es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 366 suscriptores, ocupando la posición 5 620 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 366 suscriptores.

Según los últimos datos del 22 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -33, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.71%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 489 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 226 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 23 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 366
Suscriptores
-224 horas
+317 días
-3330 días
Archivo de publicaciones
#ሀሁ_መጻሕፍት_ስጦታውን_አበርክቷል። ሀሁ መጻሕፍት መደብር ፥ የእልፍ መጻሕፍት ፕሮጀክት ተሳታፊ ልኹን በማለት ልዩ ልዩ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለፍኖተ ሕይወት ቤተ-መጻሕፍት ገቢ አድርጓል ፥ ሰ.ት.ቤታችንም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ሀሁ መጻሕፍት  ከ20 %  እስከ 50 % ልዩ ቅናሽ እያደረገ በረካታ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የሚያከፋፍል ፣ የሚያሳትም እና የሚሸጥ የመጻሕፍት መደብር ነው ፡፡ +++ እርሶም ሀሁ መጻሕፍት መደብርን በመጠቀም ፤ በሚከተሉት መንገዶች ስጦታዎን ማበርከት ይችላሉ ፡፡ 1 . የአንባቢያንን ጥም እየቆረጠ ካለው ሀሁ መጻሕፍት መደብር ጋር በቀጥታ በመሄድ ወይም በስልክ በመነጋገር መጻሕፍትን ገቢ በማድርግ ይችላሉ ፤ መጻሕፍቱን በአደራ የሚቀበሉት ሀሁ መጻሕፍት ደግሞ መጻሕፍቱን ለእኛ ያስረክባሉ ፡፡  + ከሀሁ መጻሕፍት መደብር ጋር በባንክ አካውንት ኩፖን መግዛት የሚችሉ ሲኾን ፤ የገዙትን ኩፖን ቊጥር ሲነግሩን እኛ ደግሞ ከሀሁ መጻሕፍት መድብር  መርጠን ፥ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንወስዳለን ፡፡ --- + ከሀሁ መጻሕፍት መደብር 10 መጻሕፍት ሲገዙ አንድ መጽሐፍ በነፃ የሚሰጦት ሲኾን ለእልፍ መጻሕፍት ፕሮጀክት ብለው በሚገዙበት ጊዜ ደግሞ ልዩ የእልፍ መጻሕፍት ( የፍኖተ ሕይወት ) ቅናሽ  ያገኛሉ ፡፡ የሀሁ መጻሕፍት መደብር አቅጣጫ ፤ ፩ . #ስታዲየም ---- › ናሽናል ታወር ----› ምድር ወለል ላይ ፣ ፪. #ሜክሲኮ ------›  ደብረወርቅ ታወር ----› ምድር ወለል ላይ ፡፡ #ስልክ ፤ ሀሁ መጻሕፍት ፤ --> 0911-00-67-05 ፍኖተ ሕይወት( እልፍ መጻሕፍት)  ፤ 09-22-74-40-53 | 09-19-36-36-75 ꔰ Facebook  https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool ꔰ Telegram https://t.me/medihanaelem         www.Finotehiwotsundayschool.com #share #share #share #እልፍ_መጻሕፍት

#ሀሁ_መጻሕፍት_ስጦታውን_አበርክቷል። ሀሁ መጻሕፍት መደብር ፥ የእልፍ መጻሕፍት ፕሮጀክት ተሳታፊ ልኹን በማለት ልዩ ልዩ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለፍኖተ ሕይወት ቤተ-መጻሕፍት ገቢ አድርጓል ፥ ሰ.ት.ቤታችንም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ሀሁ መጻሕፍት  ከ20 %  እስከ 50 % ልዩ ቅናሽ እያደረገ በረካታ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የሚያከፋፍል ፣ የሚያሳትም እና የሚሸጥ የመጻሕፍት መደብር ነው ፡፡ +++ እርሶም ሀሁ መጻሕፍት መደብርን በመጠቀም ፤ በሚከተሉት መንገዶች ስጦታዎን ማበርከት ይችላሉ ፡፡ 1 . የአንባቢያንን ጥም እየቆረጠ ካለው ሀሁ መጻሕፍት መደብር ጋር በቀጥታ በመሄድ ወይም በስልክ በመነጋገር መጻሕፍትን ገቢ በማድርግ ይችላሉ ፤ መጻሕፍቱን በአደራ የሚቀበሉት ሀሁ መጻሕፍት ደግሞ መጻሕፍቱን ለእኛ ያስረክባሉ ፡፡  + ከሀሁ መጻሕፍት መደብር ጋር በባንክ አካውንት ኩፖን መግዛት የሚችሉ ሲኾን ፤ የገዙትን ኩፖን ቊጥር ሲነግሩን እኛ ደግሞ ከሀሁ መጻሕፍት መድብር  መርጠን ፥ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንወስዳለን ፡፡ --- + ከሀሁ መጻሕፍት መደብር 10 መጻሕፍት ሲገዙ አንድ መጽሐፍ በነፃ የሚሰጦት ሲኾን ለእልፍ መጻሕፍት ፕሮጀክት ብለው በሚገዙበት ጊዜ ደግሞ ልዩ የእልፍ መጻሕፍት ( የፍኖተ ሕይወት ) ቅናሽ  ያገኛሉ ፡፡ የሀሁ መጻሕፍት መደብር አቅጣጫ ፤ ፩ . #ስታዲየም ---- › ናሽናል ታወር ----› ምድር ወለል ላይ ፣ ፪. #ሜክሲኮ ------›  ደብረወርቅ ታወር ----› ምድር ወለል ላይ ፡፡ #ስልክ ፤ ሀሁ መጻሕፍት ፤ --> 0911-00-67-05 ፍኖተ ሕይወት( እልፍ መጻሕፍት)  ፤ 09-22-74-40-53 | 09-19-36-36-75 ꔰ Facebook  https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool ꔰ Telegram https://t.me/medihanaelem         www.Finotehiwotsundayschool.com #share #share #share

መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል ካምባ ቅዱስ ሚካኤል ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል 45. ላሐ ቅዱስ ሚካኤል 46. ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል 47. መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል 48. ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል

አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፬. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 #ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፬. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፭. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፮. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፯. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፰. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፱. ባሕር ዳር ሽምብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፩. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፪. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፫. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፭. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፮. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፯. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፰. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፲፱. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፵፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1.. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5. ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) ዓለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል ዱከም ቅዱስ ሚካኤል ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል

#ሰኔ_፲፪   በዓለ ተዝካሩ #ለቅዱስ_ሚካኤል ሊቀ መላእክት   (#፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡)    ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ    #ሰኔ_፲፪ #መከበሩ_ስለምንድን_ነው_ቢሉ_፤ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር፤ ንሥረ አርያም የሚባል፥ ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ፥ ንዑድ ክቡር የሆነ ፥ የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ነው  እንዲሁም  የሌሎችም ቅዱሳን መታሰቢያ ቀናቸው  (ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት) ፡፡ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ነው  እነርሱም፤    #share ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤ ፠ ሐናፄ መቅደስና በሰማያት ያለ ምሥጢርን የተመለከተ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ፠67ኛ ሊቀ ጳጳስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ዘእስክንድርያ እረፍቱ ነው፤ ፠የእስክንድርያ 6ኛ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ዮስጦስ (ወንጌላዊና ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የክርስትና ጥምቀትን ያጠመቀው፥ ዲቁናና ቅስናን የሾመው) እረፍቱ ነው፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት/ ማብራሪያ፤ #፩. ቅዱስ ሚካኤል በፈቃደ እግዚአብሔር ከዲያብሎስ ጋር ተዋግቶ ያሸነፈበት፤ አምላክነትን ሽቶ በወደቀው በዲያብሎስ ምትክ ሊቀ መላእክት ሆኖ የተሾመበት እለት በመሆኑ ነው፡፡ ቀድሞ ከ100 ነገደ መላእክት ኃይላት የሚባሉ የ10 ነገደ መላእክት አለቃ ነበር፤ በዚህች ቀን ግን የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ አጋእዝት የተባሉትንና ሳጥናኤል(ሰማልያል) ይመራቸው ለነበሩት 10 ነገዶች በተጨማሪ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በአጠቃላይ ለሌሎችም 100 (99ኝ) ነገደ መላአክት አለቃ ሁኗል፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ #፪. ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት፤ ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 - 326/ በግብፅ ሃገር ንግሥት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ያሠራችውንና ጣዖት ይመለክበት የነበረውን ቤተ ጣዖትን አፍርሶ በቦታው ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አግብቶ በዓሉን በታላቅ ክብር ያከበረበት እለት ነው፡፡ #፫. ባሕራንን ያዳነበት ሊቀ ጳጳሳት እለ እስክንድሮስ የተሠራውን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ከሚያከብሩ ምእመናንን አንዱ የባሕራን አባት ነበር፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚፈራ ወር በገባ በየዐሥራ ሁለቱ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን የሚዘክርና ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት ቀን በታላቅ ክብር የሚያከብር አንድ ሰው ነበር፤ በዚህ ሰው ላይ ላይ ጥላቻ ያደረበትና ርኅራኄ የሌለው አንድ ባለጸጋ ጐረቤት ነበረው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በሚያከብርበት ጊዜ ሁሉ ይዘብትበት ይሳለቅበት ነበር፡፡     ይህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውም በዚህ ዓይነት በጐ ሥራ ብዙ ጊዜ ከኖረ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም ያርፍ ዘንድ የሞቱ ጊዜ ቀረበ። ሚስቱንም ጠርቶ ‹‹በጐ ስራ ከመሥራት ለድኃ ከመመጽወት ቸል አትበይ! የቅዱስ ሚካኤልንም በዓል በየወሩ ከማክበር አትቦዝኝ፤ ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት  ቀን ከፍ ባለ ሥነ ሥርዓት እንድታከብሪ አደራ እልሻለው›› አላት፡፡ በሚሞትበትም ጊዜ ሚስቱ ፀንሳ ነበር። ይህም ደገኛ ሰው በሰላም ዐረፈና ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ። ሚስቱም የመውለጃዋ ሰዓት በደረሰ ጊዜ ታላቅ ጭንቅ ላይ ኾነች እርሷም መልአኩን ቅዱስ ሚካኤል እንዲደርስላት ተማጸነችው በሰላምም ተገላገለች፡፡ መልኩ በጣም ያማረ ልጅ ወለደች። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ያን ሕፃን ባረከውና ‹‹ቸርነት ርኅራኄ የሌለውን የዚህን ባለጸጋ ገንዘብና ሀብት እርሻውንም ሁሉ ይህ ሕፃን እንዲወርስ እግዚአብሔር አዟል›› አለ። ያን ጊዜ ያ ባለጸጋ በሴትዮዋ ቤት መስኮት አጠገብ ሆኖ ሁኔታውን ሁሉ ይመለከት ነበርና ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ልቡ በታላቅ ሐዘን ተነካ፤ ሕፃኑንም የሚገድልበትን ምክንያት ይፈልግ ጀመር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ብላቴናውን ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀው ነበር። ብላቴናውም ዐሥር ዓመት በሆነው ጊዜ እናቱ በጣም ችግር ፀናባት፡፡ ባለጸጋው እኔ ጋር ተንከባክቤ ላሳድገው ብሎ ከእናቱ ከተቀበለ በኋላ፤ በልጅ ቁመት ልክ ሳጥን አሠርቶ ሕፃኑን በሣጥኑ ውስጥ አግብቶ በላዩ ላይ ቆለፈበትና ሣጥኑን ወስዶ ከባሕር ጨመረው፤ እንዲሁም የሣጥኑን ቁልፍ መክፈቻ አብሮ ወረወረው። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ያ ሣጥን ሳይሰጥም በባሕሩ ላይ እየተንሳፈፈ ከዚያች አገር ርቃ ወደምትገኝ የባሕር ወደብ ደረሰ። በባሕሩ አካባቢ በጎቹን አሰማርቶ የሚጠብቅ አንድ ሰው ነበርና ያንን ሣጥን ባየው ጊዜ ከባሕሩ አወጣውና ወደ ቤቱ ወስዶ ሣጥኑን ቢከፍተው ያ ባለ ፀጋ ሊገድለው ያሰበውን ሕፃን በሣጥኑ ውስጥ አገኘው።  ባየውም ጊዜ እጅግ ተደስቶ በባሕር ውስጥ ስላገኘው ስሙን "ባሕራን" ብሎ ሰየመውና እንደ ልጁ አድርጐ ይንከባከበው ዘንድ ወሰነ፡፡ ከባሕራን ሀገር የበግ ጠባቂው አገር የዐሥር ቀን ጐዳና የሚያስኬድ ርቀት ነበረው። ከብዙ ዓመታት በኋላ ያ ባለ ጸጋ ሰው ለንግድ ከሀገሩ ወጣ፡፡ በጉዞውም ላይ ሳለ ፀሐይ ስትገባ ከዚያ የበግ ጠባቂው ዘንድ ደረሰ። በግ ጠባቂውንም ‹‹ወንድሜ ሆይ ባንተ ዘንድ የማድርበት ቢኖር ታሳድረኝ ዘንድ እለምንሃለው፣ ኪራዩንም እከፍልሃለው›› ብሎ ጠየቀውና ያ በግ ጠባቂ ወደ ቤቱ አስገባው። ባለጸጋውም ገብቶ ጥቂት ካረፈ በኋላ በግ ጠባቂው ያን ብላቴና ባሕራን ብሎ ሲጠራው በሰማ ጊዜ ‹‹ልጅህ ነውን?›› ብሎ ጠየቀው። በግ ጠባቂውም ‹‹አዎን ይህ አሁን ጐልማሳ ሆኖ የምታየው ወጣት ገና ሕፃን ሆኖ ሳለ በሣጥን ተከቶ ከባሕር ውስጥ ተጥሎ አግኝቼው ወስጄ አሳድጌዋለሁና ልጄ ነው›› አለው። ባለጸጋውም በባሕር ውስጥ የጣለው ሕፃን መሆኑንም ስላወቀ ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደነገጠ፤ ይገድለውም ዘንድ ፈለገ፡፡ በበነጋውም መንገዱን ለመሄድ ሲዘጋጅ ልዩ ልዩ ምክንያት (ሰይጣናዊ ሐሳብ) በመፍጠር በግ ጠባቂውን ‹‹ወንድሜ ሆይ አንድ የማስቸግርህ ጉዳይ አለኝ ይኸውም በቤቴ የረሳሁት ነገር ስላለ ሄዶ መልእክት ያደርስልኝ ዘንድ ይህን ብላቴና እንድትሰጠኝ ነው የድካሙንም ዋጋ ሃያ ወቄት ወርቅ እከፍላለሁ›› አለው።

የደብራችን መምህር ፤ መጋቤ ምስጢር ቀጻላ ፈንቴ ስጦታቸውን አበርክተዋል ፡፡ « ያለነበበ ትውልድ እምነቱንም ባሕሉንም ሥነ ምግባሩንም ማወቅ አይችልም ፡፡በሥነ ምግባር ለመኖር በአምነት ለመጠንከር መ
የደብራችን መምህር ፤ መጋቤ ምስጢር ቀጻላ ፈንቴ ስጦታቸውን አበርክተዋል ፡፡ « ያለነበበ ትውልድ እምነቱንም ባሕሉንም ሥነ ምግባሩንም ማወቅ አይችልም ፡፡በሥነ ምግባር ለመኖር በአምነት ለመጠንከር መጻሕፍት አስፈላጊ ናቸው ፡፡የተፈለገ መጽሐፍ ኹሉ በቅድስት ቤተ-ክርስቲያን መታጣት የለበትም ስለዚኽም ኹላችንም የበኩላቸንን ልናደርግ ይገባል ፡፡ መጋቤ ምስጢር ቀጻለ ፈንቴ #እልፍ_መጻሕፍት

"...ወጣቶችን በሃይማኖት ለማጽናት በመጻሕፍት የተደራጀ ላይብረሪ አስፈላጊ ነው " መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ #እልፍ_መጸሕፍት የደብራችን መምህር መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ የመጽሐፍ ስጦታቸውን አበርክ
"...ወጣቶችን በሃይማኖት ለማጽናት በመጻሕፍት የተደራጀ ላይብረሪ አስፈላጊ ነው "                   መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ #እልፍ_መጸሕፍት የደብራችን መምህር መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ የመጽሐፍ ስጦታቸውን አበርክተው መልእክታቸውን እንደሚከተለው አስተላልፈዋል ----- እልፍ መጻሕፍት በተሰኘው መርሐ ግብር ለቀጨኔ ደብረሰላም መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የመጽሐፍ ስጦታ አበርክቻለኁ ።   ለወዳጆቼ የማስተላልፈው መልእክት ሰንበት ትምህርት ቤታችን በላይብረሪ ለማጠናከር በእንቅስቃሴ ላይ ስለምንገኝ ፥ አንድ መጽሐፍ ለሰንበት ትምህርት ቤት እንድታበረክቱ በትህትና እጠይቃለሁ ። የቀጨኔ አካባቢ ወጣቶችን በሃይማኖት ለማጽናት በመጻሕፍት የተደራጀ ላይብረሪ አስፈላጊ ነውና እንድታግዙ ለወዳጆቼ ጥሪ አደርጋለኁ ።  መጽሐፍ የምታበረክቱት በሰንበት ትምህርት ቤቱ ስማችሁ ተጽፎ የሰጣችኁት መጽሐፍ ከትውልድ ወደ ትውልድ በክብር ተይዞ የሚተላለፍ እና በረከት የሚያስገኝ ነው ።     መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ ዘቀጨኔ መድኀኔዓለም https://www.facebook.com/100078051074345/posts/pfbid02eFZURBcHDT4d5Du3NeJFsu2L1KLzhKtkekxhq9AYT9DuskZ7V15UKfSbdwV92dKql/?mibextid=CDWPTG