es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 368 suscriptores, ocupando la posición 5 631 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 191 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 368 suscriptores.

Según los últimos datos del 20 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -39, y en las últimas 24 horas de -5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.39%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 441 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 226 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 21 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 368
Suscriptores
-524 horas
+297 días
-3930 días
Archivo de publicaciones
በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ #አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ #አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ሥርዐተ_ከተራ ፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡ ፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤ *ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡ *የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤ *መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡ *እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡ *ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡ *የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ *ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡ **ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡ ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡ የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡ #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤ #ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ #ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ #ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ #ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ #ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/ #ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡ ትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡ #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤ #ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ #ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ #ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ #ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ #ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/ #ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡

#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ? #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ) #ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡ #ከተራ_ለምን_ተባለ? በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ #አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ #አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ሥርዐተ_ከተራ ፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡ ፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤ *ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡ *የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤ *መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡ *እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡ *ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡ *የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡ *ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡ **ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡ ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡ የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለ#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ? #በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ) #ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡ #ከተራ_ለምን_ተባለ? በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@fino.tehiwot.      www.finotehiwotsundayschool.com #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ   #በዓለ_ጥምቀት  #Holy_Ephipany

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ   #በዓለ_ጥምቀት  #Holy_Ephipany

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ   #በዓለ_ጥምቀት  #Holy_Ephipany

3ኛ. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም 4ኛ. ጻድቃኔ ማርያም 5ኛ. ፈለገ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት 6ኛ. ወይራ ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና ዕጨጌ ዮሐንስ #፴፩ኛ) #ወረዳ_4_ #አየር_ጤና_ኪዳነ_ምሕረት_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ 1ኛ. አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 2ኛ. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም 3ኛ. ዓለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል #፴፪ኛ) #ወረዳ_1_ #በቴል_አጠገብ_(ኳስ ሜዳ) 1ኛ. ቤቴል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል #፴፫ኛ) #በላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ወረዳ_4 #ገብርኤል_ጠበል 1ኛ. ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ #፴፬ኛ) #ወረዳ_2_ #ሮል_ሳሙና_ፋብሪካ_ፊት_ለፊት 1ኛ. ረጲ ደብረ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ካራ ቆሬ ቅዱስ ሩፋኤል 3ኛ. ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል 4ኛ. ግራር ደ/አ/ቅድስት አርሴማ 5ኛ. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም ፠ ፠ ፠ #ነፋስ_ስልክ_ላፍቶ_ክፍለ_ከተማ_ (13ት ጥምቀተ ባሕር) #፴፭ኛ) #ደብረ_ኢያሪኮ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያን_አጠገብ 1ኛ. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ፉሪ ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ማርያም 3ኛ. ደብረ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም 4ኛ. ደብረ ወርቅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 5ኛ. ፈለገ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ 6ኛ. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል #፴፮ኛ) #ጎፋ_ሠፈር 1ኛ. ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ቤዛ ብዙኃን ኪዳነ ምሕረት 3ኛ. ቄራ መብራት ኀይል ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስና ዮሐንስ መጥምቅ #፴፯ኛ) #ጀሞ_መድኀኔ_ዓለም 1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል #፴፰ኛ) #ቻይና_ካምፕ 1ኛ. ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት ማርያም #፴፱ኛ) #ጀሞ_ቊጥር_3_አደባባይ 1ኛ. ጀሞ ቊጥር 3 ቅዱስ ገብርኤል #፵ኛ) #ቶታል_አደባባይ 1ኛ. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. መካኒሳ ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፵፩ኛ) #መካኒሳ_ኮንዶሚንየም 1ኛ. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል #፵፪ኛ) #ዮሴፍ_አካባቢ 1ኛ. ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 2ኛ. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ 3ኛ. ብሔረ ጽጌ ቅድስት ማርያም 4ኛ. አዲስ አምባ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 5ኛ. ሐመረ ወርቅ ቅድስት ማርያም #፵፫ኛ) #ብሥራተ_ወንጌል 1ኛ. ደብረ ቢ/ያ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፵፬ኛ) #ደብረ_ዕንቊ_ቅዱስ_ገብርኤል 1ኛ. ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል #፵፭ኛ) #ፉሪ_ኆኅተ_ብርሃን_ቅድስት_ማርያም 1ኛ. ፉሪ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም #፵፮ኛ) #ፉሪ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ዑር(ራ)ኤል 1ኛ. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል #፵፯ኛ) #ቡልቡላ_ ኤምባሲ_አጠገብ 1ኛ. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ለቡ በዓለ ወልድ ፠ ፠ ፠ #አቃቂ_ቃሊቲ_ክፍለ_ከተማ_ (9ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፵፰ኛ) #ወረዳ_1 #አቃቂ_በሰቃ_ወንዝ 1ኛ. ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ጃቲ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 4ኛ. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም 5ኛ. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔ ዓለም 6ኛ. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል 7ኛ. ፈንታ ደ/ጽ/ቅዱስ ሩፋኤልና ቅድስት አርሴማ 8ኛ. ቀርሣ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ልደታ ለማርያም #፵፱ኛ) #ወረዳ_5 #ከቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል #፶ኛ) #ወረዳ_4 #ሰርቲ_መድኀኔ_ዓለም_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ሰርቲ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም #፶፩ኛ) #ወረዳ_9 #ገብረ_መንፈስ ቅዱስ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ኮዬ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፶፪ኛ) #ቃሊቲ_አካባቢ 1ኛ. ሠፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል #፶፫ኛ) #ወረዳ_9 #ሥላሴ_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ቂሊንጦ ቅድስት ሥላሴ #፶፬ኛ) #ወረዳ_10 #ገላን_ጉራራ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ገላን ጉራራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል #፶፭ኛ) #ወረዳ_11 #ገላን_ኢዶሮ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. ገላን ኢዶሮ ቅዱስ ገብርኤል #፶፮ኛ) #መጠሊ_ገብርኤል_ቤተ_ክርስቲያኑ_አጠገብ 1ኛ. መጠሊ ደ/አ/ቅዱስ ገብርኤል ፠ ፠ ፠ #ቦሌ_ክፍለ_ከተማ_ (19ኝ ጥምቀተ ባሕር) #፶፯ኛ) #ጉምሩክ_ወረዳ_3 1ኛ. ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ #፶፰ኛ) #ወረዳ_23 #አየር_መንገድ 1ኛ. ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ክርስቶስ ሰምራ #፶፱ኛ) #ወረዳ_06 #መገናኛ 1ኛ. መገናኛ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፷ኛ) #ወረዳ_02 #ሩዋንዳ_አካባቢ 1ኛ. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 2ኛ. ቦሌ አየር ማረፊያ መንበረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ #፷፩ኛ) #ወረዳ_13 #አድዋ_ፓርክ 1ኛ. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም 2ኛ. ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ኤ(የ)ረር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑርኤል #፷፪ኛ) #ወረዳ_9 #ሰሚት_አደባባይ 1ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ቦሌ ሰሚት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3ኛ. ቦሌ ሰሚት ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 4ኛ. በሻሌ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም #፷፫ኛ) #ወረዳ_12 #ቡልቡላ 1ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም 2ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ወቅዱ አማኑኤል 3ኛ. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ቅድስት ማርያም #፷፬ኛ) #ወረዳ_9 #ጎሮ_ሰፈር_ባሕረ_ጥምቀት 1ኛ. ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብኤል 2ኛ. ኤረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ 3ኛ. ኤረር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል #፷፭ኛ) #ወረዳ_13 #አያት_አደባባይ_ #4_ኪሎ_ሰፈር 1ኛ. አያት መ/ሕ/መድኀኔ ዓለም #፷፮ኛ) #ወረዳ_13 #መሪ_አያት 1ኛ. መሪ ምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 2ኛ. አያት ጌቴ ሴማኒ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት 3ኛ. መሪ ቅዱስ ፋኑኤል 4ኛ. መሪ ቅድስት ሥላሴ #፷፯ኛ) #በሻሌ 1ኛ. ቦሌ በሻሌ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ 2ኛ. የቃጥላ ደብረ ፀሐይ ቅድሰት ማርያም #፷፰ኛ) #ወቄ_አካባቢ 1ኛ. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤል #፷፱ኛ) #አያት_ጨፌ 1ኛ. አያት ጨፌ ደብረ ኢያሪኮ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፸ኛ) #ወረዳ_11 #ለሚ_ኮንዶሚኒየም 1ኛ. ቦሌ ሰሚት ቅዱስ ሩፋኤልና ኤዎስጣቴዎስ #፸፩ኛ) #ወረዳ_11 #አራብሳ 1ኛ. አራብሳ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ዋሻው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፸፪ኛ) #ለሚ 1ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 2ኛ. ቦሌ ለሚ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ #፸፫ኛ) #አያት_ኮንዶሚኒየም 1ኛ. አያት ጨፌ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. አያት ፈለገ ሕይወት ቅዱስ ዮሐንስ #፸፬ኛ) #ቦሌ_ቡኒ 1ኛ. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ #፸፮ኛ) #ሪፈንቲ 1ኛ. ሪፈንቲ ቅዱስ ገብርኤል 2ኛ. ቦሌ ሰሚት መካነ ሕያዋን ዋሻው ቅዱስ ገብርኤል