es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 378 suscriptores, ocupando la posición 5 573 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 194 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 378 suscriptores.

Según los últimos datos del 06 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 32, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.44%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 449 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 461 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 07 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 378
Suscriptores
-424 horas
-257 días
+3230 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ለአምላካችንና ፈጣሪያችን ቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ገዳማትና አድባራት ዐበይቶቹ (እናንተም የምታውቋቸውንና በአ
+4
እንኳን ለአምላካችንና ፈጣሪያችን ቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ገዳማትና አድባራት ዐበይቶቹ (እናንተም የምታውቋቸውንና በአቅራቢያችሁ ያሉትንከነፎቷቸው ጨምሩበት) ፠ ኦፍና አማኑኤል፤ መርሐ ቤቴ፥ አለም ከተማ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ጥንታዊ ቤ.ክ. ፠ ኤነር አማኑኤል፤ ምድረ ጕራጌ፤ እጅግ በጣም ጥንታዊ ገዳም ፠ ደብረ መንክራት በጎል ሰከበ ሚጣቅ ቅዱስ አማኑኤል፤ ከደብረ ብርሃንና አንኮበር መሃል ላይ የሚገኝ፤ በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የተመሠረተ፤ እጅጉን በጣም ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበትና የቅዱሳን መናኸሪያ የኾነ፡፡ ፠ ጫገል ቅዱስ አማኑኤል /በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከሚተዳደሩ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ/ ፠ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፣ አዲስ አበባ፤ መርካቶ መሳለሚያ ፠ ባሶ ወረዳ ጣፎ ደብረ ሰላም ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን፤ ከጢያ ከተማ ወደ አጠገብ የሚገኝ፡፡

* መድኀኔዓለም ክርስቶስ በቀራንዮ ስቊል፤ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም ድንግል፤ እስመ ኄር አልቦ እንበሌከ ቃል፡፡ ** በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው መድኀኔ ዓለም፤ ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማ
* መድኀኔዓለም ክርስቶስ በቀራንዮ ስቊል፤ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም ድንግል፤ እስመ ኄር አልቦ እንበሌከ ቃል፡፡ ** በቀራንዮ አደባባይ የተሰቀልከው መድኀኔ ዓለም፤ ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ምሬሃለሁ፥ ይቅር ብየሃለሁ በለኝ፤ ከአንተ በቀር ቸር ፥ ይቅር ባይ የለምና። ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#_ግንቦት_26_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ልደታቸው_ነው፡፡ በመብረቅ፣ በቸነፈር፣ በረሃብ፣ በወረርሽኝ፣ በእሳት ቃጠሎ ላይ ቃል ኪዳን የተሰጣቸውን የእኒህን ጻድቅ #ታሪካቸውንና_መልክአቸውን_እንሆ ብለናል፡፡ ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤ ፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤ ፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ፨ ፠በመራ ውዕይ (ሸዋ ፥ ቡልጋ) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክና ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መንና ነበር፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡ ለአብነትም፤ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤ በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤ በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤ ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤ በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርል፤ ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤ በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡ የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡ "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" የተባለለት ታላቅ አባት ነው፡፡ ፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡ *የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡ ፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው:: "*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" "በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት::  ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ ፩ኛ. #መብረቅ፣ ፪ኛ. #ቸነፈር፣ ፫ኛ. #ረሃብ፣ ፬ኛ. #ወረርሽኝ፣ ፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) #ሰላም_ለጽንሰትከ_እማኅፀነ_ቅድስት_ዮስቴና፤ #በብሥራተ_ጻድቅ_ባሕታዊ_ሠናየ_ዜና፡፡ #ሀብተማርያም_ጴጥሮስ_ሐዋርያ_ወልደ_ዮና፤ #መሐረኒ_ምግባረ_ጽድቅ_ወጸግወኒ_ልቡና፤ #አፍቅሮ_ቢጽ_እኅሥሥ_ዘምስለ_ፍጽመት_ትሕትና፡፡ ፎቶ ላይ የሚታዩት ገዳሞቹ፤ ፨ ብሔረ ብፁዓን ደበረ ይሰበይ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ ፨ ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ገዳም፤ አዲስ አበባ ከዊንጌት ትምህርት ቤት አጠገብ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

አስደሳች ዜና፤ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች እንዲሁም ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ፤ #ፈለገ_ጥበብ_የቴሌቪዥን_መርሐ_ግብር በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኮቪድ - 19ን ምክንያት ሁሉም
አስደሳች ዜና፤ ለሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች እንዲሁም ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ፤ #ፈለገ_ጥበብ_የቴሌቪዥን_መርሐ_ግብር በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኮቪድ - 19ን ምክንያት ሁሉም በያለበት ቃለ እግዚአብሔርን ማግኘት ይችል ዘንድ በመላው ዓለም ለሚገኙ የሰንበት ት/ቤት አባላትና ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ በአዲሱ ሥርዐተ ትምህርት መሠረት ዘወትር ቅዳሜ ረፋድ ጀምሮ በEOTC TV ስርጭቱን ጀምሯል፡፡ በመሆኑም በያላችሁበት ሆናችሁ ትምህርቱን እንድትከታተሉ በደስታ እናስታውቃለን፡፡ መርሐ ግብሮቹ፤ የሕፃናትና ታዳጊ፤ ቅዳሜ ከ5-6 ሰዐት ** የታዳጊና ወጣቶች፤ እሑድ ከ9-12 ሰዐት ረድኤተ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። /ምንጭ፤ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት/

አንድን አባት ሰዎች መጡና "ዘወትር ጸሎት በማድረግህ በሕይወትህ ላይ የጨመረልኽን ነገር ንገረን?" አሉት:: ** እርሱ ግን "ጸሎት በማድረጌ ከጨመርኩት ይልቅ የቀነስኹት ይበዛልና እርሱን ልንገራችኹ
አንድን አባት ሰዎች መጡና "ዘወትር ጸሎት በማድረግህ በሕይወትህ ላይ የጨመረልኽን ነገር ንገረን?" አሉት:: ** እርሱ ግን "ጸሎት በማድረጌ ከጨመርኩት ይልቅ የቀነስኹት ይበዛልና እርሱን ልንገራችኹ፡፡ ጸሎት በማድረጌ ከሕይወቴ ውስጥ ጭንቀት፣ ፍርኃት፣ ተስፋ መቁረጥና ቁጡነትን ቀንሻለኹ" አላቸው፡፡

** አርእይኒ ገጸ ዚአኪ ማርያም ምዕረ፤ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ፡፡ #ማርያም_ሆይ_ለሌላ_የማልነግረው_ነገርን_እነግርሽ_ዘንድ_አንድ_ጊዜ_ፊትሽን_ግለጪልኝ_፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤
** አርእይኒ ገጸ ዚአኪ ማርያም ምዕረ፤ ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ፡፡ #ማርያም_ሆይ_ለሌላ_የማልነግረው_ነገርን_እነግርሽ_ዘንድ_አንድ_ጊዜ_ፊትሽን_ግለጪልኝ_፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

እንኳን አደረሳችሁ፡፡ #ግንቦት_21_ደብረ_ምጥማቅ_ማርያም_የምናከብርበት_ምክንያቱና_ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_21፡፡ ግብጻውያን ክርስቲያኖች ከግንቦት 21 እስከ 25 የእመቤታችንን በዓል (ምሰሶ አቁመው፥ አጎበር ጥለው፥ ድንኳን ተክለው፥ ድባብ ዘርግተው ያከብራሉ፤ እመቤታችንም ከቅዱሳን ጋር በመገኘት ትባርካቸዋለች፡፡) እነዚህ 5ት ቀናትም ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት 5ቱን ከተ.ቊ 25ኛ እስከ 29ኛ ያለውን ይይዛሉ፡፡ እነርሱም፤ ፠25ኛና 26ኛ፤ ግንቦት 21 ና 22 ቀን በግብጽ ሃገር ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቤተክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምዕመናን በግልጽ የታየችበት ነው፡፡ ፠27ኛ፤ ግንቦት 23 ቀን ደብረ ምጥማቅ በተባለች ቦታ የታየችበት ነው፡፡ ፠28ኛ፤ ግንቦት 24 ተሰዳ ግብጽ የገባችበት ነው፤ /ኢሣ.1 9፥11፣ ማቴ.2፥13-15/ ፠29ኛ፤ ግንቦት 25 ልጇ መድኀኔዓለም ክርስቶስ የደረቁ በትሮችን ተክሎ ያለመለመበት በዓል ነው፡፡ እነዚህ ከላይ ያየናቸውን የደብረ ምጥማቅ በዓላት (ከግንቦት 21-25) በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን በግብፅ ተነሥቶ የነበረው ንጉሥ የግብጽ ክርስቲያኖች በዓሉን እንዳያከብሩ በመከልከሉ፤ ኢትዮጵያውያንም ይህንን በዓል ለማክበር ወደ ግብፅ ይሄዱ ነበርና፤ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ለመጽናኛ እንዲሆን በሃገራችን የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያምን መሠረተ፤ እመቤታችንም ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠችው፤ ይኸው ቃል ኪዳኗ ሳይታጠፍ በጻድቃኔ ማርያም ዛሬ ድረስ ስፍር ቊጥር የሌለው ብዙ ተዓምራትና የምሕረት ሥራ የሚፈጸምባት ቅዱስ ቦታ ኾና ትገኛለች፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ በሃገራችን ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅ ክብረ በዓል በስሟ ተሰይሞ በዋነኛነት!!! (በዋነኛነት!!!)የሚከበርባቸው ቦታዎች የሚከተሉት ናቸው፤ *1ኛ) #ደብረ_ምጥማቅ_ጻድቃኔ_ማርያም_ገዳም /ሰሜን ሸዋ/ *2ኛ) ሐመረ ብርሃን ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን /ጎንደር ከተማ/ *3ኛ) ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም /አዲስ አበባ/ (ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው በ Facebook, Telegram, Email, Viber, Xender, Bluetooth በማድረስ ይተባበሩ፡፡) ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጻድቁ_አቡነ_እንድርያስ_ዘመርሐ_ቤቴ_ወዘዋሻ_እንድርያስ_ወዘመቀጠዋ_ጉና_ቅዱስ_ሚካኤል ✍️ ጻድቁ አቡነ እንድርያስ ትውልዳቸዉ ሸዋ ክፍለ ሀገር መርሐ ቤቴ ሲሆን፤ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደቀ መዝሙር ናቸው፡፡ ✍️ አቡነ እንድርያስ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት የተገናኙት በታላቁ ገዳም በደብረ በንኮል ሲሆን፤ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር በሁለተኛው የኢየሩሳሌም ጉዟቸው አብረው የተጓዙ ናቸው፡፡ ✍️ በአፄ ይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጳጳስ ሆነው ወንጌልን ለመስበክና ክርስትናን ለማዳረስ ሸዋ ደብረ ሊባኖስ ላይ ሆነው በመላ ኢትዮጵያ 13 ሐዋርያትን መርጠው ለስብከተ ወንጌል ከላኳቸዉ አንዱ ጻድቁ አቡነ እንድርያስ ናቸው፤ ✍️ አቡነ እንድርያስ የደረሳቸው ሃገረ ስብከትም ምድረ እንፍራንዝ /የአሁኑ ሊቦ ከምከም ወረዳ አካባቢ/ ሲሆን ከሸዋ ተነሥተው ታቦተ ኢየሱስን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፈቃድ ይዘው መጥተዋል፡፡ ✍️ ጻድቁም በአካባቢው እንደ ደረሱ፤ ወንጌልን እየሰበኩ በአካባቢው የነበሩትን ሰዎች አስተምረው አሳምነዉ አቈርበዋቸዋል፡፡ ከዚህ ትልቅና ታሪካዊ ዋሻ ከመድረሳቸዉ በፊት ከዚህ ዋሻ በስተምዕራብ በኩል ካንዲት ትንሽ ዋሻ ገብተዉ ጸሎት ሲጸልዩ ረዳታቸዉን የእግዚአብሔር መንፈስ ከዚህ ዋሻ አለ ይለኛል ስለዚህ አንተ ከዚህ ውጣና ዋሻውን ፈልግ ብለዉ ሰደዱት፡፡ ረድአቸው አቡነ ቶማስ ዘጣና ብርጊዳም ወጥቶ ሲፈልግ ይህን ትልቅ ዋሻ ተመለከተ ቀረብ ሲል እዚህ ዋሻ ወተት እየተደፋለት የሚኖረውን ታላቅ ዘንዶ ሲመለከት በድንጋጤ እየሮጠ ለጻድቁ ከአቡነ እንድርያስ ሄዶ ነገራቸዉ፡፡ ✍️ አቡነ እንድርያስም በእግዚአብሔር ኀይል እናሸንፈዋለን ብለው ከዚህ ዋሻ ደረሱ እነዚያ ዘንዶዎችም ሊበሏቸዉ አፉቸውን ሲከፍቱ አቡነ እንድርያስ ሊባርኩ መስቀላቸውን ሲያነሡ መስቀላቸው ወድቆ የቀኝ ክንፉ ተሰበረባቸዉ፤ በዚህ ሰዐት ቢጸልዩ የእግዚአብሔር መልአክ አይዞህ ጽንዓ ብሎ መስቀላቸዉን እንደነበረ አድርጎ ሰርቶ ሰጣቸው፤ አቡኑም በመስቀላቸዉ ዘንዶዎቹን ቢባርኳቸው አንደኛው ዘንዶዉ ከዋሻዉ ወጥቶ ወደ ምዕራብ በኩል ሔዶ ግራርጌ #ጉባይ ከተባለ ቦታ ተጠቅልሎ ተኛ፤ ሌላኛው ግን እስከ ዛሬ ድረስ የደረሰበት ባይታወቅም ወደ ዋሻው ውስጠኛ ክፍል ገብቶ ቀረ፡፡ ✍️ አቡነ እንድርያስ ዘንዶዎቹን ያስወጡት ግንቦት 20/1246 ዓ.ም. ነው፡፡ ✍️ ወደ ገዳሙ በተአምራት አብረዋቸው የመጡ አራት በግምት አንድ ሜትር ቁመት ያላቸውና ከ20 እስከ አሥራ አምስት ሳንቲ ሜትር ስፋት ያላቸው ድንጋዮች መካከል ሁለቱ በደወልነት አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ ሲደወሉ ወፍራምና ቀጭን ድምጽ ስለሚያወጡ የወንድና የሴት ደወሎች ይባላሉ፡፡ በአገልግሎት ወቅት ዋሻው ድምፅ እያስተጋባ (ቀበሌ ሆኖ) ለጸሎት ቢያስቸግራቸው አቡነ እንድርያስ ዋሻውን ገስጸውት እስከ ዛሬ ድረስ ዋሻው ምንም ዓይነት ድምፅ አያስተጋባም፡፡ ✍️ አቡነ እንድርያስ ለቤተክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳት ለማምጣት #እብናት_መቀጠዋ_መልዛ_ ጉና_ቅዱስ_ሚካኤል ከተባለ ቦታ ላይ ሲደርሱ ጳጕሜን 3 ቀን ታመው እዛው አረፉ፡፡ ለአቡነ እንድርያስ ከዕረፍታቸው በፊት እግዚአብሔር መላእክትን፥ ሰማዕታትን፤ ቅዱሳንን ይዞ ወርዶ ቃል ኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ ነዳያንን ያበላ ያጠጣ እስከ ሰባት ትውልድ እምርልሀለሁ፤ ስምህ በተጠራበት ሁሉ ከሰዎች ላይ አጋንንት ይውጡልህ፥ ድውያን ይፈወሱልህ ለምጽ፣ ቁስል ይፈወስልህ ብሎ ቃልኪዳን እንደገባላቸዉ ወዲያውኑ እዚህ ቦታ ላይ ታመዉ አረፉ፡፡ በተሰጣቸው ቃል ኪዳንም ዛሬ ድረስ ከገዳሙ በስተደቡብ በሚገኘውና በሚፈልቀው ጠበላቸው፤ በገድላቸው፤ በመስቀላቸው በተለይም ከካንሰር፣ ከኪንታሮትና ከቁስል የሚድነው ሕመምተኛ ኍልቈ መሣፍርት የለውም፤ ለመቊጠርም አስቸጋሪ ነው፡፡ በየዕለቱ እንኳን ከ1 ሺህ በላይ ምዕመናን ይጠመቃል፡፡ ✍️ ቅዱስ ሥጋቸውን የመቀጠዋ ሕዝቦችና የዋሻ እንድርያስ ሕዝቦች እኔ እወስድ ፥ እኔ እወስድ እያሉ ሲጣሉ ቅዱስ ሥጋቸዉ እንደ ጥቁር ድንጋይ ከብዶ የማይነሳ ሆነ፤ በዚህ ምክንያት እጣ ሲጥሉ ለዋሻ እንድርያስ ሰዎች ደረሳቸው፡፡ ሥጋቸውን ሲያነሱትም እንደ ገለባ ቀለላቸዉና አምጥተው በዋሻው ውስጥ በክብር በሳጥን አስቀመጡት፡፡ #በገዳሙ_ውስጥ_ከሚገኙ_ድንቃ_ድንቅ_ቅርሶች_መካከል_እጅግ_ጥቂቶቹ፤ ፠ ዘንዶው ወተትና የመሥዋዕት ደም ይጠጣባቸው የነበሩ ሁለት የዕንጨት ገበቴዎች፤ በቁመቷ ልክ ከእንጨት ተፈልፍሎ በተሠራ ገንዳ ውስጥ ገብታ የገንዳውን ግራና ቀኝ በደረቷ አቅጣጫ በመብሳት በጠፍር በማሰር ትጸልይበት የነበረው #የቅድስት_ዜና_ማርያም የእንጨት መጸለያ ገንዳ፤ የዚህችን ቅድስት መታሰቢያ ቅዱስ ላሊበላ በደሪጣ (ከም ከም ወረዳ ከአዲስ ዘመን ከተማ 20 ኪ.ሜ) የዋሻ ቤተ መቅደስ በመፈልፈል የሠራላት ሲሆን፤ ኋላ ደግሞ አፄ ይስሐቅ በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይህንኑ ቦታ በስሟ ገድሞታል፡፡ እርሷም ያረፈችው በግንቦት 20 ቀን ነው፡፡ ፠ በእንጨት የተሠራ የኦሪት መሠዊያ፤ ፠ የመሥዋዕተ በግዕ ሥጋ ማስቀመጫ፤ የደሙ ማኖሪያ፡ ፠ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ለገዳሙ ከሰጧቸው 6 ነጋሪቶች መካከል ሁለቱ፤ ፠ ከእንጨት የተሠራ ቃጭል፤ ፠ በዋሻው ግድግዳ ላይ የተለያዩ ስዕላዊ ምስሎች፤ ፠ ብዛት ያላቸውና በርካታ ዘመንን ያስቈጠሩ አጽመ ቅዱሳን አበው ወእማት ይገኛሉ፡፡ ከአጽሞቹ መካከል አንዱ ሙሉ ለሙሉ ሳይፈርስ ከራስ ቅሉ እስከ እግር ጥፍሩ በዘመናዊ ሳጥን ተደርጎ ከላይ በመስታወት ታሽጎ ይታያል፡፡ ፠ አእምሮን የሚመስጥና አብዛኛውን በወይራና በጽድና በሌሎች ሃገር በቀል ዛፎች የተከበበ ጥብቅ ደን ይገኛል፡፡ ፠ ሰው መሰል ቅርፅ ያላቸው ጣዖት ማምለኪያዎች፤ … ወዘተ ለታሪክ ተቀርምጠዋል፡፡ የገዳሙ አድራሻ ገዳም የሚገኘው በደቡብ ጎንደር ሊቦ ከምከም ወረዳ፤ ከባሕር ዳር ወደ ጎንደር በሚወስደዉ መንገድ ከአዲስ ዘመን ከተማ 7 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኘው ጣራ ገዳም (እመቤታችን በስደቷ ወቅት ያረፈችበት፤ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የገደሙትና በርካታ ቅዱሳን የፈለቁበት) ላይ ወርደው በስተምዕራብ በኩል በእግር 40 ደቂቃ ተጕዘው ሲሆን ከአጠገቡ ጥነታዊው ዋሻ ተክ ሃይማኖት ገዳም ያገኛል፡፡ የዚህ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ዓመታዊ በዓሉ (አቡነ እንድርያስ ወደ ገዳሙ የገቡበትና ቅድስት ዜና ማርያ ያረፈችበትን) በየመቱ ግንቦት 20 ብዙ ሺህ ምዕመናን በተገኙበት ይከበራል፡፡ ምንጭ፤ * የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በ1999 ዓ.ም. ና በመጋቢት 19-20/2012 ዓ.ም. በቦታው ድረስ ሄዶ ከአባቶች ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ * Moges begena zemickael/መኀልየ መኃልይ በገና ማሰልጠኛ ተቋም/ * አቡነ እንድርያስ ገዳም/አቡነ እንድርያስ ዋሻ፣ ማኅበረ ቅዱሳን ድኅረ ገጽ፤ https://eotcmk.org/a/አቡነ-እንድርያስ-ገዳምአቡነ-እንድርያስ/፣ በእንዳለ ደምስስ የአባታችን የጻድቁ የአቡነ እንድርያስ በረከት ረድኤት ይደርብን፤ በቃል ኪዳናቸው ከደዌ ሥጋ ወነፍስ ይፈውሰን፤ አሜን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

/ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/፤ እስከዛሬ ድረስ፤ ✿ በጠበላቸውና በመስቀላቸው ከካንሰርና ከኪንታሮት በሽታ እልፍ አእላፋትን የሚፈውሱት፤ ✿ ወፍራምና ቀጭን ድምጽ የሚያወጡና ድምፃቸው የሚመስጥ 2ት የድንጋይ ደወሎችን ወደ ዋሻው ያመጡት፤፡ ✿ ከእንጨት የተሠራ ቃጭል የሚገኝበት፤ ✿ ዋሻው ድምፅ እንዳያስተጋባ በገዘቱት መሠረት እስከዛሬ ድረስ ድምፅ የማያስተጋባውን ዋሻ የባረኩት ጻድቁ አቡነ እንድርያስ ግንቦት 20 ክብረ በዓላቸው ነው፡፡ #ዋሻ_አቡነ_እንድርያስ ፠ የአቡነ እንድርያስ ዋሻ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ከክርስቶስ ልደት በፊትበ889ዓ/ዓ ሲሆን፤ በአፄ ባዚን ዘመን ዳጎን የተባለ የእንጨት የሰው ምስል ሰርተው ያመልኩበት ነበር፡፡ ይህም የአብርሃም አባት ታራ ይሰራው የነበረውን ባህል ይዘዉ የጣኦት ማምለኪያ አድርገውት ነበር፡፡ በዚህ ዋሻ ባልና ሚስት ዘንዶወች ነበሩ ለእነዚህ ዘንዶዎችም የእንጨት ገንዳ ተጠርቦ ወተትና የመስዋዕት ደም እየተደፋላቸው ዘንዶዎቹ ይጠጡ ነበር፤ ይህ ገንዳ አሁንም በዋሻዉ ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህን ዋሻ እስከ 450 ዓ.ም. ድረስ ጣኦት እያመለኩበት ዋሻዉን ከሦስት ክፍል ከፍለውታል፤ ቀኝና ግራውን ለእቃ ቤት፣ መሀሉን ለማምለኪያ አደረጉት፡፡ የጣኦት አምልኮት በኢትዮጵያ እየተዳከመ በሚሔድበት ዘመን የታቦተ ጽዮንና የታቦታተ ሕግ በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ሲሔድ ጣኦቱ ወደቀ ጠፋ፡፡ ፠ በዘመኑ ጌዴዎን የተባለዉ ፈላስፋ ጠበብተኞችን ወደዚህ ዋሻ ላካቸው፤ እነዚህ ጥበበኞችም ዋሻውን በሚገባ አደራጁት ከመቅደሱ ውስጥ ሁለት የድንጋይ ወጋግራዎች አራት ገጽ ጠርበው አዘጋጁ፤ የድንጋዩን ባጥ እንደ ቅዱስ ላሊበላ ጣራውን ጠርበው፤ ቅድስትና መቅደሱን ሠሩት፤ ዋሻው የይምርሐነ ክርስቶስን ይመስላል፡፡ በዚህ ዋሻም ታቦተ ቅዱስ ሚካኤልን አምጥተዉ በመስዋዕተ በግዕ ለ44 አመታት በዚሁ ዋሻ ተገለገሉበት፡፡ ፠ ዋሻው የውስጥ ስፋቱ 30 በ 40 ሜትር ሲሆን የዋሻው የውስጥ ክፍል ከወለል እስከ ጣራ 20 ሜትር ቁመት አለው፡፡ አራት በሮች ሲኖሩት እያንዳንዳቸው ከአንድ ወጥ እንጨት ተጠርበው የተሠሩ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ደረጃና የበሩ መቃን በጣና ደሴት ውስጥ ከሚገኙት ከደብረ ሲና ማርያም፤ ከደብረ ገሊላ ኢየሱስ አቡነ ዘካርያስ ገዳም፤ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም፤ . . . ጋር ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ገዳሙ ምንም ዓይነት እድሳት ያልተደረገለት ሲሆን ጥንታዊነቱን ጠብቆ የሚገኝ የዋሻ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ የደጃፉ ግንብ፣ የበሮቹና መስኮቶቹ አሰራርም ጥንታዊነቱን ብቻ ሳይሆን የቀደምት የሀገራችንን ኪነ ህንፃ ብቃት ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል፡፡ ፠ የዋሻው በሩን አልፈው ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ሰፊውን ቅኔ ማኅሌት ያገኛሉ፤ ከፊት ለፊት ቅድስትና መቅደሱ፤ እንዲሁም በትልቁ የተሳሉ የአቡነ እንድርያስ ስዕሎች ጎልተው ይታያሉ፡፡ በቤተ መቅደሱ ግራና ቀኝ ሰልፋና ደፈር በተባሉ ሰዎች በጥርብ ድንጋይ የተከለሉ ቦታዎች አሉ፡፡ /ሰልፋና ደፈር የዘንዶዎቹ ቀላቢዎች/ እንደነበሩ ገድለ አቡነ እንድርያስን በመጥቀስ አባቶች ይናገራሉ፡፡ ፠ ይህ ዋሻ ወደ ዋሻ ዜና ማርያምና ወይን ዋሻ ተክለ ሃይማኖት የሚያገናኝ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ርዝመቱ 14 (30-40) ኪ.ሜ የሚደርስ ፤ ስፋቱ 3 ሜትር ደግሞ ወደ ምስራቅና ወደ ምዕራብ 60 ሜትር እንዳለው አባቶች ይናገራሉ፡፡ ፠ የኢየሱስ፤ የቅዱስ ሚካኤልና የአቡነ እንድርያስ ታቦታት፤ እንዲሁም የአቡነ እንድርያስ መቃብር በዚሁ ዋሻ ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ፠ የክርስትና ሃይማኖት በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ሲሔድ በአፄ ይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጳጳስ ሆነው ለመላዋ ኢትዮጵያ ወንጌልን ለመስበክና ክርስትናን ለማዳረስ ሸዋ ደብረ ሊባኖስ ላይ ሆነው 13 ሐዋርያትን መርጠው ለስብከተ ወንጌል ከላኳቸዉ አንዱ ጻድቁ አቡነ እንድርያስ ናቸዉ፡፡

#ዕርገተ_እግዚእነ እንኳን ለጌታችን በዓለ ዕርገት፤ ኀሙስ ግንቦት 20/2012 ዓ.ም. አደረሳችሁ፥ አደረሰን፤ በዓሉን የሚመለከት ጽሑፍና በሁሉም አድባራትና ገዳማት የሚቆመውን ሥርዐተ ማኅሌቱን እንደተለመደው አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም ንባብ፤ መልካም የምስጋና ማኅሌት፡፡ ‹‹አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው፤ ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡›› እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ዮሐ.3፥13 ✍️ የሰውን ልጅ በመውደዱ ልዑል ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ ከሰማይ ወረደ፥ ሥጋ ለበሰ፥ በምድር ላይ ተመላለሰ፥ ምድርን በኪደተ እግሩ ቀደሰ፥ ድውያንን ፈወሰ፡፡ ✍️ ፍጹም ሰው እንደ መሆኑ ተራበ፥ ተጠማ፤ ፍጹም አምላክ መሆኑንም ያስረዳ ዘንድ አምስት ገበያ ሕዝብ በአምስት እንጀራ በሁለት ዓሣ አጠገበ ማቴ.14፥19፡፡ ✍️ መምህረ ትሕትና ነውና ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በዚህ ዓለም ኖረ ለሐዋርያት ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን አስተማረ፤ ትምህርት በሚገባ ከተረዳለት በኋላ ለድኅነተ ዓለም በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ተሰቀለ፡፡#ወገብረ_መድኀኒተ_በማዕከለ_ምድር_በምድር_መካከል_መድኀኒትን_አደረገ_እንዲል _መዝ.73፥12 ✍️ ነቢያት እንደተናገሩ በሞቱ ዓለምን አድኖ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ብርሃነ መለኮቱን ገልጾ ተነሣ፡፡ የተተነበየውን ትንቢት ፈጽሞ ተነሣ፡፡ ✍️ በሞቱ ሞታችንን ሻረልን፤ ‹‹በሞቱ ሞትን አጠፋው›› እንዲል መጽሐፈ ኪዳን፡፡ ሕንፃ መነኰሳት ‹እርሱ በሁሉ ምሉዕ ሲሆን በመቃብር ለመቀበር ዮሴፍ ኒቆዲሞስ ገንዘውት ታየ፡፡ ከመሬት ውስጥ በመቀበሩም ሙስና መቃብርን አጠፋ፤ ከሥሩም ነቀለው ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን መጀመሪያ ለማርያም መግደላዊት ገለጸ ማር.16፥9፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ትንሣኤው ሲመሰክር ‹‹ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፤ ተቀበረም፤ መጽሐፍ እንደሚል፤ በሦስተኛው ቀን ተነሣ፡፡ ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፡፡ ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ›› 1ቆሮ.15፥3-8 ብሎ ክርስቶስ ትንሣኤውን ለተከታዮቹ በሙሉ የገለጠ መሆኑን መስክሯል፡፡ ✍️ የሚያምኑ ፈሪሳውያንም ‹‹ትንሣኤው ምትሐት ነው›› እንዳይሉ እየታየ እያስተማረ እስከ 40 ቀን ድረስ መቆየቱን ይገልጽልና፡፡ በዚህም የአርባ ቀን ከትንሣኤ በኋላ ቆይታው ሦስት ቀን ጉባኤ አድርጎ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ ቅዱስ ወንጌል ይነግረናል፡፡ ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሲገለጥላቸው ይህ ሦስተኛ ጊዜ ነበረ እንዲል ዮሐ.21፥14 ይህንም ሊቃውንት አባቶቻችን፡- 1ኛ) *የትንሣኤ 2ኛ) *የአግብኦተ ግብር /ዳግም ትንሣኤ/ 3ኛ) *የጥብርያዶስ፡፡ በዚህ 40 ቀን ቆይታ መጽሐፈ ኪዳንን ለደቀ መዛሙርቱ አስተምሯል፡፡ ✍️ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም ዕርገቱን ለመናገር ከሰማየ ሰማያት መውረዱን አስቀድሞ ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ማንም ወደ ሰማይ የወጣ የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው ብሎ ከዕርገቱ በኋላ በየማነ አብ፥ በዘባነ ኪሩብ ፥ ወደ ሰማይ የወጣ ከእርሱ በቀር ሌላ እንደሌለ አስረግጦ ነገረን፡፡ ሲጀምር ከሰማይ መውረዱን ማስቀደሙ ወረደ ብሎ ዐረገ ለማለት ይመቻል፡፡ ተጸነሰ ተወለደ ለማለት ጥንቱ ከሰማያት ወረደ ማለት እንደሆነ ሁሉ፤ ‹‹ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ ተነሣ›› ለማለት ‹‹ጥንቱ፤ ተጸነሰ፥ ተወለደ፥ አደገ፥ ተመላለሰ፥ ሠላሳ ዓመት ኖረ›› የሚለው ነው፡፡ ስለሆነም ቅዱስ ዮሐንስ ጠርዝና ጠርዙን ይዞ ተናገረ፡፡ ✍️ ‹‹ወረደ ዐረገ›› የሚሉት ሁለት ቃላት የዓለም ድኅነት መነሻና መድረሻ ናቸው፤ እነዚህን ሁለት ቃላት ስናይ በሁለቱ መካከል የተፈጸሙትን የአምላክ ሥራዎች ልብ ማለት ይገባል፡፡ ቤት በመሠረት ይጀመራል በጣሪያ ይፈጸማል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን የቤዛነት ሥራ ሲያስረዳ በዮሐ.1፥14 ‹‹ቃል ሥጋ ኮነ፤ቃል ሥጋ ሆነ›› ብሎ ጀምሯል፤ ይህንንም ቃል ‹‹ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም›› በማለት ሰው መሆኑን ብቻ ሳይሆን በአርያም የሚኖር መሆኑን አስተማረን፡፡ እንግዲህ ጌታችን ዕርገት እንዲሁ እንደ እንግዳ ደራሽ ፥ እንደ ውኃ ፈሳሽ አለመሆኑን ቀድሞ በነቢያት የተነገረ፤ ኋላም በሐዋርያት የተመሰከረ መሆኑን ማወቅ ያስፈለጋል፡፡ #የክርስቶስ_ዕርገት_በትንቢተ_ነቢያት ፠ ‹‹ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አደረገ ወረደም ጨለማ /ዲያብሎስ/ ከእግሩ በታች ነበር በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ በነፍሳትም ክንፍ በረረ፡፡›› መዝ.17፥9 ፠ ‹‹አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ ዐረገ መዝ.46፥5 ወደላይ ዐረግህ፥ ምርኮን ማረክህ ፥ ስጦታንም ለሰዎች ሰጠህ›› መዝ.67፥18፡፡ ፠ ‹‹ዘምሩ ለእግዚአብሔር ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ፤ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ›› መዝ.67፥33፡፡ #የክርስቶስ_ዕርገት_በትምህርተ_ሐዋርያት ፠ ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ፡፡ ማር.16፥19 ፠ ‹‹እስከ ቢታንያ አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡››ሉቃ.24፥50 ፠ ‹‹ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ ደመናም ከዐይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤ እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ እነሆ ነጫጭ ልብስ ለብሰው ሁለት ሰዎች /መላእክት/ በአጠገባቸው ቆሙ ደግሞም ‹‹የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት ዳግመኛ ይመጣል፡፡›› አሏቸው›› ሐዋ.1፥9-12 በማለት ሐዋርያት የክርስቶስን ዕርገት ከመላእክት ጋር ሆነው እንደተመለከቱ ደስታውን እንደተካፈሉ ቅዱስ ሉቃስ ጽፎልናል፡፡ በትንሣኤው ነጭ ልብስ ለብሰው የታዩ መላእክት የደስታ ዘመን ነው ሲሉ በዕርገቱም ነጭ ልብስ ለብሰው የዕርገቱን የምሥራች ለሐዋርያት አብስረዋል፡፡ /ምንጭ፤ የቃል ትምህርትና በመምህር ምሥጢረ ሥሳሴ ማናየ/ የአምላካችን ቸርነቱ ረድኤቱ አይለየን፡፡ ፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

እስከዛሬ_ድረስ #በላስታ_ተራራ_ጭላዳ_እህል_እንዳይበላ_ለገዘቱት #በጎንደር_ከተማ_ጅብ_እንስሳቶችን_እንዳይበላ_ለገዘቱት፡፡ ለታላላቆቹ አባቶች ለአቡነ ዓቢየ እግዚእና ለአቡነ ዮሴፍ ዓመታዊ በዓል (ግንቦት 19) በሰላምና በጤና አደሳችሁ፡፡ /#በጻድቃን_ተዓምራት_ማድረግ_ለምትጠራጠሩ፤/ #ጻድቃን_ከበዓለ_ዕረፍታቸው_በኋላ_ዛሬም_ከማማለድም_አልፈው_በቃልኪዳናቸው_ተዓምራት_እንደሚያደርጉ_ኑና_እዩ_ተመልከቱ፡፡ ተዓምራትን ማየት ለምትፈልጉ ኹሉ ሂዳችሁ እዩ!!!!!)፡፡ ፠ ክብረ በዓላቸው ✍️ የአቡነ ዓቢየ እግዚእ በተንቤን መረታ ደብረ መድኃኒት፣ በጎንደር ከተማ ጥንታዊ በኾነው በዓቢየ እግዚእ ኪዳነምሕረት፣ በመቀሌ እንዳ ገብርኤል /እንዳ አቡነ ዓቢየ እግዚእ/፣ በአዲስ አበባ ሞጆ አካባቢ ባለው ቤ.ክ በድምት ይከበራል፡፡) እንዲሁም ✍️ (የአቡነ ዮሴፍ በላስታ ላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኘውና ወደ ላለበላ የሚጓዝ ኹሉ ሊያየው በሚችል በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘውና በኢትዮጵያ በከፍታ ከራስ ደጀን ተራራ ቀጥሎ በሚገኘው የዋሻ ገዳማቸው ይከበራል)፡፡ ሁለቱም ቅዱሳን አስካሁን ጊዜ ድረስ የሚታይ ባለ አስደናቂ የቃልኪዳን ተዓምራት አላቸው፤ አቡነ ዮሴፍ ከላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ገዳማቸው #ጭላዳ_እህል_ጠባቂ_ሳያሻው_እህል_እንዳይበላ_ገዝተውታል፤ አቡነ ዐቢየ እግዚእ ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ቦታ (ለምሳሌ በጎንደር ከተማ) አሁንም ድረስ #ጅብ_እንስሳቶችን_እንዳይበላ_ገዝተዋል፡፡ #አቡነ_ዮሴፍ_ዘእንጂፋቱ * በወሎ ላስታ ሰውንና ዝንጀሮን በቃል ኪዳን ያስተሳሰሩ #እስከዛሬ_ድረስ_ዝንጀሮ_እህል_እንዳይበላ_የገዘቱ፤ * እመቤታችን ዕጣን እየሰጠቻቸው፤ * ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑ (እንደ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባና አቡነ ዘርዓ ቡሩክ) ናቸው፤ * ወደ ደብረ ሐዊ በመሄድ ሱባዔ ገብተው ቅዱስ ያሬድን በተሰወረበት የተመለከቱ፤ * ገዳማቸው በላሊበላ በቅርበት አቡነ ዮሴፍ ተራራ ተብሎ በሚጠራ ተራራ ቦታ ላይ የሚገኝ የዋሻ ቤ.ክ አላቸው፡፡ #አባ_ዓቢየ_እግዚእ_፤ * አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ትግራይ ተንቤን (መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቻቸው ያፍቅረነ እግዚእ እና ጽርሐ ቅድሳት ይባላሉ፡፡ * አጥምቀው 'ዓቢየ እግዚእ' ሲሉ ስም ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ ሰላማ መተርጕመ መጻሕፍት ናቸው:: ትርጉሙም "በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው" ማለት ነው:: * በሕፃንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቁ፡፡ * ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኰስ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደብረ በንኮል ሔደው መንኵሰዋል፡፡ * በደብረ በንኰል ገዳም በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በኋላ ወደ ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያንን አግኝተዋል፤ በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን አፍርተዋል፡፡ * ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ፡፡ ከትግራይ እስከ ደንቢያ ሃገረ ስብከታቸው ነው:: * አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት ሲንቀሳቀሱ ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ፤ ቀኑ ነሐሴ 10 ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ፤ ጻድቁ ባካባቢው የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና "አምላከ ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ፤ ይህን ድንቅ ያዩ ከ1,000 በላይ አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል፤ ይህም ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር) ይከበራል:: * ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ፤ ያኔ ጐንደር በቀሃና አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች፤ ጻድቁ ቀን ቀን እየሰበኩ፥ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፤ በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ፥ እባብና መሰል አራዊት ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት፤ ይህንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ፤ በፍጹም ልባቸውም ስለ ሕዝቡ ለመኑ፡፡ የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ ‹‹በስምህ የተማጸኑ፥ በቃል ኪዳንህ ያመኑ፥ በምድር አራዊት አይሠለጥኑባቸውም፤ በሰማይም እሳትን አያዩም፤ ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም፡፡›› ብሏቸው አርጓል፡፡ ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ ገዳማቸው ተንቤን ተመልሰዋል፡፡ ዛሬም ድረስ ከብቶችን ጅብና መሰል አውሬ እየበላ የሚያስቸግራቸው ምዕመናን ገድላቸውን ሲያስነብቡ ይርቃሉ፡፡ * አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት በቅድስና ኑረው፥ 3 ሙታንን አስነስተው፥ ብዙ ድውያንን ፈውሰው፥ ብሔረ ብጹዓንን ጎብኝተው፥ የድኅነት ቃል ኪዳንም ተቀብለው፥ በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን አርፈዋል፡፡ ** አምላካችን በወዳጆቹ ምልጃ ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይሠውርልን፡፡ ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው በ Facebook, Email, Viber, Xender, Bluetooth በማድረስ ይተባበሩ፡፡ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡

#ፍትሕ_ለደብረ_ምሕረት በማኅበራዊ ድረ ገፃችን ላይ ፕሮፋይል በማድረግ ቅሬታችንን እናሰማ፡፡!!! ፠ ባለፈው ሳምንት ግንቦት 12 ለሙስሊም ወንድሞቻችን የተሰጠው 30,000 ካሬ መሬት በሕግ አግባብም ሆነ በሌሎች መመዘኛዎች ሕገወጥና ተቀባይነት የሌለው ነው፡፡ ለማሳየነት ያህልም ፠ * የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 712/2004 እና * ግንቦት 24 ቀን 2010 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሀይማኖት ተቋማት ለአምልኮ ማካሄጃ ቦታ አፈቃቀድ መመሪያ ቁጥር 1 /2010 * በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ቦታ ሊዝ ደንብ ቊጥር 49/2004 እንዲሁም * በከተማው አስተዳደር የከተማ ቦታ ሊዝ መመሪያ ቁጥር 11/2004 በተደነገጉት መሠረት፤ የመመርያው ዓላማ፤ የአምልኮ ማካሄጃ የቦታ ጥያቄዎችን ግልጽነት፤ ፍትሐዊነት እና ተጠያቂነትን ነው ይላል፡፡ ✍️ የተሰጠው ቦታ ዓላማውን የሳተ፤ በግልጽነትና በፍትሐዊነት ያልተደረገ፤ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል ስለገቡ በሚል ሰበብ እንጂ ሕግና መመሪያና ተከትሎ ያልተሠራ ነው፡፡ ፍትሐዊነት የሌለው ነው ስንልም፤ ቁጥሮች አይዋሹምና ነው፤ እስቲ እንመልከተው ከዚህ በፊት በነበረው ቈጠራ ኦርቶዶክሱ፤ ፫ ሚልዮን ፸፻፶ ሺ (3,750,000) ሙስሊሙ፤ ፰፻ ሺ (800,000) ሌሎች፤ ፬፻ ሺ (400,000) የአብያተ እምነቶች ስብጥር ስንመለከት ግን፤ ለኦርቶዶክሳውያን ፪፻ (200) አብያተ ክርስቲያናት ሲኖራቸው ለሙስሊሞች ደግሞ ወደ ፬፻ (400) የሚጠጉ መስጊዶች አላቸው። ይህም ማለት ፡- ለ፲፰ሺ ፯፻፶ (18,750) ኦርቶዶክሳውያን ፩ ቤተ ክርስቲያን፣ ለ፪ሺ (2,000) ሙስሊሞች ፩ መስጊድ አላቸው ማለት ነው። ኦርቶዶክሳውያን በሙስሊሞቹ ስሌት አብያተ ክርስቲያናት ይኑሯቸው ቢባል ሊኖሩ የሚገባቸው አብያተ ክርስቲያናት በቁጥር ፩ሺ ፰፻፸፭ (1,875) ይኾኑ ነበር፡፡ አሁን ካሉት አብያተ ክርስቲያናት በላይ ሌላ ፩ሺ ፮፻፸፭ (1,675) ያስፈልጉ ነበር ማለት ነው፡፡ ይህም ሊሠሩ ከሚገባቸው ፹፱ በመቶው (89%) ገና አልተሠሩም ማለትን ያጠይቃል፡፡ ወይም ሙስሊሞቹ በኦርቶዶክሱ ስሌት ሲታዩ ደግሞ ሊኖራቸው ይገባ የነበረው የመስጊድ ብዛት ፵፫ (43) ብቻ ነበረ። መስጊዶች ከምጣኔው በ፫፻፶፯ (357) ቁጥር አልፈዋል ማለትን ያሳያል። ይህም ፰፻፴ በመቶ (830 %) ንረት መኖሩን ያስረዳል። ይህንን ብናውቅም ለምን ብዙ መስጊዶች ይሠራሉ ብለን ተቃውመን አናውቅም። ምቀኝነት የለብንም፡፡ ከደጀ ሰላማችን ላይ መስጊድ ሥሩ ብሎ ያላሰቡትን ቀስቅሶ የሚያነሣሣ መንግሥት ሲመጣብን ግን እንዴት እንለፈው? ጠቅላይ ሚንስትሩ ብቻ ቃል ስለገቡ እንዴት ነው መመሪያና ሕግ እያለ ቃል ገቡ በሚል ሰበብ ብቻ እንዲህ ዓይነት ዓይን ያወጣ እኩይ ተግባር የሚከናወነው???፡፡ አንቀጽ 5. የአምልኮ ቦታ ስለመጠየቅ እና ስለመፍቀድ 5.6.ቦታው ተዘጋጅቶ ሲቀርብ ጽህፈት ቤቱ ከውሳኔ ሀሳብ ጋር ለከተማው አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ እንዲቀርብ ይደረጋል፡፡ ✍️ በካቢኔው ውሳኔ ሳያገኝ፤ በጠቅላይ ሚንስትሩ ቃል መግባትና በከንቲባው አስረካቢነት የተፈጸመ ሕገ ወጥ ተግባር ነው፡፡ አንቀጽ 7. የአምልኮ ማካሄጃ ቦታ ለመመደብ የሚሟሉ መስፈርቶች በከተማው ውስጥየአምልኮ ቦታእንዲመደብ የሚከተለት መሥፈርቶች መሟላት አለባቸው፤ 7.1. ለአምልኮ ማካሄጃ ሊመደብ የሚችለው ቦታ ቅይጥ የመኖሪያ መሬት አጠቃቀም ውስጥ ሆኖ የመዳረሻ መንገዱ ስፋት ቢያንስ ሰብሳቢ (15 ሜትር) መሆን ይኖርበታል፡፡ 7.2. በአካባቢው ከሚገኘው ከራሱ ነባር የአምልኮ ቦታ አዲስ ከተጠየቀው የአምልኮ ቦታ ቢያንስ በሁለም አቅጣጫ 3 ኪሎ ሜትር ሬዴየስ የሚርቅ መሆን አለበት፡፡ ✍️ በአቅራቢያው ከሚገኝ መስጊድ 3ት ኪ.ሜ. ርቀት Radius ርቀት የሌለውና መመሪያውን የሚጥስ ነው፡፡ 7.3. በተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት መካከል ሊኖር የሚገባው ርቀት 500 ሜትር ሬዴየስ ይሆናል፡፡ ✍️ ከአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (በተለምዶ ከርቸሌ ሚካኤል) እንኳን 500 ሜትር 100 ሜትር Radius እንኳን ርቀት የለውም፡፡ 7.4. ለአምልኮ ማካሄጃ አገልግሎት ቦታ የሚጠይቅ የሀይማኖት ተቋም በሚጠይቅበት አካባቢ ማለትም በሁሉም አቅጣጫ በ1.5 ኪለሎ ሜትር ሬድየስ ባለ በወረዳ ውስጥ የተመዘገበ ቢያንስ 7000 ምዕመን ነዋሪ መኖር አለበት፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ተመሳሳይ የሀይማኖት ተቋም ካለ በሁለም አቅጣጫ እስከ 1.5 ኪል ሜትር ሬዲየስ ባለው ክልል ውስጥ ያሉት ምእመናን በአዲሱ የሀይማኖት ተቋም ሊመዘገቡ አይችሉም፡፡ ✍️ በተጠቀሰው ቦታ ላይ የተጠቀሱት ቊጥር ያላቸው ሙስሊም ወንድሞቻችን እንደማይገኙ ከአካባቢው ነዋሪዎች እንረዳለን፡፡ ✍️ ከተጠቀሰው ቊጥር እጅግ በጣም ብዙ ቊጥር ያለው የአካባቢው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመን ግን ለአፍሪካ ኅብረት ተብሎ ከቦታው ሲነሳ በቂ ቦታ ስላልተሰጠው እንዲሰጠው በተደጋጋሚ እንዲሰጠው እየጠየቀ ሳለ ነው፤ አንዱን ልጅ፤ አንድን የእንጀራ ልጅ አድርጎ የሚሠራ የመንግሥት አሠራር የመጣው፡፡ 7.5.ከአምልኮ ማካሄጃ አገልግሎትጋር አብረው የማይሄዱ ማለትም ከአህጉር አቀፍና አለም አቀፍ ተቋማት፣ ከጦር ካምፖች፤ ከዋና ዋና ንግድ ቦታዎች፤ ከቆሻሻ መጣያ ቦታዎች፤ ከደህንነት ተቋማት እና ከሌሎች የአምልኮ ሁኔታ ሊያውኩ የሚችሉ የመሬት አጠቃቀም ቦታዎች ያለው ርቀት ቢያንስ ከ500 ሜትር በላይ መሆን አለበት፡፡ ነገር ግን በሥራ ላይ የዋሉ ሌሎች ሕጎች ካሉ በሕጎቹ ላይ የሰፈረው ርቀት ገዢ ይሆናል፡፡ ✍️ የተሰጠው ቦታ ከአኅጉር አቀፍ ያውም ዋና የአፍሪካ ኅብረት መሥሪያ ቤት አጥር ለአጥር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህም መመሪያውን የጣሰና አእምሮ ያለው ሰው የሠራው ካርታ እንኳን አይመስልም፡፡ 8.ለአምልኮ ማካሄጃ አገልግሎት የሚመደብ ቦታ ስፋት በየትኛውም የከተማው ክልል ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም የሀይማኖት ተቋም አዲስ የሚመደበው የአምልኮ ማካሄጃ ቦታ ስፋት ከ2,000 እስከ 4,000 ካሬ ሜትር ይሆናል፡፡ ✍️ የተሰጠው ቦታ የ4,000 ካሬ ሜትር የእጥፍ እጥፍ የእጥፍ እጥፍ ያውም 30000 ካሬ ሜትር ነው፤ በእነዚህና በመሳሰሉት ጉዳዮች መንግሥት ላወጣው ሕግ እንኳን የማይታመን፤ እንደ ወንድምና እኅት በማኅበራዊ ሕይወት የሚኖሩትን ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች እንዲጣሉ ጸብ ማጫሪያ የሆነን መሠረት ድንጋይ የሚጥል፤ ዝም ብሎ ሕግና መመሪያን እየጣሱ ቃል ገብቻለሁ በማለት መሬትን ሸንሽነው ለእወደድ ባይነትና ለምርጫ ኮሮጆ ድምፅ ማሟያነት የሚያውል ነው፡፡ የከተማው ከንቲባ የተናገሩት እውነታነቱን ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነው፤ ለምሳሌ ቦታው ለአፍሪካ ኅብረት ማስፋፊያ ተብለው የተነሣ ቦታ መሆኑን ድፍን የአዲስ አበባ ነዋሪ እየታወቀ ቦታው ላይ 2ት የመንግሥት ተቋማት ግንባታ ሊያከናውኑ ባለመቻላቸው ነው ለመስጊድነት የሰጠነው የሚለው፤ የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ለአፍሪካ ኅብረት ማስፋፊያ ተብሎ ከቦታው ተነሥቶ በቂ ቦታ እንዲሰጠው በተደጋጋሚ እየጠየቀ ሳለ አንዱን ልጅ፤ አንድን የእንጀራ ልጅ አድርጎ የሚሠራ የመንግሥት አሠራር መሠራቱ፡፡

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በግንቦት ፲፮/፳፻፲፪ ዓ.ም
+1
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በግንቦት ፲፮/፳፻፲፪ ዓ.ም በቀ/ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ ጋብቻህን የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታችን አባል ወንድማችንና መምህራችን፤ #ዲ.ን_ #ደጀኔ_ግዛው #ከማርታ_ከበደ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#የያዕቆብ_ልጆች_ወይስ_የ_……. #ልጆች፡፡ ‹‹ከመጠምጠም መማር ይቅደም›› የሚለውን ብሂል ያልሰሙና በሠሩት ድራማ ዙሪያ በቂ ችሎታው የሌላቸው ‹‹ያላዋቂ ሳሚ …. ይለቀልቃል›› የተባለላቸው ድራማ ሰሪዎች፡፡ #፠# በፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ 11ኛ ክፍሉን የያዘው ‹‹የያዕቆብ ልጆች›› ድራማ (በካም ግሎባል ፒክቸርስ፤ በኪሩቤል አስፋው ፕሮዲውሰርነት፤ በፈቃዱ ከበደ ማሞ ዳይሬክተርነት፤ በኤፍሬም ሽፈራው /ሚኪ/፣ ኢዮብ ጥላሁን፣ የማነ ብርሃን መለሰ ኤዲተርነት) የሚዘጋጅ የቴሌቪዥን ድራማ ሲሆን የሚያጠነጥነው በገንዘብ ውርስ ክፍፍል የሚተራመስ ቤተሰብ ውስጥ ለካህኑ የውርስ ኑዛዜ በሟች መሰጠቱ ነው፤ ይህ በሃገራችን የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን በድራማው ላይ በተለይም ቄሱን ሆኖ ድራማውን መሥራቱ ባልከፋ ነበር፡፡ ነገር ግን፤ ፠ የድራማው ቄስ የሀብት ተጋሪ ለመሆን የተጠቀመበት መንገድና ክፉ አስመስሎ መሳል ቀሳውስትን ፈጽሞ የማይገልጽና የማይወክል ነው፡፡ (እውነተኛ ቀሳውስት ለቃላቸው የተማኑ ከመሆናቸውም በላይ፤ የሚችሉ ከሆነ የንስሐ ልጃቸውን ልጆች በሚችሉት ሁሉ አሳድገው ለወግ ማዕረግ የሚያበቁ፤ አንዳንዶችም ከልጃቸው ጋር ወስደው የሚያሳድጉ ናቸው፤ እንኳን የውርስ ተጋሪ ለመሆን ሊሯሯጡ ይቅርና) የቄሱ አለባበስ፣ የአባቶቻችን የቀሳውስትን አለባበስ አይደለም፤ ፠ የድራማው ቄስ ያደረገው ቀሚስ በአብዛኛው ጊዜ መነኰሳት የሚለብሱትን ነው፤ ፠ የድራማው ቄስ ያጣፋው ነጠላ የሴት ነጠላ እንጂ የቀሳውስት አይደለም፤ (እውነተኛ ቀሳውስት ከላይ የሚደርቡት ጋቢ፥ የሚለብሱት ኩታ፥ የሚጣፉት ነጠላ የካህናትና አባቶችን እንጂ የእኅቶችን ነጠላ አይደለም፡፡) ፠ የድራማው ቄስ በመስቀሉ በሥርዓት ማማተብ አይችልበትም፤ (እውነተኛ ቀሳውስት ሲያማትቡ ሥርዐት ያለው መሆኑን ልብ ይሏል) ፠ የድራማው ቄስ የሰው ችግር አይገባቸውም፤ (ቀሳውስት ግን የሰውን ችግር የሚረዱና ምክር የሚለግሱ ስለችግርተኛው ሰው ብለው ፠የድራማው ቄስ ወሬው ሁሉ ‹‹ድል ያለ ድግስ›› ይደገስ እና እንብላ የሚል ነው፤ (እውነተኛ ቀሳውስት ግን ለሥጋ ድግስ ሳይሆን ለነፍስ ድግስ የሚጨነቁ ናቸው፡፡) ፠ የድራማው ቄስ አረማመዱ ከርፋፋና የተወላገደ ዓይነት ነው፤ (እውነተኛ ቀሳውት ሲራመዱ ተጠንቅቀው፥ ሲቀመጡ ነቅተው፥ ሲናገሩ መጥነው ነው፡፡) ፠ የድራማው ቄስ ጥምጥማቸው ያላዋቂ ነው፤ (እውነተኞች ቀሳውስት የመድኀኔ ዓለም ክርስቶስ አክሊለ ሦክ ምሳሌ የሆነውን ጥምጣም ሲጠመጥሙ አክሊለ ሦክን አስመስለውና አሳምረው ነው፡፡ ) ይገርማል እኮ፤ * እንኳን ዕውቅ ሆኑ ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊዳረስ በሚችል ሚዲያ ለሚተላለፍ ድራማ ይቅርና፤ እኛም በሰ/ት/ቤት ውስጥ እንደመኖራችንና በአብዛኛው ሰ/ት/ቤት የኪነጥበባት ክፍል እንደመኖሩ ድራማና ጭውውት ሲሰራ ስለሚሠራው ድራማ አስቀድሞ በቂ ልምምድ ይደረጋል፤ * የድራማውን ገጸ ባሕርይ ከመሥራትህ በፊት ስለምትሠራው ገጸ ባሕርይ የቅርብ ልምምድ ሊኖር በእጅጉ ይገባል፡፡ ….. ጥምጣም መጥምጠም አለባበስም ራሱ ራሱን የቻለ ልምምድ ያስፈለገዋል፤ እንዲሁ ቀሳውስት አምረው፥ ጠምጥመው ስታይ … ዝም ብለህ የምትጠመጥመው አይደለም… አለበለዚያ ‹‹ከበሮ በሰው እጅ ሲይዙት ያምር›› ነው የሚሆነው ነገሩ፡፡ * የአለባበስና የ<charcter› አሣሣልና መመስለን፤ ዕውቀቱና ልምዱ፥ ችሎታውን አተገባበሩ ካለቸውን ከሚችሉ ባለሙያዎችና ከቴአትር ቤቶች ጭምር መጀመሪያ ቁጭ ብሎ መማር ያስፈልጋል፤ እንዲሁ ዝም ብሎ ደርሶ ድራማ ሠሪ መሆን ያልዋኙበትን ውቅያኖስ መተረክ ማለት ነው፡፡ * በዚህም አዘጋጆቹም አውቀውትም ሆነ ሳያውቁ፥ አስተውለውትም ይሁን ሳያስተውሉ፥ እንዲያው ዝም ብሎም ይሁን ሆን ብለው የቤተክርስቲያኒቱን ምልክት ላይ እያፌዙና መልካም ስምን ጥላሸት እየቀቡ ነው፡፡ የፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀሳውስትን የማይወክልና የማይገልጹ ተግባራትን ማስተላለፉ ምን የሚሉት ነው፤ …. የኤዲቶርያል ክፍላቸውስ ለመሆኑ ምንድን ነው የሚሠራው፤ የሃይማኖት፣ የፖለቲካ፣ የባህል፣ … መሰል ነገሮችን ማረም ካልቻለስ ምኑን ነው ኤዴተር የሚያደረገው፤ ነው ወይስ ኤዲተር ለምስልና ድምፅ ብቻ ነውን??? ለድራማዎች እና ቴአትሮች የጦር መሣሪያ መያዝ ፤ የወታደርና የፖሊስ ልብስ ሲያስፈልግ አስቀድመው ከመሣሪያውና ከልብሱ ባለቤትና አስተዳዳር ፈቃድ ጠይቀው ሲያገኙ ነው፤ የቤተክርስቲያኒቱን ንዋያተ ቅድሳትና ምልክቶች ግን ያለማንም ፈቃድ በአደባባይ መቀለጃ ማድረጋቸው፤ ያሳዝናል፥ ያስቀይማልም፡፡ ክፍያ ይከፈለው እንጂ አሁን አሁን ኮሚዲውም፥ ዘፋኙም፥ አርቲስቱም፥ ኮማሪውም፥ ቀልደኛውም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ እምነታችን ላይ ከሚፈጽሙት ተግባር ሊቆጠቡ ይገባል፡፡ ያለበለዚያ፤ ** በነብስ ያስጠይቃል፤ በሥጋዊ ሕግም ቢሆን ያስጠይቃቸዋል፤ ሲብስም ‹‹ለቀጣፊ ይገባዋል ጥፊ›› የሚሏትን ነገር እንድናስታውሳት ያደርገናል፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡