es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 378 suscriptores, ocupando la posición 5 573 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 194 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 378 suscriptores.

Según los últimos datos del 06 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 32, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.44%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 449 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 461 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 07 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 378
Suscriptores
-424 horas
-257 días
+3230 días
Archivo de publicaciones
#ስለ_ነገዋ_ቤተክርስቲያን_የምትጨነቁ_ከሆነ_የሰንበት_ትምህርት_ቤትን_አገልግሎት_በልባችሁ_አኑሩ_ብጹዕ_አቡነ_ጎርጎርዮስ ✞ ✞ ✞ ጥቂት ለማይባል ጊዜ በሰ/ት/ቤታችን እና በደብሩ አስተዳደር መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ‘‘ይፈታል’’ የተባለውን ውሳኔ የያዘ ደብዳቤ ከሀገረ ስብከቱ ለደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት የመድረሱን ዜና ሰማን፡፡ እኛም የአለመግባባቱን መንስኤ ላልተረዱት ምዕመናንና አባላቶቻችን ጉዳዩን ግልጽ ለማድረግ እና የውሳኔውን #ኢ_ፍትሐዊነት ለማስረዳት ይህንን ጻፍን፡፡ … የሰ/ት/ቤቱ የ55 ዓመታት ጉዞ አልጋ በአልጋ አልነበረም፤ ይልቁንም በበርካታ ተግዳሮችትና ፈተናዎች የታጀበ ነበር፡፡ ከእነዚህ ችግሮች ውስጥ ግን እንደ #ማስተማርያ_ቦታ_እጥረት ሰ/ት/ቤቱን በብርቱ የፈተነው የለም፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ እና ሰ/ት/ቤቱ በቂ የማስተማርያ ቦታ እንዲሰጠው በየዘመኑ ለተቀያየሩት የደብሩ አስተዳደር አካላት በተደጋጋሚ ጥያቄውን ቢያቀርብም ምላሽ ሳይሰጠው ቀረ፡፡ ይህ የቦታ ጥያቄ 2008ዓ.ም ላይ በተደራጀና በተጠና መልኩ የሰ/ት/ቤቱን የሕንጻ ዲዛይን እና የደብሩን ማስተር ፕላን አካትቶ ሰ/ት/ቤቱ የ50ኛ ዓመት በዓሉን ባከበረበት ወቅት ለደብሩ ቀረበ፡፡ ከብዙ ዓመታት ጥረት እና ትዕግስት በኋላ አጥጋቢ የሆነ ምላሽ ከደብሩ ተገኘ፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ቀድሞ የነበረበት ቦታ ላይ (ያሁኑ #መዋዕለ_ሕጻናት ላይ) ለመንፈሳዊ ትምህርትና አገልግሎት የሚውል ሕንጻ የመዋዕለ ሕጻናቱ ውል ሲጠናቀቅ እንዲሠራ ፈቃድ ተሰጠው፡፡ … ባሳለፍነው ዓመት የመዋዕለ ሕጻናቱ ውል ተጠናቆ ሰ/ት/ቤቱ የተሰጠውን ቦታ ሊረከብ ሲል አዲሱ የደብሩ አስተዳደርና ሰበካ ጉባኤ የቀድሞውን ሰበካ ጉባኤ ውሳኔ ሻረ፡፡ ወሉን ዳግመኛ ለ5ዓመታት አራዘመ፤ ከመንፈሳዊው ትምህርት ይልቅ በኪራይ ለሚገኘው ጥቂት ብር የሰ/ት/ቤቱ የዘመናት ጥያቄ በብር ተለወጠ። … ይሄ ዳግመኛ የተነሳው የማስተማርያ ቦታ ጥያቄ ሳይመለስና መቋጫ ሳያገኝ ደብሩ ሌላ ዕቅድ ይዞ ብቅ አለ፡፡ ‹‹የደብሩን ገቢ ለማሳደግ ለንግድ የሚውል ባለ 5 ወለል (G+5) ሕንጻ ለመገንባት›› ሰፊ እንቅስቃሴ ጀመረ፡፡ ይህንንም ህንጻ ለመገንባት አሁን ሰ/ት/ቤቱ ለትምህርት እና አገልግሎት የሚጠቀምበትን ቦታ መረጠ፡፡ (የሰ/ት/ቤቱ የቦታ ጥያቄ ሳይመለስ መሆኑን ልብ ይለዋል) ሰ/ትቤቱም በምትኩ በደብሩ ማስተር ፕላን ላይ ወደ ጸደቀለትና በቀድሞ ሰበካ ጉባኤ ወደ ተሰጠው (አሁን መዋዕለ ሕጻናት ወደ ሆነው) ቦታ እንዲዘዋወርና ደብሩም ያሰበውን ዕቅድ እንዲያስፈጽም ይሁንታውን ሰጠ፡፡ … የደብሩ አስተዳደር በማስተር ፕላኑ ላይ ለሰ/ት/ቤቱ የተሰጠውን #ቋሚ_ቦታ ከመስጠት ይልቅ ለትምህርት ምቹ ያልሆኑ፣ ሌላ ተደራራቢ አገልግሎት ያለባቸው፣ ሰንበት ትምህርት ቤቱን የጽዋ ማኅበራት ላይ ጥገኛ የሚያደርጉ እንዲሁም አንዳንዶቹም ከቅጽረ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ ጊዜያዊ ቦታዎችን አቅረበ፡፡ ችግሩን በቋሚነት ከመፍታት ይልቅ ጊዜያዊና አጫጭር መፍሔዎች ላይ አተኮረ፡፡ … የደብሩ አስተዳደር ለሕንጻው ግንባታ ያሳየውን ቁርጠኝነት ለሰ/ት/ቤቱ ጥያቄ መድገም አልቻለም፡፡ የሰ/ት/ቤቱን #የቋሚ_የቦታ_ጥያቄ ወደ ጎን በመተው ሕንጻውን ለመገንባት እንቅስቃሴውን አጠናከረ፡፡ … ቀናት ቀናትን እየተኩ ሲሄዱ ልዩነቶች ሰፉ፡፡ የሰ/ት/ቤቱ አጭርና ግልጽ ሆነው የመብት ጥያቄ እንደ አለመታዘዝና አመጽ ከፍ ሲልም እንደ ሥርዓት አልበኝነትም ተቆጠረ፡፡ አጀንዳውን ቀይሮ ጉዳዩን የካህናት እና የሰ/ት/ቤት ጸብ ለማድረግ ተሞከረ፡፡ ጉዳዩን ለመፍታት ለቁጥር የሚታክቱ ስብሰባዎች ተደረጉ፤ መፍትሔ ጠቋሚ ጥናቶች ቀረቡ፤ በሽምግልና ተሞከረ፤ በርካታ የደብዳቤ ልውውጡች ተደረጉ፤ ከአካባቢው የጸጥታ አካላትም ጋር ሳይቀር ውይይቶች ተደረጉ፡፡ #መፍትሔ_ግን_ጠፋ፡፡ … ይህ አለመግባባት ለዳኝነት ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሄደ፡፡ ችግሩን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት #የካቲት_7_2012ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር መሰብሰቢያ አዳራሽ በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ #በመምህር_እንቁባህርይ_ተከስተ ሰብሳቢነት፣ በመምሪያው ፀሐፊ በመምህር ሰሎሞን ኃይለማርያም ቃለ ጉባኤ ያዥነት፣ የደብሩ አስተዳዳሪና ጸሐፊ፣ የደብሩ የሰበካ ጉባኤና የልማት ኮሚቴ አባላት፣ የሰ/ት/ቤቱ ሥራ አመራሮች፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ኃላፊ #ቀሲስ_ሔኖክ፣ የአራዳና ጉለሌ ክፍላተ ከተማ ሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት ኃላፊ ዲያቆን ኢንጂነር አርአያ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ተወካዮች በተገኙበት ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ የሚከተሉት #የጋራ_ውሳኔዎች ላይ ተደረሰ፡፡ … 1ኛ) ደብሩ ለሰ/ት/ቤቱ አገልግሎት የሚሆን፣ የወደፊት የሰ/ት/ቤቱን ሕንጻ ማስገንባት የሚችል #600_ካሜ_ቦታ #በቋሚነት_ቅጽረ_ቤተክርስቲያን ውስጥ እንዲሰጥ፤ ከ#600_ካ.ሜ ያነሰ 599 ካ.ሜ እንኳን ቢሆን ተቀባይነት እንደማይኖረው፣ 2ኛ) ደብሩ የተባለውን #600_ካሜ ቦታ መስጠት ካልቻለ ሰ/ት/ቤቱ ከ40ዓመታት በላይ ሲገለገልበት የነበረውን አሁን #መዋዕለ_ሕጻናት የሆነውን ቦታ እንዲሰጥ 3ኛ) የደብሩ ሰበካ ገባኤ 600 ካሜ ቦታ በቋሚነት ለሰ/ት/ቤቱ መስጠቱን የሚያረጋግጥ ቃለጉባኤ እንዲልክ፣ ይህንንም በቦታው ላይ ተገኝተው ትክክለኛነቱን እንዲያረጋግጡ ቀሲስ_ሔኖክን፣ መምህር_ሰሎሞንን፣ ዲ/ን ኢንጂነር አርአያን፣ ኢንጂነር ሕሊናን ጉባኤው መርጦ በጸሎት ተጠናቀቀ፡፡ (ውሳኔዎቹ በቂ የድምጽ ማስረጃ የተያዘባቸው ናቸው፡፡) … ደብሩ እሰጣለሁ ያለው የሴቶች መጠለያ ቦታ (ከቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በስተ ግራ የሚገኘው) በደብሩ የልማት ቴክኒክ ኮሚቴ መሀንዲሶች ተለካ፤ ነገር ግን ግማሹ እንኳን አልተገኘም፤ 265 ካ.ሜ ብቻ ሆነ፡፡ በምህንድስና የግንባታ ሕግ መሠረትም ከአጥሩ መራቅ ያለበት (off set) 1.5ሜትር እና በመንገድ ሥራ ምከንያት የሚቀነሰው 1.5ሜትር ግምት ውስጥ ገብቶ ሲሰራ የተጣራ #108_ካሜ ብቻ እንደሆነ በደብሩ መሀንዲሶች ተረጋገጠ፡፡ … ደብሩ ግን ለካሬ ማሟሟያ ብቻ እንዲሆን የሰንበት ትምህርት ቤቱን ሕንጻ ማስገንባት የማይችሉ እና እጅግ በጣም የተራራቁትን የሰ/ት/ቤቱን የንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ፣ ጽ/ቤት፣ ቤተ መጻሕፍት፣ የአብነት ት/ቤቶች፣ የጽጌ ማኅበርተኞች አዳራሽ እና ካልጠፋ ቦታ #ታላቅ_ምሥጢር_የሚፈጸምበትን ክርስትና ቤት፤ ቤተልሔሙ ብቻ ሲቀር #ከደብሩ_መሐንዲሶች_ዕውቅና_ውጪ ሙያው የሌላቸውን ሰዎች በማስለካት እና ሆን ተብሎ የሰ/ትቤቱ የሰበካ ጉባኤ ተወካይ እንዳይገኝ በማድረግ 626 ካ.ሜ ሰጥቻለሁ አለ፡፡ … የመስክ ምልከታ እንዲያደርግ እና አጣርቶ ሪፖርት እንዲያቀርብ የተሰየመው ልዑክ ደግሞ የሚከተለውን ሪፖርት አቀረበ፡- ‹‹ከ295ካ.ሜ ውጪ የተዘጋጀ ቦታ ካለመኖሩም ባሻገር ቀሪዎቹ ጊዜያዊ እንጂ ቋሚ ቦታዎች ከመሆናቸውም ባሻገር በቀን 7/06/2012ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት #በተወያየነውና_በደረስነው_መሠረት_የተዘጋጀ_አለመሆኑን_እንገላጻለን፡፡›› የሚል ነበር፡፡ … በቀርቡ ግን ከሀገረ ሰብከቱ ለደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት የተጻፈው እና የመምሪያውን ውሳኔው የያዘው ደብዳቤ ግን በቀን 7/06/2012ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ከተደረሰበት ስምምነት #ፍፁም_ተቃራኒ የሆነና በተለመደው የቤተክህነቱ ብልሹ አሠራር የተተበተበ ነው፡፡ … ይሄ ኢ-ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት ውሳኔ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ዘንድ ተቀባይነት የለውም፡፡ ይኸውም ቃል በቃል..

ባሕራንም መልእክቱን ለማድረስ ዘጠኝ ቀን ተጉዞ የአንድ ቀን ጎዳና ሲቀረው እነሆ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በፈረስ ተቀምጦ ወደሱ ደረሰና ወዴት እንደሚሄድ ጠየቀው፡፡ ባሕራንም ‹‹ከአንድ ባለጸጋ ሰው የተጻፈ ደብዳቤ ይዤ እርሱን ለማድረስ ዕገሊት ወደምትባል አገር እሄዳለሁ›› አለው። ንዑድ ክቡር የሚሆን ቅዱስ ሚካኤልም "እስኪ የመልእክቱን ደብዳቤ አሳየኝ?" አለው፡፡ ባሕራንም ‹‹ጌታዬ ለማንም አታሳይ ብሎኛል›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹እሺ ያም ባይሆን እንደተጠቀለለ አሳየኝ›› አለው፡፡ ባሕራንም አሳየው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በሞቱ ደብዳቤ ላይ እፍ ቢልበት የሞቱን ትእዛዝ አጥፍቶ የሕይወት ትዕዛዝ ጽፎበታል፡፡ በደብዳቤው ላይ የተጻፈውን የሞት መልእክት ደምስሶ ‹‹ከእኔ ከባለጸጋ ዕገሌ የተጻፈ›› ይልና ‹‹ይህን መልእክት ይዞ ለመጣሰው ዕገሊት የምትባለዋን ልጄን አጋቡት (ዳሩለት) በዱር የተሰማራውን ከብቴን ፥ በቤት ያለውን ሀብቴን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቴን በሙሉ አውርሼዋለሁና እኔ እስክመጣ ድረስ አትጠብቁ በሄድኩበት ሀገር የምቆይበት ጉዳይ አለኝና፤ በቤቴና በንብረቴ ላይ ሙሉ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና የወደደውን ያደርግ ዘንድ አትከልክሉት ስለዚህም በእኔና በአንተ መካከል የምንተዋወቅበትን ምልክት አድርጌበታለሁ›› የሚል ጽሑፍ ጻፈበት "እንግዲህ ወደ ባለጸጋው ቤት ሂድና ይህን መልእክት አድርስ አለው፤ ባሕራንም ‹‹እሺ ጌታዬ እንዳዘዝከኝ አደርጋለሁ›› ብሎ ጉዞውን ቀጠለና የዚያን የባለፀጋ ቤት እየጠየቀ ከደረሰበት በኋላ ደብዳቤውን ለሹሙ ሰጠው። ያም ሹም ደብዳቤውን ተቀብሎ ሲያነብ የታተመበት ማኅተም ዕውነተኛ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በቤተ ክርስቲያን ደንብ የባለጸጋውን ልጅ አጋባው፣ የሠርጉንም በዓል እስከ ፵ ቀን ድረስ በታላቅ ደስታ አከበሩ። ከሠርጉም በዓል ፍጻሜ በኋላ ያ ባለጸጋ ሰው ከሄደበት አገር ወደ ሀገሩ ተመልሶ ገባና በቤቱ አካባቢ ሲደርስ የደስታና የዘፈን ድምፅ ስለሰማ "ይህ የምሰማው ድምፅ ምንድነው?" ሲል ጠየቀ፡፡ ሰዎቹም ‹‹ባሕራን የተባለ ጐበዝ ካንተ ዘንድ ልጄን ዳሩለት የሚል ትእዛዝ አምጥቶ ልጅህን አግብቶ በሠርጉ ምክንያት ይዘፍናሉ ይደሰታ፤ እነሆ እየበሉና እየጠጡ በቀንና በሌሊት እየዘፈኑ ሲደሰቱ ፵ ቀን ሆኗቸዋል በመልእክትህም እንዳዘዝከው ገንዘብህን የወንድና የሴት ባሮችህን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረትህን ሁሉ በሙሉ አስረክበውታል›› አሉት። ያም ባለጸጋ ያህን ቃል በሰማ ጊዜ ከድንጋጤው የተነሳ በታላቅ ቃል በመጮኽ ከመሬት ላይ ተከስክሶ ሞተና ነፍሱን አጋንንት ተረክበው ወደ ሲኦል አወረዷት። ከዚህም በኋላ ባሕራን የተባለ ያ ጐልማሳ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ እያከበረ ዝክሩን እየዘከረ ይኖር ጀመር። በዚያን ጊዜ በጉዞ ላይ ሳለ ተገልጾለት የሞቱን መልእክት ወደ ሕይወት የለወጠለት ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነም አወቀ ተረዳ። ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ሊቈጥሩት የማይቻል ብዙ ስለሆነ በኛም ላይ ኃይለ ረድኤቱ አድሮብን ይኑር እስከ ዘላለሙ ድረስ አሜን፡፡ #፬. አፎምያን ያዳነበት ቅድስት አፎምያ ሀገሯ ኪልቅያ ነው፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ መስፍነ ኪልቅያ ነበረ፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ ነበር፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጕል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፤ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም ፥ በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኵሴ መስሎ አጋንንትን መነኰሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡ እርሷም ‹‹ከቤት ገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ›› አለቻቸው፡፡ ሰይጣናቱም ‹‹እኛማ በነግህ ጸልየናል?›› አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን ‹‹...እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ፥ ስታረጂ የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊት ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ፥ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ›› አላት፡፡ ቅድስት አፎምያም ‹‹አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ፥ አትጸልዩ ያልከኝ፤ ጌታ ምጽዋትን መጽውቱ ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? ርግቦች እንኳን ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም፤ ታዲያ ጥንት በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?›› ብላ ሞገተችው፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ ከላይ እንዳየነው በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሰኔ 12 ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?›› በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው ‹‹በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም›› ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ። ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ 12 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ #፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

እንኳን አደረሰን፡፡ ሰኔ ቅዱስ ሚካኤልና ሥርዐተ ማኅሌት፡፡ #ሰኔ_፲፪ #መከበሩ_ስለምንድን_ነው_ቢሉ_፤ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር፤ ንሥረ አርያም የሚባል፥ ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ፥ ንዑድ ክቡር የሆነ ፥ የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ስለኾነና የሌሎችም ቅዱሳን መታሰቢያ ቀናቸው ስለኾነ ነው፡፡ እነርሱም፤ ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤ ፠ ሐናፄ መቅደስና በሰማያት ያለ ምሥጢርን የተመለከተ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ፠67ኛ ሊቀ ጳጳስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ዘእስክንድርያ እረፍቱ ነው፤ ፠የእስክንድርያ 6ኛ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ዮስጦስ (ወንጌላዊና ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የክርስትና ጥምቀትን ያጠመቀው፥ ዲቁናና ቅስናን የሾመው) እረፍቱ ነው፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት/ ማብራሪያ፤ #፩. ቅዱስ ሚካኤል በፈቃደ እግዚአብሔር ከዲያብሎስ ጋር ተዋግቶ ያሸነፈበት፤ አምላክነትን ሽቶ በወደቀው በዲያብሎስ ምትክ ሊቀ መላእክት ሆኖ የተሾመበት እለት በመሆኑ ነው፡፡ ቀድሞ ከ100 ነገደ መላእክት ኃይላት የሚባሉ የ10 ነገደ መላእክት አለቃ ነበር፤ በዚህች ቀን ግን የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ አጋእዝት የተባሉትንና ሳጥናኤል(ሰማልያል) ይመራቸው ለነበሩት 10 ነገዶች በተጨማሪ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በአጠቃላይ ለሌሎችም 100 (99ኝ) ነገደ መላአክት አለቃ ሁኗል፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ #፪. ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት፤ ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 - 326/ በግብፅ ሃገር ንግሥት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ያሠራችውንና ጣዖት ይመለክበት የነበረውን ቤተ ጣዖትን አፍርሶ በቦታው ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አግብቶ በዓሉን በታላቅ ክብር ያከበረበት እለት ነው፡፡ #፫. ባሕራንን ያዳነበት ሊቀ ጳጳሳት እለ እስክንድሮስ የተሠራውን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ከሚያከብሩ ምእመናንን አንዱ የባሕራን አባት ነበር፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚፈራ ወር በገባ በየዐሥራ ሁለቱ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን የሚዘክርና ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት ቀን በታላቅ ክብር የሚያከብር አንድ ሰው ነበር፤ በዚህ ሰው ላይ ላይ ጥላቻ ያደረበትና ርኅራኄ የሌለው አንድ ባለጸጋ ጐረቤት ነበረው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በሚያከብርበት ጊዜ ሁሉ ይዘብትበት ይሳለቅበት ነበር፡፡ ይህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውም በዚህ ዓይነት በጐ ሥራ ብዙ ጊዜ ከኖረ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም ያርፍ ዘንድ የሞቱ ጊዜ ቀረበ። ሚስቱንም ጠርቶ ‹‹በጐ ስራ ከመሥራት ለድኃ ከመመጽወት ቸል አትበይ! የቅዱስ ሚካኤልንም በዓል በየወሩ ከማክበር አትቦዝኝ፤ ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት ቀን ከፍ ባለ ሥነ ሥርዓት እንድታከብሪ አደራ እልሻለው›› አላት፡፡ በሚሞትበትም ጊዜ ሚስቱ ፀንሳ ነበር። ይህም ደገኛ ሰው በሰላም ዐረፈና ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ። ሚስቱም የመውለጃዋ ሰዓት በደረሰ ጊዜ ታላቅ ጭንቅ ላይ ኾነች እርሷም መልአኩን ቅዱስ ሚካኤል እንዲደርስላት ተማጸነችው በሰላምም ተገላገለች፡፡ መልኩ በጣም ያማረ ልጅ ወለደች። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ያን ሕፃን ባረከውና ‹‹ቸርነት ርኅራኄ የሌለውን የዚህን ባለጸጋ ገንዘብና ሀብት እርሻውንም ሁሉ ይህ ሕፃን እንዲወርስ እግዚአብሔር አዟል›› አለ። ያን ጊዜ ያ ባለጸጋ በሴትዮዋ ቤት መስኮት አጠገብ ሆኖ ሁኔታውን ሁሉ ይመለከት ነበርና ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ልቡ በታላቅ ሐዘን ተነካ፤ ሕፃኑንም የሚገድልበትን ምክንያት ይፈልግ ጀመር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ብላቴናውን ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀው ነበር። ብላቴናውም ዐሥር ዓመት በሆነው ጊዜ እናቱ በጣም ችግር ፀናባት፡፡ ባለጸጋው እኔ ጋር ተንከባክቤ ላሳድገው ብሎ ከእናቱ ከተቀበለ በኋላ፤ በልጅ ቁመት ልክ ሳጥን አሠርቶ ሕፃኑን በሣጥኑ ውስጥ አግብቶ በላዩ ላይ ቆለፈበትና ሣጥኑን ወስዶ ከባሕር ጨመረው፤ እንዲሁም የሣጥኑን ቁልፍ መክፈቻ አብሮ ወረወረው። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ያ ሣጥን ሳይሰጥም በባሕሩ ላይ እየተንሳፈፈ ከዚያች አገር ርቃ ወደምትገኝ የባሕር ወደብ ደረሰ። በባሕሩ አካባቢ በጎቹን አሰማርቶ የሚጠብቅ አንድ ሰው ነበርና ያንን ሣጥን ባየው ጊዜ ከባሕሩ አወጣውና ወደ ቤቱ ወስዶ ሣጥኑን ቢከፍተው ያ ባለ ፀጋ ሊገድለው ያሰበውን ሕፃን በሣጥኑ ውስጥ አገኘው። ባየውም ጊዜ እጅግ ተደስቶ በባሕር ውስጥ ስላገኘው ስሙን "ባሕራን" ብሎ ሰየመውና እንደ ልጁ አድርጐ ይንከባከበው ዘንድ ወሰነ፡፡ ከባሕራን ሀገር የበግ ጠባቂው አገር የዐሥር ቀን ጐዳና የሚያስኬድ ርቀት ነበረው። ከብዙ ዓመታት በኋላ ያ ባለ ጸጋ ሰው ለንግድ ከሀገሩ ወጣ፡፡ በጉዞውም ላይ ሳለ ፀሐይ ስትገባ ከዚያ የበግ ጠባቂው ዘንድ ደረሰ። በግ ጠባቂውንም ‹‹ወንድሜ ሆይ ባንተ ዘንድ የማድርበት ቢኖር ታሳድረኝ ዘንድ እለምንሃለው፣ ኪራዩንም እከፍልሃለው›› ብሎ ጠየቀውና ያ በግ ጠባቂ ወደ ቤቱ አስገባው። ባለጸጋውም ገብቶ ጥቂት ካረፈ በኋላ በግ ጠባቂው ያን ብላቴና ባሕራን ብሎ ሲጠራው በሰማ ጊዜ ‹‹ልጅህ ነውን?›› ብሎ ጠየቀው። በግ ጠባቂውም ‹‹አዎን ይህ አሁን ጐልማሳ ሆኖ የምታየው ወጣት ገና ሕፃን ሆኖ ሳለ በሣጥን ተከቶ ከባሕር ውስጥ ተጥሎ አግኝቼው ወስጄ አሳድጌዋለሁና ልጄ ነው›› አለው። ባለጸጋውም በባሕር ውስጥ የጣለው ሕፃን መሆኑንም ስላወቀ ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደነገጠ፤ ይገድለውም ዘንድ ፈለገ፡፡ በበነጋውም መንገዱን ለመሄድ ሲዘጋጅ ልዩ ልዩ ምክንያት (ሰይጣናዊ ሐሳብ) በመፍጠር በግ ጠባቂውን ‹‹ወንድሜ ሆይ አንድ የማስቸግርህ ጉዳይ አለኝ ይኸውም በቤቴ የረሳሁት ነገር ስላለ ሄዶ መልእክት ያደርስልኝ ዘንድ ይህን ብላቴና እንድትሰጠኝ ነው የድካሙንም ዋጋ ሃያ ወቄት ወርቅ እከፍላለሁ›› አለው። ያም በግ ጠባቂ ስለ ወርቁ ስጦታ ደስ በመሰኘት ያን ጐልማሳ ጠርቶ ‹‹ልጄ ባሕራን ሆይ ይህ ክቡር ሰው ለሥራ ጉዳይ ወደ ቤቱ ሊልክህ ይፈልጋልና መልእክቱን አድርስለት እግዚአብሔር በሰላም ያግባህ›› ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም ‹‹እሺ መልካም ነው አባቴ ሆይ ያዘዝከኝን ሁሉ ለመፈጸም ዝግጁ ነኝ›› አለው። ከዚህም በኋላ ያ ባለጸጋ ‹‹ይህችን የመልእክት ደብዳቤ ይዞ ወደ አንተ የመጣውን ስሙ ባሕራን የተባለውን መልእክቷ በደረሰችህ ጊዜ ፈጥነህ ግደለው፤ ገድለህም ሬሣውን ከጉድጓድ ጣለው እኔ በሰላም ተመልሼ እስክመጣ ድረስ ማንም ማን ይህን ምሥጢር አይወቅ›› የሚል ጽሑፍ ለሹሙ ጽፎ አዘጋጀ፤ በአገልጋዩ (በሹሙ)ና በእርሱ መካከል የሚተዋወቁበትን ማኅተም በደብዳቤው ላይ አትሞ ለባሕራን ሰጠው፡፡ ለመንገዱም የሚሆነው ስንቅ ሰጥቶ ላከው።

ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡ ሃሌ ሃሌ ሉያ ለቤተ ክርስቲያን፤
+5
ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡ ሃሌ ሃሌ ሉያ ለቤተ ክርስቲያን፤ ሐነፃ ላሊበላ ለቤተ ክርስቲያን፡፡ /ወረብ ዘሸዋ፤ በየካ ሚካኤል በሰኔ የሚወረብ የቤቱ የሸዋ ወረብ ቀለም/፤ ዛሬ የሐናፄ መቅዱስ ቅዱስ ላሊበላ(ላልይበላል) ክብረ በዓሉ ነው፡፡ (በአዲስ አበባ የቅዱስ ላሊበላ ክብረ በዓል በየካ ሚካኤልና በአንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚከኤል አብሮ ይከበራል፡፡)

#የመቊጠርያው_መክሊት፡፡ #መሆንና_መምሰል፤ #ሁለቱም_ለየቅል፡፡ በቅብዓ ሜሮን የከበረ መስቀል ከጠረፍ እስከ ጠረፍ እያለ፤ በመቊጠሪያ እናጠምቃለን፥ ተአምራት እንሠራለን የሚሉ በጤናቸው ሆነው ይመስላችኋልን???!!፨ ፠ ልብ ያለው ልብ ይበል፥ በማስተዋል መንገድ ያስተውል፡፡ #መቊጠሪያ_ (Prayer Beads /Rosary/ Ropes) ፠ መቊጠሪያ ፤ ማለት ትርጕሙ ኈለቈ (ቈጠረ) ካለው የግአዝ ግስ የወጣ ሲሆን፣ መቊጠር፥ ፩ድ፣ ፪ት እያሉ መቊጠር፣ አቈጣጠር፤ ቈጠራ ማለት ሲሆን ዋና አገልግሎቱ ለጸሎት ጊዜያት መጸለያነት ነው አባቶቻችን የሚጠቀሙበት ነው፡፡ ፠ ምሳሌነቱም፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ የተገረፈበት ልምጭን በማሰብ በክብ ነገር ተቀርጾ ፥ በገመድ ውስጥ ገብቶ የምንጠቀምበት ነው፡፡ ልክ፤ † የተሰቀለበት መስቀልን፤ በቤተ ክርስቲያን ከጉልላቷ ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች ላይ፣ በካህናት እጅ፣ በዲያቆናት መጾር መስቀል፣ በአንገታችን፣ በልብሳችንና በተለያዩ ነገሮች ላይ እንጠቀመዋለን፤ † የተመታበትን ዱላ፤ በመቋሚያ መልክ እንጠቀምበታለን፤ † የታሠረበትን ጅራፍ፤ በከበሮ ላይ ለመወጠርያነት እንጠቀምበታለን፤ † ያለበሱትን ቀይ ግምጃ /ከለሜዳ/፤ ክቡር ሥጋው በሚቀርብበት ዐውድና ጻሕል፤ ደሙ በሚቀርብበት በጽዋ ላይ በምናለብሰው ማኅፈዳት (ቀይ ግምጃ /አልባሳት/) እንጠቀምበታለን፤ † የታሠረበትን ገመድ፤ በአንገታችን ላይ በማኅተምነት እንጠቀምበታለን፡፡ † በተቀሰቀለ ጊዜ በራሱ ላይ ያቀዳጁትን የሾህ አክሊል፤ በአባቶቻችን መነኰሳት ቆብ ላይ እንጠቀምበታለን፤ † የተገነዘበትን ሰበን በካህናት ጥምጣም ላይ እንጠቀምበታለን፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በየዕለቱ 7ት የጸሎት ጊዜያትን (ነግህ፣ ጠዋት፣ ቀትር፣ ተሰዐት፣ ሠርክ፣ ንዋም፣ መንፈቀ ሌሊት) አውጃለች፡፡ ‹‹ሳታቋርጡ ጸልዩ ፥ በሁሉ አመስግኑ…›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ /1ኛ ተሰ. 5፥18/፤ * በእነዚህ 7ቱ የጸሎት ጊዜያትና በሌሎችም የጸሎት ጊዜያቶች መቊጠርያን አባቶቻችንና እናቶቻችን (በተለይም በገዳም ያሉ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን፤ እናቶቻችንና እኅቶቻችን መነኰሳት) እንዲሁም ቆራብያን ሲጸልዩ ይጠቀሙበታል፡፡ ምክንያቱም፤ ሀ. ሐሳብ ስለሚበዛባቸው፤ በትኩረትና በተመስጦ ሆነው እንዲጸልዩ፡፡ ሁ. ዓለምን በቃኝ ለማለታቸው መለያ፥ ምልክት ስለሆነ፡፡ (ወታደርን ወታደር የሚያስብለው ትጥቅና መለዮው እንደሆነ ሁሉ፤ የመነኰሳት መለያቸው ጭምር ነው፡፡) ሂ. አርድዕት መነኰሳት በሥራ ወቅትና ሌሎችም መነኰሳት በጕዞ ወቅት ከእጃቸው ስለማይለይ የጸሎት ጊዜያታቸውን አሳትውሰው እንዲጸልዩ ስለሚረዳቸው፡፡ ሃ. በየጊዜያቱ የሚጸልዩትን ጸሎት በትክክል እንዲያደርሱና በተለይም ቊጥራቸውን እንዳይሳሳቱ ስለሚረዳቸው ጭምር፡፡ ሄ. በትውፊተ አበው መሠረት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን አብዛኛውን ጊዜ የምንጠቀምባቸው መቊጠሪያዎች በክር ውስጥ ባለ 41 ድብልብል ነገሮች እና ባለ 64 ድብልብል ናቸው ፠ ባለ 41 የመሆኑ ምሥጢር፤ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን 40 ጊዜ ግረፍ የሚለውን የኦሪት ሕግ ተላልፈው አንዱ ደከመኝ ፥ አንዱ ሰለቸኝ፥ አንደኛው ቊጥር ተሳሳተብኝ እያሉ ከ40 በላይ 41 ግርፋትን (6,666ግርፋትን) ለማሰብ፤ ፠ ባለ 64 የመሆኑ ምሥጢር፤ እመቤታችን ድንግል ማርያም በምድር ላይ የኖረችበት እድሜን ለማሰብ ነው፤ ፠፠ አንዳንድ አባቶች ግን ባለ33ት፣ ባለ 150፣ ባለ 300 ድብልብሎች በመቊጠርያ ውስጥ ይጠቀማሉ፡፡ ፠፨፠ መቊጠሪያችንን በ5፣ በ7፣ በ12 ድብልብሎች መካከልም መክፈያ በማድረግ የሚከተሉት ጸሎቶች ይጸለያሉ፡፡ (አጸላለዩ ግን እንደሚጸልየው ሰው ብርታት ሊለያይ ይችላል) ፠ አቡነ ዘበሰማያት፤ በዋነኛነት ይጸለያል (ብዙ ጊዜ 12 ጊዜ ይደገማል) ፠ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ (ብዙ ጊዜ 12(41) ጊዜ) ፠ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ (41 ጊዜ) ፠ ኪርያላይሶን (41 ጊዜ) ፠ ሳዶር ፥ አላዶር፥ ዳናት፥ አዴራ፥ ሮዳስ (5 ጊዜ) ፠ ኦ! አምላክ (41 ጊዜ) ፠ ኦ! ክርስቶስ (41 ጊዜ) ፠ ኤሎሄ (አምላኬ) (41 ጊዜ) ፠ በከመ ምሕረትከ ወአኮ በከመ አበሳነ (እንደ ምሕረትህ እንጂ እንደ በደላችን አይሁን፡፡ (12 ጊዜ) ፠ ተዘከረኒ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ (አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ) (12 ጊዜ) ፠ የእመቤታችን ጸሎት (ሰላም ለኪ) (ብዙ ጊዜ 7፥ አንዳንዶችም 12፥ 64 ጊዜ) ፠፠ ግሁሳን በሃታውያንና መናንያን ግን በግርፋቱ ልክ 6,666 ጊዜ እየቈጠሩ እንዲሁም ከላይ ከተጠቀሱት ስሞች በተጨማሪ ዐረብ የስቅለት የምንላቸውን ስሞች እየጠሩ የሚጸልዩ አሉ፡፡ * ከዚህ በተጨማሪ ግን የራስን የግል ጸሎትን በተጨማሪነት በመቊጠሪያ እየቈጠሩ መጸለይ ይቻላል፡፡ * መቊጠርያን ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን፣ የአንገሊካንናን የሉተራን ፕሮቴስታንቶች ደግሞ በተወሰነ ደረጃ ይጠቀሙበታል፡፡ ከላይ በተዘረዘሩት የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት መሠረት መቊጠርያ ለአባቶች ጸሎት ማድረሻ፣ እንጂ ወጣቶች የሚጸልዩበት፤ አጥማቅያን? የሚያጠምቁበት፣ ባሕታውያን በሕዝብ ፊት ሰውነታቸውን የሚገርፉበት አይደለም፡፡ ታዲያ በአሁኑ ወቅት፤ ፠ <<አጥማቅያን ነን>>!!!??? የሚሉ በቅዱስ ሜሮን የከበረ፥ ሕሙማንን መፈወሻ፥ ተአምር ማድረጊያ የከበረ መስቀል እያለ፤ አጋንንትን በጸሎት ማራቅ እየተቻለ፤ ለምን በመቊጠርያ እየገረፉ እናጠምቃለን፥ በመቊጠርያ እንፈውሳለን እያሉ ያታልላሉ፡፡??? ‹‹ባሕታውያን ነን›› ‹‹ከገዳም ተልከን ነው›› እያሉስ በሕዝብ ፊት ለመታየትና ለውዳሴ ከንቱ በመቊጠርያ ለምን ሰውነታቸውን ይገርፋሉ፤ ያልሆኑትን ለመምሰል፤ (በመቊጠርያ ተአምር ሠሩ ለመባል)፤ አጋንንትን ከሚያስለፈልፉ ዕጽዋት መቊጠርያን በመሥራትን በማስለፍለፍ ተአምራት አደረግን ለማለት፤ በአጋንንት የሠራዊት አለቃ ጭፍሮቹን በማስጮህ ፈዋሽ ለመምሰል፤ (ልብ በሉ የሚይዙት መቁጠርያ በሜሮን ያልከበረ መሆኑን፤ በሌሎች የአባቶች መቊጠርያና በሜሮን በከበረ መስቀል ግን አለመፈወሳቸውን ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡) ከመቊጠርያ ንግድ ገንዘብ ለመሰብሰብ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

በመዲና ከተማችን የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው 28ት (20ት በቅዱስ ሚኤል በዋና መጥርያነት የሚጠሩ፤ 8ት ደግሞ በድርብነት የሚጠሩ) ገዳማትና አድባራትን እንጠቁማችሁ፡፡ /ፎቷቸውን ያልለጠፍናቸውና ስማቸውን ያልጠቀስናቸውን ካሉ እንድትልኩልን በሊቀ መልአኩ ስም እንጠይቃለን፡፡) 1. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ሾላ፤ መገናኛ) 2. *አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል /ጭቁኑ/፤ ፈረንሳይ 3. *ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል (አዲሱ ሚካኤል)፤ አውቶብስ ተራ 4. *ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፤ /ቦሌ/ 5. *ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ 6. *መካኒሣ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል፤ 7. *ኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲምሲ ሚካኤል በመባል የሚጠራ) 8. *አፍሪካ ደብረ ምሕረት ሚካኤል (ከርቸሌ ሚካኤል)( ቀድሞ ወህኒ ቤት ሚካኤል) 9. *ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል 10. *ቤቴል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 11. *ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ 12. *የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል 13. *ሐያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) 14. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ በአዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ፤ ከ110 ዓመታት በፊት የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም መቃኞ ቤት የተተከለበት፡፡) 15. *ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራራ) 16. *ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል 17. *ቃሊቲ ሠፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል 18. *ኤረር (ጎሮ ሰፈር) መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል 19. *ቦሌ በሻሌ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ 20. *ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤል እንዲሁም በድርብነት 1. *እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት 2. *መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ (ስድስትኪሎ) 3. *ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ (መስቀል አደባባይ) 4. *ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ቤ.ክ (ኋላ ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል በሚል እየተጠራ የሚገኘው)፤ (ኢምግሬሽን አጠገብ) 5. *ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ (ኋላ ወመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚል እየተጠራ የሚገኝ) 6. *ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የጠበል ቤቱ ላይ ለብቻው የቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ አለ፡፡) 7. *ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል 8. *ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የመጨረሻው_ክፍል#፲፬ #ንስሐ_መግባት_እንደሚያስፈልግና_ንስሐ_ያልገባ_እንደሚጠፋ፤ #የመጨረሻው_ክፍል #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል#፲፬ ፠ ከሞት የተረፉትን ሰዎች እንዲህ አላቸው፤ እናንተም ንስሐ ካልገባችሁ እንደ እነርሱ ትጠፋላችሁ፡፡ ይህ ክፉና ታላቅ መከራ እንዴት እንደአገኛቸው እስቲ ንገሩኝ፡፡ ከዚህ ዳንስ ቤት ከሚስቶቻችሁ ጋር እንድትገቡ ያዘዛችሁ ማን ነው አላቸው፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት፡፡ በየወሩና በየሳምንቱ ከሴቶቻችሁና ከልጆቻችሁ ጋር ወደ ዳንስ ቤት ሂዳችሁ የሥጋ ደስታ ፈጽሙ ብለው አባቶቻችንና እናቶቻችን ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን አዘዙን አሉት፡፡ ዳግመኛም ከእኛ እያንዳንዱ በዳንስ ቤት የሕግ ሚስቱን ትቶ ከወደዳት ሴት ጋር ይተኛ ዘንድ አዘዙን አሉት፡፡ ፠ አባ ጳውሊም፤ የኀጢኣት ሥራችሁ በጨለማ ነውና ሰው ልጆቹንና ዘመዶቹን ለይቶ እንዴት ሊያውቃቸው ይችላል አላቸው፡፡ ያን ጊዜ ከእኛ አንዱ ስንኳ ልጆቹን ዘመዶቹን ለይቶ አያውቅም፡፡ ማስተዋል እንደሌላቸው እንስሳት እንሆናለን እንጂ አሉት፡፡ ፠ አባ ጳውሊም፤ በዳንስ ቤት ውስጥ ከነበሩት መካከል የዳነ የለምን አላቸው፡፡ እነርሱም ዐሥር ሰዎች ተርፈዋል አሉት፡፡ አባ ጳውሊም ሂዳችሁ ወደእኔ አምጧቸው አላቸው፡፡ እነርሱም ሂደው አመጧቸው፡፡ ፠ አባ ጳውሊም፤ እነዚያን ከሞት የተረፉትን ሰዎች በዳንስ ቤት ያገኛችሁ መከራ እንዴት እንደሆነ አስረዱኝ አላቸው፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት፡፡ ወደ ዳንስ ቤት ገብተን በተሰበሰብን ጊዜ መብራቱን አጠፋን፡፡ ያን ጊዜ ከእኛ እያንዳንዱ በእጁ የገባችውን ሴት ያዘ፡፡ ሳናውቅም በድንገት መብረቅ በረቀ፡፡ ወዲያውም ዓይናችንን ታወርን አእምሯችንንም አጣን፡፡ በዚያን ጊዜ በእባቦች፣ በአንበሶች፣ በጥቋቁር ሰዎች አምሳል ተመስለው አጋንንት በላያችን ላይ ሰፈሩ፡፡ አባ ጳውሊ አዞናልና ያለፈቃዳችን ልናጠፋችሁ ነው አሉን፡፡ ከእኛ ዐምስት ወንዶችና ከዐምስት ሴቶች በስተቀር የተረፈ የለም አሉት፡፡ በዚያ የተሰበሰቡ የሀገሩ ሰዎችም ስለዘመዶቻቸው የአሟሟት ሁኔታ በሰሙ ጊዜ ሩጠው አባ ጳውሊን ይዘው እንዲህ አሉት፡፡ አባቶቻችንና ወንድሞቻችንን ዘመዶቻችንና ልጆቻችንን ሚስቶቻችንንም ያጠፋህ አንተ ከሆንክ እኛም አንተን እንደነሱ እናጠፋሃለን አሉት፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጳውሊም፤ እናንተ የእፉኝትና የእባብ ልጆች ኀያሉ ልዑል እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ሳለ በእኔ ላይ ክፉ ነገር ማድረግ እንደምን ይቻላችኋል አላቸው፡፡ ይህንን ነገር ሲናገራቸው ከፊቱ ወድቀው እንደ ሞተ ሰውም ሆኑ፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጳውሊ፤ በጸሎቱና በእግዚአብሔር ኀይል ከወደቁበት አነሳቸው፡፡ እነርሱም ወዲያው እንደተነሡ አቤቱ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ይቅር በለን ሕይወታችንን ከዚህ ዓለም አታጥፋ ብለው ወደ እርሱ ጮኹ፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጳውሊም፤ ከረከሰና ከክፉ ሥራችሁ ተመልሳችሁ በእኔ አምላክ ካላመናችሁ እናንተም እንደ እነርሱ ትጠፋላችሁ አላቸው፡፡ ያን ጊዜ ሁሉም አንድ ሁነው ቃልህን አንተላለፍም ያዘዝከንን እናደርጋለንና እንደወደድክ እዘዘን አሉት፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጳውሊም፤ አስቀድመው የሞቱ ወገኖቻቸውን እንዲቀብሩ አዘዛቸው፤ እንዳዘዛቸውም አደረጉ፡፡ ከዚህ በኋላ እውነተኛውን የክርስትና ሃይማኖት አስተማራቸው፡፡ ለቅዱስ ስሙ ክብርና ምስጋና ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም (የባሕርይ አምላክነት) አመኑ፡፡ ከዚህ በኋላ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስም ስም አጠመቃቸው፡፡ ሥጋውና ደሙን አቀበላቸው፡፡ ፍጹም ክርስቲያን ሆኑ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ በዓቱ ተመልሶ በመጾምና በጸሎት ሲጋደል ኖረ፡፡ መልካም ተጋድሎውን ፈጽሞ ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብሎ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ዐርፎ ወደ እግዚአብሔር ሄደ፡፡ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ ተፈጸመ፡፡ የአባ ጳውሊ ጸሎቱና በረከቱ ከሰይጣን ተንኮልና ወጥመድ ሁላችንም ሕዝበ ክርስቲያን ይጠብቀን፡፡ አሜን፡፡ ሰላም ለአባ ጳውሊ፤ ዘንጉሥ ወዓሊ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ፤ ርዕሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም፡፡ ትርጕም፦ በበረሃ ላሉ ባሕታውያን(መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል፡፡ ፠፠ ምንጫችን፤ * ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን በሚል ርዕስ ከግእዝ ወደ አማርኛ ያሳተመው መጽሐፍ፣ * ዜና አበው ግእዝ በግእዝ መጽሐፍ * ፍኖተ ቅዱሳን /FINOTE KIDUSANZETWAHIDO እና ዋልድባ ዋሊ የቴሌግራም ገጽ፡፡ ** ሰ/ት/ቤታችን የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወትም ለአነባብ እንዲመች በ፲፬ት ተከታታይ ክፍል ከፍለንና አዘጋጅተን ያቀረብንላችሁን እንደ መዐር የጣፈጠ፥ እንደ ጭማቂ የተጨመቀ ጣፋጩን ተዋስኦት (ቃለ መጠይቅ) ጨረስን፤ በጸሎት የበረታችሁ ሰ/ትቤታችንን አስቡልን፡፡ የተጻፈውን ትምህርትም እንድንጠቀምበት፤ ለሌሎችም እንድንተርፍበት የአምላካችን ፈቃዱ ይሁን፡፡) ፠ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ እኛ ሁላችንም ሕዝበ ክርስቲያንን ይማረን፥ ይጠብቀን፡፡ ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ በእውነት ይሁን ይደረግ አሜን፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

አንብብዋ ለዛቲ ጦማር እምጥንታ፥ እስከ ተፍጻሜታ፤ በትዕግስት (ይህችን ጽሑፍ በትዕግስት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንብቧት)፤ ብዙ የብዙ ብዙ ጥቅም ታገኙበታላችሁና፡፡ #በኋላ_ዘመን_መነኰሳትን_ሰይጣን_በምን_ዓይነት_ሁኔታ_እንደ_ሚበረታባቸው፤ #በሰሉቅያ_ሃገር_ያሉ_በዝሙትና_በዳንስ_ቤት_ውስጥ_በሚሠራ_ርኵሰት_የሚደርስ_ቅጣትና_መከራ፡፡ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲፫_ ፠ አባ ጳውሊ፤ መልአኩን ሰይጣን ኀጢኣት ይሠራሉና ለወንድሞችህ መነኰሳት አልቅስ ብሎ የነገረኝ እውነት ነውን አለው፡፡ መልአኩም አዎ በኋላ ዘመን ከመነኰሳት መካከል ተለይተው ኀጢኣት የሚሰሩ አሉ፡፡ ኀጢኣት የሚሰሩበትም ምክንያት ይህ ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር ከምታደርሳቸውና የዘለዓለም ሕይወትን ከሚያገኙባት መልካም ሥራ ሁሉ ልቡናቸው ይርቃል ፤ ይደክማልና ነው፡፡ የቀደሙ የአበውንና የቅዱሳንን ሕግና ሥርዐትም አይጠብቁምና፡፡ የአበው ቅዱሳን ፥ ጻድቃንም ሥርዐታቸው ትሕትናና ታዛዥነት ፤ ፍቅርና ሰላም ፤ ጾምና ጸሎት ፤ ጥሪት ቁሪት አለማበጀትና ገንዘብ አለመውደድ፤ መረጋጋት ትዕግሥትን ማዘውተር፤ ውዳሴ ከንቱን መጥላት፤ የነፍስና የሥጋ ንጽሕና ይህንን የመሰለ ነው አለው፡፡ በኋላ ዘመን መነኰሳት ተድላና ደስታ በመፈለግ ገዳማዊነታቸውን ይተዋሉ፡፡ ተጋዳዮችና ደጋጎች የሆኑ አባቶቻቸው በሕይወተ ሥጋ ሳሉ በሠሩላቸው ሥርዐት ጸንተው አይኖሩምና፡፡ መነኰሳት ሲሆኑ በገድል ጽሙዳን በሆኑ መነካሳት ወንድሞቻቸው ላይ ይዘባበታሉ፡፡ ስለዚህ ያን ጊዜ ብዙ ገዳማትና አድባራት ይደክማሉ ፤ ብዙዎችም ይጠፋሉ ፤ ነገር ግን ጥቂቶቹ በእግዚአብሔር ፈቃድና በደጋጎቹ ቅዱሳን ቃል ኪዳን ይጠበቃሉ፡፡ ፠ ዳግመኛ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ አባ ጳውሊን እንዲህ አለው፤ በኋላ ዘመን ክፉ ዘመን እንደሚመጣ አስቀድሜ ብነግርህም ከሊቃነ ጳጳሳትና ከካህናት ከምእመናንና ከመነኰሳት መካከል በትዕግሥታቸውና በመልካም ሥራቸው በሃይማኖታቸው ጸንተው የእግዚአብሔርን ሕጉንና ትእዛዙን ጠብቀው የሚኖሩ ተጋዳዮች ንጹሖች እውነተኞች ደጋጎች አሉና፡፡ በበደለኞችና ኀጢአት አዘውትረው በሚሠሩ ተስፋ እንዳይቆርጡ ፤ ምድራዊ የሥጋ አኗኗራቸውን አይተው በደለኞችን እንዳይከተሉ ነገር ግን ታግሠው ነፍሳቸውን እንዲያድኑ ፤ ሌሎችንም መክረው አስተምረው በንስሐ ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመልሷቸው ፤ ለሚሰሙትና ለሚያነቡት ከኀጢአት ለመጠበቅ ለማስተዋል ለንስሐ ነፍስና ሥጋን ለመጥቀም ረዳትና አጋዥ እንዲሆን ጠላት ዲያብሎስ የነገረህን ሁሉ ጻፍ አለው፡፡ ፠ "ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ አባ ጳውሊን አስቀድመህ ተነስተህ ወንድሞችህ ተኝተው ወደ አሉበት ሂድ፡፡ ኋላ ወደ ሀገሩ ሰዎች ሂደህ በዚያም ሰይጣን የነገረህን ሁሉ ንገራቸው፡፡ ከክፉና ከረከሰ ሥራቸው እንዲመለሱ ምከራቸው አስተምራቸው፡፡ እነርሱ በአንተ ትምህርት ይመለሳሉና፡፡ ጥንቱንም እውነተኛ የክርስትና ሃይማኖት የላቸውምና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቃቸው፡፡ እግዚአብሔር ነብዩ ሕዝቅኤልን በአሕዛብ መካከል ርኵሰታቸውን ሁሉ ይናገሩ ዘንድ ከሰይፍና ከረኃብ ከቸነፈርም ጥቂቶች ሰዎችን ከእነርሱ አስቀራለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ ብሎ እንደተናገረው ፤ (ሕዝ.፲፪:፲፮) ከሞት የዳኑት ሰዎች በወገኖቻቸው ላይ ስለተደረገው ነገር ምስክር ይሁኑ፡፡ ስለሞቱት ሰዎችም አትዘን እንደ ሥርዐቱ ቅበራቸው እንጂ አለው፡፡ አባ ጳውሊም ሂዶ መነኰሳት ወንድሞች ካሉበት ሲደርስ ተኝተው አገኛቸው፡፡ እነርሱ ሳያውቁ ቀድሞ ተኝቶ ከነበረበት ቦታ ገብቶ ዐረፈ፡፡ በነጋ ጊዜ የሀገሩ ሰዎች በዳንስ ቤት የሆነውን ነገር ሰሙ፡፡ ሀገሩ በሙሉ በልቅሶና በኀዘን ድምፅ ታወከ፡፡ ፠ አባ ጳውሊም፤ ለወንድሞቹ መነኰሳት የዚህች ሀገር ሰዎች የሚያለቅሱበትን ምክንያት አውቃችኋልን አላቸው፡፡ እነርሱም የሆነውን አላወቅንም አሉት፡፡ ከእርሱ ጋር የነበረውን ዲያቆን ጠርቶ ልጄ! ወደ እነዚህ ሰዎች ሂደህ የሚያለቅሱበትንና ይህ ታላቅ መከራ በምን እንዳገኛቸው ተረድተህ ወደ እኛም ተመልሰህ የሆነውን ንገረን አለው፡፡ ያም ዲያቆን ወደ ሀገሩ ሰዎች ሂዶ ይህ በእናንተ የሆነው ምንድን ነው አላቸው፡፡ ወንድማችን! በዚህች ሌሊት ያገኘንን መከራ አልሰማህምን አሉት፡፡ ያም ዲያቆን እኛ የገዳም ካህናት ነን ከገዳሙ ተልከን ወደ ተላክንበት ስንሄድ ከዚህች ሀገር ስንደርስ መሸብን፡፡ እነሆ ዛሬ በዚህች ሀገር አደርን፡፡ ነገር ግን በውስጧ የሆነውን አላወቅንም አላቸው፡፡ ከእነርሱም አንዱ ከመፍራቱና ከመደንገጡ የተነሣ እየተንቀጠቀጠ እንዲህ አለው፡፡ ወንድሜ ሆይ ሂደህ ወንድሞችህ መነኰሳትን ኑ ከእኛ ጋር አልቅሱ ብለህ ጥራቸው፡፡ ወይም አባቶቻችንንና ወንድሞቻችንን ያገኛቸው ታላቅ መከራ እንዳያገኛችሁ ርቃችሁ ሂዱ በላቸው አለው፡፡ ረድኡም ያ ሰው ያለውን በሰማ ጊዜ ፈጥኖ ሂዶ ለመነኰሳት ወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ ፠ አባ ጳውሊም ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ወንድሞች ሆይ ሙታንን ከመገነዝ ወደ ኋላ ማለት ስለማይገባ መልካም ሥራ እንሠራ ዘንድ ፈጥነን ወደ እነርሱ እንሂድ፡፡ የሚገባ መልካም ሥራ ነውና አላቸው፡፡ እነርሱም እሺ እንሂድ አሉት፡፡ አባ ጳውሊም ከእነርሱ ጋር የሀገሩ ሰዎች ወደ አሉበት መንደር ሂዶ የሞቱት ሰዎች ወደ የት ነው ያሉት አላቸው፡፡ ከሞት የዳኑት ሰዎችም ወንድማችን በዚህ ዳንስ ቤት በወገኖቻችን የደረሰውን ታላቅ መከራ ናና እይ አሉት፡፡ አባ ጳውሊና መነኰሳት ወንድሞቹ ሂደው ከዳንሱ ቤቱ በር በደረሱ ጊዜ ያ ዲያቆን አስቀድሞ ገባ፡፡ ያም ዲያቆን አባ ጳውሊን መምህር ሆይ ወንዶችና ሴቶች ከአንድ ላይ እያሉ የልዑል እግዚአብሔር መዓት ስለደረሰባቸው ሁሉም አንድ ላይ ሙተዋልና ወደ ውስጥ አትግባ አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊም መለሰ ዲያቆኑን እንዲህ አለው፡፡ እነዚህን ሰዎች ይህ መከራ በምን እንደ አገኛቸው ተረዳ አለው፡፡ ዲያቆኑም በዳንስ ቤቱ የሆነውን ሊያይ ተመልሶ ገባ፡፡ ዲያቆኑም ወደ ዳንስ ቤቱ በገባ ጊዜ በሩካቤ ኀጢኣት እርስ በርሳቸው እንደተያያዙ ሙተው አገኛቸው፡፡ ሰውነታቸውም በቁስል የተመታና በእሳት የተቃጠለ ስለሆነ ከእነርሱ አንዱን ስንኳ ከወንዶችና ከሴቶች ማን እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ፠ አባ ጳውሊም ባያቸው ጊዜ ታላቅ ኀዘን አዘነ፡፡ ካዘነም በኋላ ስለእነዚህ ስለሞቱ ሰዎች ልናለቅስ አይገባም፡፡ ከእኛ እያንዳንዱ ስለራሱ ኀጢኣት ያልቅስ እንጂ አለ፡፡ #ንስሐ_መግባት_እንደሚያስፈልግና_ንስሐ_ያልገባ_እንደሚጠፋ፤ …….. ክፍል ፲፬ና የመጨረሻው ክፍል.… ይቀጥላል ይጠብቁን/

#በኋላ_ዘመን_ሰይጣን_ለምን_ኃይሉንና_ክፋቱን_እንደሚገለጽና_እንደሚበረታ_፤ ሰይጣን ደቃዱን ለሚፈጽሙት ሰዎችም እንደማይጠቅማቸውና ይቅርታና ምሕረት እንደሌለው …. ያንብቡ፡፡ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲፪_ ፠ አባ ጳውሊ፤ ፈቃድህን ያደረጉ ክፉዎች ሰዎችን እንድታጠፋቸው የታዘዝክበት ጊዜ ደርሷልና በዚህ ዳንስ ቤት ፈቃድህን በፈጸሙ ሰዎች ላይ ምን ለማድረግ ታስባለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ ለትእዛዝህ የተገዛሁ ነኝ፡፡ ጸሎትህ አስሮ ስለያዘኝ እስከአሁን ድረስ ቆይቻለሁና እንደ አዘዝከኝ አደርጋለሁ አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ የታዘዝከውስ በዳንስ ቤት ያሉትን ሰዎች ለሌሎች አርአያ እንዳይሆኑ እንድትገላቸው ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተ ክፉ ሽማግሌ ለነዚህ ሰዎች ለምን አታዝንላቸውም አትራራላቸውም አንተ መንፈሳዊ የደጋጎች ወገን ነህና አለው፡፡ #አባ ጳውሊ፤ #ፈቃድህን ለሚፈጽሙ ሰዎች እንደማትጠቅማቸውና ይቅርታና ምሕረት እንደሌለህ ሌሎች አውቀው ከአንተ እንዲሸሹ ይህንን ጥፋት እንድታደርግባቸው እሻለሁና የታዘዝከውን ፈጥነህ አድርግ፡፡ ነገር ግን በወዳጆችህ ይህንን ክፉ ሥራ እንዳደረግህ ምስክር እንዲሆኑ ከእነርሱ ዐሥር ሰዎችን አስቀር አለው፡፡ ሰይጣንም አባ ጳውሊን እነዚህን ሰዎች አጠፋቸው ዘንድ ከዳንስ ቤቱ በር አካባቢ ርቀህ ሂድልኝ አለው፡፡ ያን ጊዜም አባ ጳውሊ የመላእክት ጌታ ሆይ አገልጋይህን ከሰይጣን እጅ አድን ብሎ ጸለየ፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ ወደ ሰይጣን በተመለከተ ጊዜ ሁለት የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ መልኩ ተለውጦ እንደሚነድ እሳት ሁኖ አየው፡፡ ያን ጊዜ ሰይጣን፤ ሰዎች በኃጢአት ሥራ ወደ አሉበት ወደ ዳንስ ቤቱ መካከል ገባ፡፡ ያን ጊዜ አጠፋችሁ ዘንድ ታዝዣለሁና በሁላችሁም ላይ መጣሁባችሁ እያለ እንደ መብረቅ በታላቅ ድምፅ እየጮኸ ሲናገር ተሰማ፡፡ ያን ጊዜ ከመከራቸው ጽናት የተነሣ የዳንስ ቤቱ ጩኸት ከፍ ብሎ ተሰማ፡፡ ጩኸታቸውም እንደ ብዙ ገበያ ሕዝብ ከርቀት ይሰማ ነበር፡፡ ሁሉም በዳንስ ቤት ያሉት በክፉ አሟሟት ሞቱ፡፡ ከእነርሱም መካከል ከዐምስት ወንዶችና ከዐምስት ሴቶች በስተቀር ሌላ የተረፈ የለም፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ አባ ጳውሊ፤ ከዳንስ ቤቱ በር ርቆ ሄደ፡፡ እየሄደም ሳለ አቤቱ ሰይጣናት በእኔ ላይ እንዳይሰለጥኑ አትተወኝ፡፡ በጽኑዕ ሥልጣንህና በይቅርታህም ክንፍ ሰውረኝ እያለ ጸለየ፡፡ ከዚህ በኋላ ለቅዱስ አባ ጳውሊ በሚያምር ጎልማሳ አምሳል የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለት ፤ እንዲህም አለው፡፡ እነሆ ከዚህ ሸንጋይና ቀናተኛ ርኵስ ከሆነ ጠላት እንድጠብቅህና እንዳድንህ መሐሪና ይቅር ባይ አምላክ ልኮኛልና የተባረክ ቅዱስ አባት ሆይ ከእነዚህ ርኵሳን አጋንንት የተነሳ አትፍራ፡፡ የጠየቅኸውን በሙሉ እውነቱን እንደነገረህ ዕወቅ፡፡ ክፉ የማሳት ሥራውን ከአንተ ምንም አልሸሽገብህም፡፡ የነገረህን በሙሉ ለሁሉ ሰው እንዲደርስና ትምህርት እንዲሆን ጻፍ፡፡ ዲያብሎስ ይህን የነገረህን የማሳትና የክፋት ወጥመድ በዚህ ትውልድ አብዝቶ አያደርገውም፡፡ ነገር ግን ከብዙ ዘመን በኋላ አብዝቶ ይፈጽመዋል ፤ ያደርገዋልም አለው፡፡ #አባ ጳውሊም መልአኩን ሰይጣን በኋላ ዘመን ኃይሉንና ክፋቱን መግለጽና መበርታት የሚችለው ስለምንድነው ነው አለው፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤልም ለአባ ጳውሊ እንዲህ እያለ ይነግረው ጀመር፡፡ #የሰው_ሁሉ_ኅሊና_በየጊዜውና_በየሰዓቱ_እግዚአብሔርን_ከማሰብና_ከመልካም_ሥራ_ሁሉ_ስለሚርቅና_ስለሚሰንፍ_ነው_አለው_፡፡ (መዝ.፲፩:፪ ፤ ማቴ.፳፬:፲ ፤ ፩ጢሞ.፬:፩) በኋላ ዘመን ብዙዎቹ የቀናች ሃይማኖታቸውን ትተው በማወቅም ባለማወቅም የአጋንንትን ትምህርት ይከተላሉ፡፡ በኋላ ዘመን ሰዎች ራሳቸውን ወዳድ የኃጢአትን ተድላ ደስታ የሚወዱና ከእግዚአብሔር ፍቅር የራቁ ይሆናሉ፡፡ (፪ጢሞ.፫:፬) ሁላቸውም ገንዘብ ወዳጆች ይሆናሉ፡፡ ብዙ ገንዘብ ቢሰበስቡም አይበቃቸውም፡፡ እነርሱም ይበቃናል አይሉም፡፡ በሰማይና በምድር የተመሰገነ እግዚአብሔርንም ፈጽመው አያመሰግኑትም፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ለአባ ጳውሊ መናገሩን ቀጠለ፤ በኋላ ዘመን ዘወትር እየተማሩ እየተገሠጹ እያለ አያስተውሉም ፤ ከጥፋትም አይመለሱም ፤ እውነትንም ፈጽመው አያውቋትምና፡፡ (፪ጢሞ.፫:፯) ብዙ መምህራንና መጻሕፍት በእነርሱ ዘንድ እያሉላቸው የሐሰተኞች መምህራንን ትምህርት ለመስማት ገሥግሰው ይሄዳሉ፡፡ (ማቴ.፳፬:፲፩) በኋላ ዘመን ሰው ሁሉ የማይጠቅም ተአምራትና ምልክትን ይፈልጋልና፡፡ ሰዎች ምልክት በመፈለጋቸው ምክንያት ሰይጣን የሚፈልጉትን በማስመሰል በምትሐት ያሳስታቸዋል፡፡ በኋላ ዘመን ሰይጣን በብዙ ሰዎች ልቡና ቊጥር የሌለው ብዙ እንክርዳድን ይዘራልና፡፡ (ማቴ.፲፫:፳፭) ይህም ትዕቢት ፣ ኩራት ፣ የምንዝር ጌጥ መውደድ ፣ መመካት ፣ ዝሙት ፣ ቅንአት ፣ ቂም በቀል ፣ መናፍቅነት ፣ ስንፍና ፣ ሌብነት ፣ ነገረ ሰሪነት ፡ ራስ ወዳድነት ፣ ነፍሰ ገዳይነት ፣ በነፍስም በሥጋም የሚያጸይፍ የኃጢአት ሱስን መውደድ ይህን የመሰለ ነው አለው፡፡ # በኋላ ዘመን መነኰሳትን ሰይጣን በምን ዓይነት ሁኔታ ይበረታባቸዋል፤ …….. ክፍል ፲፫ .… ይቀጥላል ይጠብቁን/

አንብብዋ ለዛቲ ጦማር እምጥንታ፥ እስከ ተፍጻሜታ፤ በትዕግስት (ይህችን ጽሑፍ በትዕግስት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንብቧት)፤ ብዙ ጥቅም ታገኙበታላችሁና፡፡ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲፩_ #ሰይጣን_በውኃ_ምንጮች_ለምን_እንደሚያድር፤ #ነገሥታት_መኳንንትንና_መሣፍንትን_በምን_እንደሚፈትናቸው፡፡ #ጳጳሳትንና_መነኰሳትን_በምን_እንደሚፈትናቸው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ በውሃ ምንጮች እንደምታድሩ ሰዎች የሚናገሩት እውነት ነውን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ እውነት ነው አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ የምታድሩት በምን ምክንያት ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ የፈጣሪያቸውን ሕጉንና ትእዛዙን ቢያፈርሱና ስሙንም ባይጠሩ፥ የእኛን ፈቃድ ቢፈጽሙ፥ በስማችን ጠርተው ቢያመልኩን ነው እንጂ፤ በመልካም ምግባር ሆነው በፍጹም ሃይማኖት የእግዚአብሔርን ስም ቢጠሩ ኃይል የለንም፡፡ #እኛ_ብዙ_ዓይነት_በሽታን_አእምሮ_ማጣትን_እብደትን_እናመጣለን፡፡ #ሰውን_ባሳመምነው_ጊዜ_ሄዶ_በእኛ_ስም_ሲጠመቅ_ከበሽታው_ይድናል፡፡ #በዚህም_ስመ_ክርስትናው_ትጠፋለች፡፡ #ሰዎች_የታመመው_ሲድን_ባዩና_በሰሙ_ጊዜ_እኛን_ያመልካሉ፡፡ #ባላወቋት_መንገድ_አሳስተን_እናጠፋቸዋለን፡፡ #መንፈሳውያንን_መንፈሳዊ_በማስመሰል_እናጠምዳቸዋለን፡፡ #መንፈሳዊ_በሚመስል_ነገር_የተጠመዱ_ከእኛ_አያመልጡም_አለው፡፡ /ማቴ.፯፥፲፭፤ ፳፬፥፲፩/ ፠ አባ ጳውሊ፤ አስቀድመህ ለነገሥታት፥ ለመኳንንት፥ ለስልጣናት፥ ለታላላቆቹ ለመሳፍንት፥ ለሊቃውንት አልቅስ ያልከኝ ስለምንድን ነው አለው፡፡ ሰይጣን፤ ሹመታቸው ታላቅ እንደመሆኑ ኃጢአታቸውም ብዙ ነውና፡፡ በሹመት ራስን ከፍ ማድረግን፥ ውዳሴ ከንቱን፥ ትምክሕትን፥ ትዕቢትን እናመጣባቸዋለንና፡፡ መሻርን መድከምን ሞትን እንዳያስቡ እናደርጋቸዋለንና፡፡ ቀናውን ፍርድ ትተው በመማለጃና በአድልዎ እንዲፈርዱ፤ የማስተዋል አእምሯቸውን እናጠፋዋለንና፡፡ እውነተኛውን ፍርድንና ቀናውን መንገድ ይተዋሉ ፤ ስለዚህ ዘወትር ድሆችን፥ ደካሞችን ያስለቅሳሉ፡፡ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ፈቃድ እናርቃቸዋለን ፤ ስሙን እንዳይጠሩ እናደርጋቸዋለን ፤ ትምክሕትን፥ ትዕቢትን፥ ገንዘብ መውደድን በልባቸው እናሳድርባቸዋለን፡፡ በዚህ ምክንያት ጦርነት አሥነስተው እርስ በርሳቸው ይጋደላሉ ፤ የእነርሱ መከራ ለታላቁም ለታናሹም ለሀገሩ ሁሉ ይተርፋል፡፡ በኃጢአታቸውም ይጠፋሉ አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ፤ በሊቃነ ጳጳሳት ፥ በጳጳሳት ፥ በኤጲስ ቆጶሳትስ ላይ ምን ምክንያት አግኝተህ ትዋጋቸዋለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ ከሁሉ አብልጠው ብርን ፥ ወርቅን ፥ ገንዘብን እንዲወዱ አደርጋቸዋለሁ፡፡ #ለማይገባው ሥልጣነ ክህነትንም በገንዘብ እንዲሰጡ ፤ ለነዳያን ለድሆች እንዳያዝኑ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ለሌላው የሚያስተምሩትን የሕጋቸውን ጎዳና እንዳያስተውሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ዘወትር ኃላፊውን የምድር ተድላ ደስታ እንዲያስቡ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ጠብን ፥ ጥላቻን በልቡናቸው አሳድራለሁ ፤ አንዱ ጓደኛውን በቅናት እንዲከሰው አደርጋለሁ፡፡ #ለጸሎትም በቆሙ ጊዜ ጠባቸውን እንዲያስቡ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ቂማቸውን እንዳይረሷዋትም አንዱ ባልንጀራውን እንዲረግም አደርጋቸዋለሁ፡፡ #ኃላፊውን ገንዘብ ለመሰብሰብ እንዲተጉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት እኔ የማሳያቸውን የልብስ ዓይነት የልብስ ይለብሳሉ፡፡ ዳግመኛም በገዳም የሚኖሩትን መነኮሳት አብልጬ እጣላቸዋለሁ፤ የኅሊና ጦር አመጣባቸዋለሁ፡፡ #ከእንቅልፍ_በነቁ_ሰዓት_ወይም_ለጸሎት_ሲነሡ_የውዳሴ ከንቱና የቅንዓት የትምክሕት ሐሳቦችን አመጣባቸዋለሁ፡፡ ድካማቸውን ከንቱ አደርጋለሁ፡፡ በጾማቸውና በተጋድሏቸው እንዳይጠቀሙ አደርጋቸዋለሁ፡፡ #በበአታቸው_በአንድ_ቦታ_እንዳይጸኑ_አደርጋቸዋለሁ፡፡ በሥራ ላይ ያሉትንም ሥራቸውን እንዲያመልኩና እኔ እበልጣለሁ እንዲሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በዚህ ሥራቸው ትቢትን ፥ ትምክሕትን ፥ ውዳሴ ከንቱ አመጣባቸዋለሁ፡፡ #የዚህ_ዓለም_ተድላና_ደስታ_እንዲወዱ በማድረግ እዋጋቸዋለሁ፡፡ #የውሸት_ሕልም_በማሳየት አሳስታቸዋለሁ፡፡ #የመምህሮቻቸውን_ትእዛዝ_እንዳይቀበሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ከልባቸው ትሕትናንና ታዛዥነትን የምትጠቅም#የአበውን_ምክር_መስማትን_አጠፋባቸዋለሁ፡፡ እንደ መቃብር በውጫዊ እይታቸው ያማሩ በውስጣቸው ግን ኃጢአትን ርኵሰትን የተሞሉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ አንድ ስንኳ ሳላስቀር ከእግዚአብሔር ቸርነት ፈጽሜ እስከ ማርቃቸው ድረስ ባለኝ ዐቅሜ ሁሉ እዋጋቸዋለሁ፡፡ እነሆ የጠየቅኸኝን ክፉ የሆነች የማሳት ምስጢሬንና የክፋት ሥራዬን ሁሉ ምንም ሳልደብቅህ ያለ ፈቃዴ ነገርሁህ አለው፡፡ #ቅዱሳን ሰይጣንን እንደሚያዙት፤ ቀሲስ አባ ጳውሊ የሰይጣንን ምሥጢር ስላውጣጣው እንዳይተናኰሉት ስለመጠየቁና የነገሩት እውነት መሆኑን፤ የነገሩትም ወደፊት እንደሚፈጸምና በጽሑፍ እንዲቀመጥ ማድረጉን…….. ክፍል ፲፪.… ይቀጥላል ይጠብቁን/

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፲_ 👉 #ሰይጣን ያልበደሉትን ሰዎች ለምን እንደሚፈትናቸው፤ በኋላኛው ዘመን ደጋግ ነገሥታትና መኳንንት፤ ንጹሐን ካህናት ፥ ሊቃውንትና መምህራን ፤ ጳጳሳትና ቆሞሳት እንደሚታጡ፤ መነኰሳትም የሰይጣን ወዳጅ እንደሚሆኑና ይህን ለማራቅ መጸለይ እንደሚገባ፡፡ † አባ ጳውሊ፤ አንተን ያልበደሉህን ሰዎች እንዲህ የምታደርገው ለምንድን ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሃይማኖታቸው የቀና፥ ሥነ ምግባራቸው ያማረ ስለሆነ እንቀናባቸዋለን፡፡ ስለዚህ አሕዛብ ክፉ ሥራቸውን አይተው ሃይማኖታቸውን እንዲነቅፏት ለማድረግ ነው አለው፡፡ † አባ ጳውሊ፤ ከሕይወትና ከመልካም ሥራ የተለየህ ክፉ ባላጋራ፤ ኀጢአት በእነርሱ ላይ ከወዴት ትመጣለች? የዓመፅ መገኛ፥ የኃጢአት መኖሪያ፥ የጽድቅ ጠላት አንተ ነህ እንጂ አለው፡፡ /ዮሐ.፰፥፵፫/ ዲያብሎስ፤ የዓመፅና የክፋት ሁሉ መገኛ ብሆንም፤ የኀጢአት ፈጻሚዋ እኔ ብቻ አይደለሁም፡፡ #የማቀርብላቸውን_የክፋት_ሥራ_ካልተቀበሉኝ_እነርሱን_በኃይል_ማስገደድ_አይቻለኝም፡፡ ነገር ግን በብዙ ዘዴና ተንኮል ሥራዬን እንዲቀበሉ አቀርብላቸዋለሁ፡፡ #ለመልካም_ሥራ_መንፈሳዊና_አስተዋይ_ካልሆኑ የክፋት ሥራዬን ሳይመረምሩ ይቀበሉኛል፡፡ እነርሱን ለማሳት አመች ጊዜና ወቅት ሳገኝ ከመልካም ሥራ ሁሉ አርቃቸዋለሁ፡፡ በክፉ ሥራ ፈጽሜ እገዛቸዋለሁ፡፡ ለእያንዳንዳቸው በመካከላቸው ዘወትር ጠብ፥ ክርክር ይሆናል፡፡ የነፍሳቸውንና የሥጋቸውን ረብ ጥቅም አጠፋለሁ፡፡ ቃሌን ትእዛዜን አንቀበልም ብለው ቢያሸንፉኝ #በትንሽ_ኃጢአት_እቀርባቸዋለሁ፡፡ በልቡናቸው ሐሜትን፥ ነቀፋን አሳድርባቸዋለሁ፡፡ በመሥዋዕቱ ፊት በቤተ መቅደስ የማይገባ ሥራ እንዲሠሩና እንዲናገሩ አደርጋቸዋለሁ፡፡ በክፉ ሥራቸው ፈጽሞ ደስ ይለኛል፡፡ ዳግመኛ #ሕዝቡ_ቀሳውስቱንና_ካህናቱን_ሊቃውንቱንም_እንዲነቅፉ_አደርጋለሁ፡፡ ሁላቸውንም ከጽድቅ ሥራ ሰንፈው ለኃጢአት ሥራ እንዲተጉ አደርጋቸዋለሁ፡፡ ንስሐ እንዳይገቡ በውስጣቸው ፍርሐትን ፥ ትምክሕትን ፥ ስንፍናን አሳድርባቸዋለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት የወንድሞቻቸውን ኀጢአት እንጂ የራሳቸውን ኀጢአት አይናዘዙም፡፡ በዚህ ምክንያት ለበደላቸው ስርየት የለውም፡፡ ከኀጢአት እንዳይርቁ በእነርሱ ላይ የማላመጣው ምክንያት የለም፡፡ ምክሬን ከሰሙኝ ፈጽሜ የክርስቶስን ጸጋ አሳጣቸዋለሁ አለው፡፡ † አባ ጳውሊ፤ ይህንን ሰምቶ ፈጽሞ አለቀሰ፡፡ ሰይጣንም፤ አባ ጳውሊ ሲያለቅስ ባየ ጊዜ ደስ አለው፤ ይስቅበትም ጀመር፡፡ እንደ አንተ ካህናት ናቸውና ስለ እነርሱ ታለቅሳለህን አለው፡፡ በእውነቱ ማልቀስ ከወደድክ ስለ ደጋግ ነገሥታትና ስልጣናት ፥ ስለ መኳንንትና ስለ ሊቃውንት ፥ ስለ መሳፍንትና ስለ ገዢዎች መታጣት ፊትህን ጸፍተህ አልቅስ፡፡ ዳግመኛም ስለ ንጹሐን ሊቃነ ጳጳሳትና ስለ ኤጲስ ቆጶሳት ፥ ስለ ቆሞሳትና ስለ ሁሉም ደጋግ ንጹሐን ካህናት መታጣት አልቅስ፡፡ አብዝተህም ስለ ቤተክርስቲያንና ስለ ገዳማት አልቅስ፡፡ ይልቁንም በገዳማት ስለሚኖሩ ስለወንድሞችህ መነኰሳትና ስለ እኅቶችህ መነኰሳይያት ፈጽመህ አልቅስ፡፡ #በኋላ_ዘመን_ዘመዶቼና_ወዳጆቼ_አደርጋቸዋለሁና_አለው፡፡ † አባ ጳውሊ፤ በምን ሥራ እንዲህ ታደርጋቸዋለህ? አለው፡፡ ሰይጣንም፤ እነርሱ ራሳቸው በፈቃዳቸው ጎዳናዬን ሁሉ ይከተላሉና ፤ ፈቃዴንም ይፈጽማሉና ፤ የማሳስባቸውን ይሠራሉና ፤ ቃሌን አይተላለፉምና ፤ መዐዛዬንም ይወዳሉና ነው አለው፡፡ † ቅዱስ አባ ጳውሊ፤ ይህንን የሰይጣን ነገር በሰማ ጊዜ ታላቅ ሐዘን አዘነ፡፡ ያን ጊዜ ሰይጣንን እንዲህ አለው፡፡ አንተ የተረገምህ ክፉ ርኩስ እነሆ! ሌላ የክፋትህን ምክንያት እጠይቅሃለሁና እንዳትሸሽገኝ እምልሐለሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ ታላቅና ኃያል በሆነ ፤ ብርሃንን በፈጠረ በእርሱ ማልኩ፡፡ ከአንተ ምስጢሬን ልሸሽግ ብወድም አልቻልኩም፡፡ ምንም ፈጽሞ ልዋሽህ ስልጣን የለኝምና የምትጠይቀኝ ምንድን ነው? አለው፡፡ 👉 #ሰይጣን በውኃ ምንጮች ለምን እንደሚያድርና ነገሥታት፥ መኳንንትንና መሣፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፲፩.… ይቀጥላል ይጠብቁን/