጻጸሙ መተግበር ካልቻለ መላውን የቀጨኔ ምዕመናን በቅርቡ የኮቪድን ህግ በመከተል የምንጠራችሁ እና አፈጻጸሙን በጋራ የምንሰራ መሆኑን አስቀድመን ልንገልጽላችሁ እንፈልጋለን ፡፡ ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን!!!

ለተከበራችሁ ለአጥቢያችን ምእመናን በሙሉ ከሁሉ አስቀድመን ሰላመ እግዚአብሔር በያላችሁበት ይድረሳችሁ ይህንን ጹሑፍ በጥሞና አንብባችሁ አስተያየታችሁን ጻፉልን ! ሰ/ት/በታችን በቋሚ የማስተማርያ ቦታ ጥያቄ ምክንያት ለበርካታ ጊዜያት እየሄደባቸው ያሉትን ጕዳዮች እና የደረሰባቸውን ውጤቶች እያሳወቅናችሁ መቆየታችን ይታወቃል፡፡ ከመስከረም 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 13/2013 ዓ.ም ድረስ ከአ.አ ሐገረ ስብከት የተወሰኑትን ውሳኔዎች ቀጥታ በሰ/ት/ቤቱ የ ፌስ ቡክ እና በደረ ገጽቻን አስነብበናችሁናል፡፡ ብጹዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ የአ.አ እና የጉራጌ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የመጀመርያ ውሳኔያቸውን መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ወደ ደብራችን ከላኩልን በኃላ መጋቢት 20/2013 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቱን ተወካዮች እና የደብሩን አስተዳደር ተወካዮች በቢሯቸው ጠርተው ካወያዩን በኋላ ለአፈጻጸም የሚረዳንን 3 አማራጮችን ሰጥተውን የአካባቢያችንም ሽማግሌ የሆኑት ታላቅ ሰው አቶ ተድላ ተሾመ እንዲሰበስቡን መመርያ ሰጥተውን ነበር፡፡ ብጹዕነታቸው እኛን እንዲሰበስቡን የመረጧቸው አቶ ተድላ ተሾመ በአካባቢ የተከበሩ ፣ ተሰሚ የሆኑ ፣ ሀገራዊ በሆኑ ትላልቅ አጀንዳዎች ላይ ማለትም የእርቅ ኮሚቴነት ፣ ሀገር ስትበጠበጥ በአረጋጊነት ከሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን በልዑክነት የሚመደቡ ፣ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያንን እድሳት በበላይነት እየመሩ የሚገኙ እና በመንፈሳዊ ሕይወታቸውም የተመሰከረላቸው ታላቅ እባት ናቸው፡፡ ብጹዕነታቸውም የሰጡን 3 አማራጮች 1. ሰ/ት/ቤቱ ወደ መዋዕለ ሕጻናት እንዲዘዋወር እና ለመዋዕለ ሕጻናቱ ደግሞ በቤተክርስቲያኑ ጀርባ የሚገኙት የገራዥ ቤቶች ላይ እንዲሰራ እና ደብሩ ካሰራው ሱፐር ሆሊ ሴቪየር ኢለመንተሪ ት/ት ቤት ጋር ተመጋጋቢ ሆኖ እንዲቀጥል፡፡ 2. የደብሩ አስተዳደር በዚህ ፍቃደኛ ካልሆነ ሰ/ት/ቤቱ አገልግሎቱን ማስፋት ስላለበት አሁን ባለበት አዳራሽ ላይ የራሱን ሕንጻ ገንብቶ የመማር ማስተማሩን ሂደት እንዲያስቀጥል፡፡ 3. የመዋዕለ ሕጻናት ግቢው ለሁለት ተከፍሎ ሰ/ት/ቤቱ እና መዋዕለ ህጻናቱ እኩል እንዲሄድ የሚል አባታዊ መመርያ ሰጥተው ከ3ቱ አንዱ መርጠን በቃለጉባኤ እንድናሳውቃቸው አዘውናል፡፡ በዚሁም መሰረት በክቡር አቶ ተድላ ተሾመ እጅግ የበሰለ ሰብሳቢነት ለሁለት ቀናት ጥልቅ የሆነ ውይይት ለረጅም ሰዓታት ከማህበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር ማለትም ( አጋፋሪ ዳዊት ፣ ቀሲስ ተ/መድኅን ፣ መልአከ ሕይወት ታደለ ፣ ቀሲስ ኃ/ማርያም ) ጋር በመሆን የተወያየን ሲሆን በ3ቱም አማራጮች ላይ ጥቅምና ጉዳታቸውን በማንሳት ሀሳብ ተንሸራሽሯል፡፡ ከዚህም በኋላ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ የጋራ ስምምነት አድርገናል 1. ሰ/ት/ቤቱ አሁን ባለው አዳራሽ ላይ ለሰ/ት/ቤቱ ህንጻ ከሚሰራ የደብሩ ልማት ቢገነባ የማኅበረ ካህናቱን የኑሮ ሁኔታ ስለሚሻሻል እና በቅዱስነታቸውም ለኮሜርሻል አገልግሎት የሚውል መሰረት ስለተጣለበት በዚሁ እንዲቀጥል በሰ/ት/ቤቱም በካህናቱም ተወካዮች ታምኖበታል፡፡ 2. መዋዕለ ሕጻናቱ ሙሉ በሙሉ ወደ ጋራዥ እንዲሄድና ሰ/ት/ቤቱ ሙሉ በሙሉ ወደ ነበረበት ቦታ የአሁኑ መዋዕለ ህጻናት እንዲገባ ከሰ/ት/ቤቱ ሃሳብ ቢቀርብም ተቀባይነት አላገኘም መዋዕለ ሕጻናቱ ወደ ጋራዥ እንዲሄድ ያልተፈለገባቸው 3 ዋና ምክንያቶች ደግሞ ቦታው ሾጣጣ ስለሆነ፣ ለቅሶ በአካባቢው በብዛት ስለሚያልፍ እና ናቸው ፡፡ ከዚህም ውጪ ማኅበረ ካህናቱ ካጸደቁት ውጪ ሌላ ሃሳብ አናመጣም፡፡ ካህናቱ በስብሰባቸው ወቅት መዋዕለ ህጻናቱ ጋራዡ ጋር አይገባም ብሎ በአንድ ድምጽ አጨብጭቦ ነው ከስብሰባው የወጣው የሚል ሃሳብ አቅርበዋል፡፡ ነገር ግን ሰ/ት/ቤቱ መዋዕለ ሕጻናት ውስጥ መማርያ ህንጻ እንዲገነባና ለመዋዕለ ህጻናቱ ለጊዜው ሌላ ጊዜያዊ ቦታ እናመቻቻለን በማለት ሃሳብ አቅርበዋል፡፡ 3. ሰ/ት/ቤቱ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ገብቶ የራሱን ማስተማርያ የሚሆን ህንጻ እንዲገነባ እና የምድር ወለሉ ግን ለመዋዕለ ህጻናት አገልግሎት እንዲውል ሃሳብ ሲያመጡ ይህ ሃሳብ የሰ/ት/ቤቱ ባይሆንም ነገር ግን ግቢው ውስጥ በተለይ ላለፉት 2 ዓመታት ሰላም ስለጠፋ ሰ/ት/ቤቱ ለሰላም ሲባል ይህንን ሃሳብ ተቀብሎታል፡፡ በዚህ ሀሳብ በመስማማት ሰ/ት/ቤቱ ቀድሞ ወደነበረበት ቦታ የሚገባበትን እና ተተኪ ትውልድ የማፍራት ተግባሩን አጠናክሮ የሚቀጥልበትን ፣ የደብራችንም ልማት አሁን ሰ/ት/ቤቱ ባለበት አዳራሽ ላይ በመገንባት ለደብሩ ገቢ የሚያስገባበትን ፣ መዋዕለ ህጻናቱም አሁን ደብሩ ካሰራው ከትልቁ ት/ት ቤት ጋር ተመጋጋቢ እንዲሆን በጋራዦቹ ላይ የሚሰራበትን ዲዛይን ጭምር ሰ/ት/ቤቱ አቅርቧል፡፡ የሰ/ት/ቤቱ ተወካዮች ከማኅበረ ካህናት ተወካዮች ጋር የጋራ ስምምነት ካደረግን በኋላ ሌላ 3ኛ ሃሳብ የማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች አመጡ፡፡ ይህም 1. የምድር ወለሉ ለመዋዕለ ህጻናቱ እንዲሰጥ ሆኖ 1ኛ ፎቅ እና 2ኛ ፎቅ ደግሞ ለደብሩ አስተዳደር ቢሮ በቋሚነት እንዲሆን የሚል ሃሳብ በማቅረባቸው እና ይህ ደግሞ ከሰ/ት/ቤቱ አገልግሎት ጋር ፍጹም የሚሄድ ስላልሆነ በዚህ ሃሳብ ሳንስማማ ብጹእነታቸው መመርያ ይስጡበት በማለት በ2 ሃሳባች ማለትም በደብሩ ልማት እና በሰ/ት/ቤቱ መዋዕለ ህጻናት ውስጥ የመማርያ ህንጻ ለመገንባት በመስማማት በአንዱ ሃሳብ ደግሞ በ1ኛ ፎቅ እና 2ኛ ፎቅ ለደብሩ ጽ/ቤት አገልግሎት ይሁን ብለው ማህበረ ካህናት ሃሳብ ባቀረቡት ባለመስማማት ቃለ ጉባኤውን ተፈራርመን ልከናል፡፡ ብጹእነታቸውም ይህንን ቃለጉባኤ በመረዳት ሚያዚያ 13/2013 ዓ.ም ለደብራችን አስተዳደር በብጹእነታቸው ደረጃ ለ2ኛ ጊዜ በሀገረ ስብከት ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ደብዳቤ ልከዋል፡፡ የላኩት ደብዳቤ ለሰላም ለፍቅር ለአንድነት ሲባል በደንብ ግራ ቀኙን አይተው አጢነው እስከ ሚያዚያ 20/2013 ዓ.ም ድረስ የመዋዕለ ህጻናቱ ውል እንዲቋረጥ/እንዲሻሻል የሚያስገድድ ደብዳቤ ለደብራችን አስተዳደር ልከዋል፡፡ በደብዳቤው ላይ ሰ/ት/ቤቱ የሚያሰራው የመጨረሻው ወለል በጊዜያዊነት ለደብሩ አስተዳደር እንዲውል ያዛል ይሁንና እንዲህም ተወስኖ አሁንም ግን የደብራችን አስተዳደር ይህንንም ደብዳቤ ሊያስፈጽም አልቻለም፡፡ ከማህበረ ካህናቱ ጋር ብንስማማም የጋራ መግባባት ላይ ብንደርስም ሊቀ ጳጳሱ ለ 2ኛ ጊዜ ቢወስኑም አስተዳደሩ ግን ሊያስፈጽም ያልፈለገበት ምክንያት ግልጽ አይደለም፡፡ ሰ/ት/ቤታችን ለሰላም እያደረገ ያለውን ጥረት በአንድ በኩል ብቻ ሆነና ውጤት ሊያመጣ አልቻለም ፡፡ የደብራችን አስተዳደር አሁንም በግቢው ውስጥ ሰላም እንዲመጣ ምንም አይነት ጥረት እያደረገ አይደለም፡፡ ከሰላሙ ይልቅ በትናንሽ አጀንዳዎች ከሰ/ት/ቤቱ ጋር መጣላት የሁልጊዜው ጸባዩ አድርጎታል እንግዲህ ከሊቀጳጳስ በላይ ማን አለ ?? እንዴት የበላይ አካል መመርያ እና ትእዛዝ አይፈጸምም ?? ለዚያውም የጳጳስ....በእውነት ምን አይነት ዘመን ላይ ደረስን?? ጳጳስ ጊዜ ወስዶ የጻፈው ቀርቶ የተናገረው እንኳ ታላቅ ኃይል አላት ፡፡ እንግዲህ ብጹእነታቸው ከአንዴም ሁለት ጊዜ ደብዳቤ አወረዱ ... መድኃኔዓለም እኮ ፍቃዱን ከምናውቅባቸው በርካታ መንገዶች አንዱ በብጹአን አበው ሊቃነ ጳጳስት ላይ አድሮ ነው አስተዳደር የሊቀጳጳስን መመርያ ካላከበረ ከአስተዳደሩ በታች ያሉት አካላት አስተዳደሩን እንዴት ያከብሩታል?? እሱ የበላዩን ሲያከብር ከስሩ ያሉት ደግሞ እሱን ያከብሩታል፡፡

የስደትና የመመለስ ታሪክ የሚገልጽ፤ ስብከት ለ15 ደቂቃ ካሰሙ በኋላ በስደት ሀገር ሲዘመር የነበረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ መዝሙር ተዘመረ፡፡ በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ የቡራኬ ጸሎት አድርገው ናዝዘው፣ ሠርሆተ ሕዝብ ካደረጉ በኋላ፣ ታቦቱ ወጥቶ ሥርዓተ ዑደት ተደርጐ የበዓሉ ፍጻሜ ሆነ፡፡ ፠ የቤተ ክርስቲያኑ (የገዳሙ) ቅዱሳት ስዕላት፤ ቤተ ክርስቲያኑ ተመርቆ አገልግሎት ከጀመረ ከ8 ዓመታት በኋላ በውጭ ሀገር ሰዓሊ ከ1950 ዓ.ም እስከ 1954 ዓ.ም. በነበረው ጊዜ የተሣሉ ናቸው፡፡ ፠ ገዳሙ እንደታላላቅ ገዳማት ማኅሌት አይቆምበትም የከበሮና የጸናጽል ድምፅም አይሰማበትም፡፡ ታቦቱ የሚነግሠውም በዓመት አንዴ ሚያዝያ 27ት ብቻ ነው፡፡ #የገዳሙ_መተዳደሪያ፤ ፠ ገዳሙ በተመሠረተበት ጊዜ ራሱን እንዲችል ለማድረግ አባ ሃና በገንዘብና ከግል ርስታቸው 1 ጋሻ መሬት በመስጠት እንዲረዳበት ሰጥተዋል፡፡ ንጉሣውያን ቤተሰቦችም አክሲዬን በመግዛት ይህን ገዳም ረድተዋል፡፡ ገዳሙ ራሱ የካህናት ኑሮ እንዲሻሻል ለማድረግ የሥጋጃ ሥራ በመክፈል ጥረት አድርጓል፡፡ ፠ ገና ከመሠረቱ አንስቶ ልዩ የሚያደርገው አገልግሎቱ በአብዛኛው በአማርኛ ቋንቋ መከናወኑ ነው፡፡ እንዲሁም የማታ ስብከት መርሐ ግብር በማዘጋጀት በቀዳሚነት የሚጠቀስና ዛሬም ድረስ ተጠናክሮ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ፠ በሰሙነ ሕማማት የሚካሄደው አጠቃላይ መርሐ ግብር (በተለይም መልክአ ሕማማቱ እንደ ዋልድባ ገዳም ሰሙኑን በአራራይ ዜማ መባሉ) በብዙዎች ላይ ትዝታን የሚያመጣ ነው፡፡ ፠ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ባለቤት ነው በቤተክርስቲያኑ #ተምሮ_ማስተማር_ሰንበት_ትምህርት_ቤት (ማኅበር) ፠ ተምሮ ማስተማር በኢትዮጵያ ቀደምት ሰንበት ትምህርት ቤት ነው፡፡ ፠ ሰንበት ትምህርት ቤቱን የሚመራው ሰብሳቢው ከገዳሙ የሚወከል ነው፡፡ ፠ በአሁን ወቅት ከሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተለየ መልኩ መስማት ለተሳናቸው ትምህርት ያስተምራል፡፡ ፠ በሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤቶች ከተለመደው የተከታታይ ትምህርት የተለያ የአብነት ትምህርት ቤትን መሠረት ያደረገ ሥርዐተ ትምህርትና ትምህርት ይሰጣል፡፡ ፠ ዓይነ ሥውራንን ታሳቢ ያደረገና በብሬል የተዘጋጁ መጻሕፍትን ጭምር የያዘ የተደራጀ ቤተ መጻሕፍት አለ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ