es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 366 suscriptores, ocupando la posición 5 646 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 192 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 366 suscriptores.

Según los últimos datos del 18 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -95, y en las últimas 24 horas de 11, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.81%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.33% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 344 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 430 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 19 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 366
Suscriptores
+1124 horas
-67 días
-9530 días
Archivo de publicaciones
ዘጥቅምት ፳፬፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፩ኛ ዙር ዓመት፤  ፭ ሳምንት፥ ዘጥቅምት ፳፬) በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት፤ ወቅዱስ ፊልጶስ ሰማዕት፤ ወዕረፍቱ ለአቡነ ዲዮስቆሮስ ካልዕ፤ ወልደታ ለቅድስት ሐና እመ ሳሙኤል፤ ወዕረፍቱ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ እኁኁ ለቅዱስ ባስልዮስ። ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ✤ የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤ ✤ የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡ ✤በማኅሌት በምትቆሙ ጊዜ በጸሎታችሁ ደብራችንን ደብረ ሰላምን፤ ሰ/ት/ቤታችንን ፍኖተ ሕይወትን እና በውስጧ ያሉ አገልጋዮቿን አስቡልን፡፡✤ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 http://tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥቅምት_20_በዓለ_ልደቱ_ለኤልሳዕ_ነቢይ #በዓሉ_በእንጦጦ_ራጉኤል_ይከብራል። ኤልሳዕ የስሙ ትርጒም “እግዚአብሔር ደኅንነት ነው” ማለት ነው፡፡ነቢዩ ኤልሳዕ እጅግ ባለጠጋ የሆነ ሰው ነበር። ከዕለታት በአንደኛ ዕለት በ12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነቢዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው፤ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ይለዋል ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብኝ ይለዋል፤ እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት፤ ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። የኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ሆኖ አድሮበት ለረጅም ጊዜ እግዚአብሔርን አገለገለ፣ ብዙ ተአምራትንም አደረገ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ኢያሪኮ ከተማ በሚገባበት ጊዜ በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎች ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ እነርሱ እንደመጣ ባዩ ጊዜ “የዚች ከተማ ኑሮ መልካም ነው ውኃው ግን ክፉ ነው ምድሪቱም ፍሬዋን ትጨነግፋለች” አሉት፡፡ የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ይህን ልመና ለኤልሳዕ ያቀረቡት እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ነገርን ሁሉ መለወጥ እንደሚችል ይታመኑ ስለነበር ነው፡፡ ነቢዩ ኤልሳዕ የሰዎቹን ችግር ከተረዳ በኋላ የከተማውን ሰዎች አዲስ ማሰሮ እና ጨው እንዲያመጡለት አዘዘ፡፡ ሰዎቹም ኤልሳዕ እንዳዘዛቸው አደረጉ፡፡ አዲስ ማሰሮ በውስጡ ጨው አድርገው አመጡለት፤ ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ ውሃው ምንጭ ወደ አለበት ስፍራ መጥቶ ጨው ጣለበት እና “እግዚብሔር እንዲህ ይላል ይህን ውኃ ፈውሼዋለሁ ከዚህም በኋላ ሞትና ጭንገፉ አይሆንበትም” ብሎ ለከተማው ሰዎች ተናገረ፡፡ ኤልሳዕም እንደ ተናገረው ውኃው እስከ ዛሬ ድረስ ተፈውሶአል፡፡ የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ከዛ ጊዜ ጀምሮ ንጹሕ ውሃ መጠጣት ጀመሩ፡፡ የምድሪቱንም ፍሬ ተመገቡ፡፡ እግዚአብሔር በነቢዩ አልሳዕ ድንቅ ነገር ሰለአደረገላቸው ዘወትር ያመሰግኑ ነበር፡፡ እምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳዕ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች። ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። እምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳዕ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች፤ የዚህ ነቢይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገስት19 ላይ በስፋት ተጽፏል ጥቅምት 20 ልደቱ ሲሆን ሰኔ 20 ቀን ደግሞ በዓለ እረፍቱ ነው። /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ዘጥቅምት ፲፯፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፩ኛ ዙር ዓመት፤  ፬ ሳምንት፥ ዘጥቅምት ፲፯) በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት፤ ወቅዱስ ፊልጶስ ሰማዕት፤ ወዕረፍቱ ለአቡነ ዲዮስቆሮስ ካልዕ፤ ወልደታ ለቅድስት ሐና እመ ሳሙኤል፤ ወዕረፍቱ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ እኁኁ ለቅዱስ ባስልዮስ። ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤ ✤ የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤ ✤ የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡ ✤በማኅሌት በምትቆሙ ጊዜ በጸሎታችሁ ደብራችንን ደብረ ሰላምን፤ ሰ/ት/ቤታችንን ፍኖተ ሕይወትን እና በውስጧ ያሉ አገልጋዮቿን አስቡልን፡፡✤ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡ አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ፣ አባ ይምዓታ ከሀገረ ቁስያ፣ አባ ገሪማ ከሮም፣ ከአንፆኪያ አባ ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ ጉባ፣ ከእስያ አባ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ ጴንጠሌዎን፣ ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡     ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትን ማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸው ሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ አረጋዊ አሏቸው፡፡ አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደእርሱ በመንፈቀሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤ በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም ተሠውረዋል፡፡ ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡ **#ቅዱስ_ሙሴ_ብእሴ_እግዚአብሔር_በዓለ_ዕረፍታቸው_፡፡ ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው የእግዚአብሔር ሰው የተባለ የቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥቅምት_14፤ ** #ቅዱስ_ገብረክርሰቶስ_(#አብደል_መሲህ_) #በዓለ_እረፍቱ_፤ በጎ ሥራን ከሚሠሩ፤ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ  ከቊስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና ከመርኬዛ ልጅ የላቸውም ነበርና ኢየሩሳሌም ድረስ ሂደው በስዕለት ያገኙት ታላቅ አባት ነው፡፡ ስሙንም ቤተሰቡ አብደል መሲህ ብለው ሰየሙት፤ (አብደል ማለት አገልጋይ ማለት ሲሆን መሲህ ማለት ክርስቶስ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜውም ገብረ ክርስቶስ (የክርስቶስ ሥራ) ማለት ነው፡፡       እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ የቤተክርስቲያንንና ሥጋዊ ትምህርትን አስተማሩት፤ አድጎም በጎለመሰ ጊዜ የሮሜውን ንጉስ ልጅ አጭተው እንደሥርዓቱ አጋቡት። እሱ ግን በምድራዊ ሕይወት ከመደሰት ይልቅ በሰማይ ስለሚያገኘው ነገር አብዝቶ ይናፍቅ ነበርና በጋብቻ ከመኖር ይልቅ ምንኵስናን ይወድ ነበርና በሰርጉ ዕለትም እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ  ሙሽራው ገብረክርስቶስ ተነስቶ ወደ ሙሽራይቱ ሔዶ እጇንም ይዞ ከእርሷ ጋር ቃልኪዳን አደረገ፤ ከዚያም የሃይማኖት ጸሎትን አድርሶ ለእርሷም ምን አይነት ሕይወት መኖር እንደሚፈልግ አስረድቷት የተሞሸረበትን ልብስ ከላዩ አውልቆ የግምጃ ልብስን ለብሶ ለመሄድ ተነሳ፡፡ ሙሽራይቱም ‹‹እኔን ለማን ትተወኛለህ?›› ብላ አልቅሳ ጠየቀችው፡፡ እርሱም ‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ እተውሻለሁ፤ እኔም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ልከተለው እሄዳለሁ፤ የአባቴ መንግስት ኃላፊ ነውና፡፡ አንቺም መሀላሽን አስቢ፡፡›› አላት፡፡ ያን ጊዜ መሃላዋን አስባ ዝም አለች።       ከቤቱ ተነስቶ ወጣ፤ በመርከብ ከሚጓዙ መንገደኞች ጋር ያመት መንገድም ወደሚሆን አርመንያም ተጓዘ።      በነጋም ሰዓት አባትና እናቱ ሙሽራው ልጃቸውን ለማግኘት ወደ ሰርጉ አዳራሽ ገቡ፤ እንዳሰቡት ግን ሙሽራው ልጃቸውን አላገኙትም፤ ይልቁንም ሙሽሪቷን እያለቀሰች አገኟት እንጂ፡፡ እነሱም አጥብቀው በጠየቋት ሰዓት መሐላን አስምሏት በሌሊት እንደሄደ ነገረቻቸው፤ ታላቅ ለቅሶን አለቀሱ። ይፈልጉት ዘንድም ንጉሥ አባቱ አምስት መቶ አገልጋዮችን ላከ፡፡ ለድሆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት ያደርጉ ዘንድ ብዙ ገንዘብን ሰጣቸው ገብረክርስቶስ ግን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በተሰራች አርመንያ ሀገር በምትገኝ በአንዲት ቤተክርስቲያን ደጅ መኖር ጀምሮ ነበር፡፡       አባቱ የላካቸው ሁለቱ አገልጋዮችም ከዚያ ደርሰው ስለርሱ መርምረው ነበር፤ ወሬውን ግን ማግኘት ተሳናቸው፡፡ ለድሆችም ምጽዋትን ተቀብሏል ግን እንደማንኛውም የኔቢጤ ስለመሰላቸው ማወቅ ተስኗቸው ነበር፡፡ በዚህችም ቦታ ማንም እሱ የንጉሥ ልጅ፤ ቅዱስ መሆኑን ሳያውቅ 15 ዓመት ኖረ፡፡                                  እመቤታችን ለአንድ ቄስ ተገልጻ ገብረ ክርስቶስን ወደ ቤ/ን ያስገባው ዘንድ አዘዘች፤ ገብረክ ርስቶስም ይህን ባወቀ ጊዜ በሌሊት ተነስቶ በእመቤታችን ስዕል ፊት ‹‹እመቤቴ ሆይ የተሰወረ ሥራዬን አንቺ ለምን ገለጥሽ አሁንም ወደ ሚሻለኝ ምሪኝ›› ብሎ ስዕሏን ተሳልሞ በሌሊት ወጥቶ ወደ ባህሩ ወደብ ደረሰ፡፡     ወደሌላ ሃገርም ሊሄድ ወዶ በመርከብ ተሳፈረ ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ከአባቱ አገር ደረሰ እሱም እናትና አባቴ ለኔ የፈለጉትን እየሰጡኝ ለነሱ ምጽዋት ይሆንላቸው ዘንድ በደጃቸው ልኑር ብሎ በፈቃዱ ወደ እነርሱ ሄደ፡፡ የእነርሱን መዳን ሽቷልና ፊቱ በጣም ተለውጧልና ከቤተሰቦቹም ይሁን ከገረዶቻቸው መሃል ማንም ያወቀው አልነበረም ከውሾቹ በቀር፡፡ ለአባቱም እኔ መጻተኛ ነኝና በቤተ መንገሥትህ ደጅ ፊት ለፊት እንዳትረሳኝ ጎጆ ሥራልኝና ልኑር አለው፤ አባቱም የልጁን ኹኔታ አስቦ እኔም ልጄ እንዲሁ አይደል ብሎ ፈቀደለትና መኖር ጀመረ፡፡ የቤተ መንግሥቱ ባለሟሎችና እንዲንከባከቡት የታዘዙት ሠራተኞች ግን ሲገቡና ሲወጡ ሽታው እንዳያስጨንቀን ይህን ምስኪን አስውግዱልን እያሉ ወጭትና ድስትም እያጠቡ በላዩ ይደፉበት ነበር፡፡ ውሾችም እንዲናከሱበትና እንዲበሉት የሥጋ ትርፍራፊ ይጥሉበት ነበር፡፡ ውሾች ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር፡፡ ቅዱስ አባ ገብረ ክርስቶስም ጊዜ እየረዘመ በሄደ ጊዜ የባሮቹ በደል እየበዛ ሲመጣ (መቋቋም ስላቃተው ሳይሆን ለእነሱ በደል እንዳይሆንባቸው ሲል) ወደ እግዚአብሔር ይወስደው ዘንድ ለመነ፡፡ ከዚያም ታሪኩን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻው ጽፎ በእጁ ይዟት አረፈ፤ የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ ፈጣሪም እንደፈለገ ነፍሱን ከሥጋው ለየለት፡፡ ለሱም ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ የዕረፍት ቀኑም እሑድ ነበርና ሕዝቡ ሁሉና ካህናቱ ከሊቀጳጳሳቱ ጋር በቅዳሴ ጊዜ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሳሉ ‹የእግዚአብሔርን ሰው በንጉሡ በቴዎዶስዮስ ቤት ፈልጉት› የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ በዚያን ጊዜ ሂደው በአረፈበት ቦታ አገኙት፡፡ በእጁም ውስጥ የተጨበጠ ክርታስን አዩ፡፡ ሊወስዷትም ሽተው መውሰድ ተሳናቸው በአንድነትም በጸለዩ ጊዜ እጁ ተፈትታ ወስደው አነበቧት፡፡ አባትና እናቱም ልጃቸው እንደሆነ አወቁ ታላቅ ጩኸትም ሆነ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ አክብረውም በጥምቀት 14 በእረፍቱ ቀን ቀበሩት መቃብሩም በሽተኞችን ሁሉ በመፈወስ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተዓምራቶችን የሚያደርግ ሆነ ከጻድቁ ረድኤት በረከት ያሳትፈን፡፡ ፠*፠ #አቡነ_አረጋዊ ፠*፠ (#ዘሚካኤል)#ወቅዱስ_ሙሴ_ብእሴ_እግዚአብሔር #አቡነ_አረጋዊ (#ዘሚካኤል) ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው ይስሐቅና ከእናቸው እድና  የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው፤ ወንድሞቹም ቴዎድሮስ እና ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡ የቀድሞው ስማቸው ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡ ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡ እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡ አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ  በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት

#ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ ** በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊልጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን (በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰማያዊውም
+2
#ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ ** በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊልጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን (በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰማያዊውም ሆነ ምድራዊውን ውለታ የዋለልን) የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ #በሀገራችን__ብቸኛ_በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. #ደብረ_ምጥማቅ-ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ " እነሆ በውሀ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድነው? " የሐዋርያት ሥራ ፰÷፴፮ **በኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውና በአዲስ አበባ የሚገኘው ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ.ክ የተመሠረተው በ3ኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ የቅዱስ ፊልጶስ ክብረ በዓል በዓመት 2ት ጊዜ ነው፤ #ጥቅምት 14 በዓለ ዕረፍቱ #የካቲት 20 ቅዳሴ ቤቱ ነው ‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።"ዕብ. 13፥7 ፠፠፠ ‹‹ደብሩሰ ለቅዱስ ፊልጶስ ትመስል ደብረ ሲና፤ ወሀደረ ላዕሌሃ እግዚአብሔር ሐፁር የዐውዳ ወጽጌረዳ በትምዕርተ መስቀል፡፡›› #አድራሻ_- ኮልፌ አጠና ተራ ወደ፡ሎሚ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ኢንዱስትሪ መንደር ሳይደርሱ ፠1. ከመርካቶ በባስ ቁጥር 69 ጠሮ በሚወስደው መንገድ፣21 ልኳንዳ ወርደው ወደ ቀድሞ 04 ቀበሌ ፠2. ከአየር ጤና እና ዙሪያው በባስ ቁጥር 87 አጠና ተራ ወርደው የቀለበት መንገድ የእግረኛ መሻገሪያ ተሻግረው ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል ፠3. ከቡራዩ አስኮ አካባቢ ለምትመጡ በባስ ቁጥር 28 አጠና ተራ ወርደው በቀኝ በኩል ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል።

#የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤
+7
#የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤ ይኸውም የበሶ እምነት ለብዙ ችግሮች ፈውስ ነው፡፡ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያትም በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናንም እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ *** +++ #የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል ዐበይቶቹ፤ ፠ በደብረ ዳሞ፣ ፠ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም፣ (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት ይገኛል) (ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ክብረ በዓል በደብራችን ሲከበር 100 ዓመታት ሞልቶታል፤ እንኳን ክብረ በዓል የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ማኅበር እንኳን 100 አካባቢ አስቈጥሯል፡፡) ፠ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ (አለርት ሆስፒታል አጠገብ፤ ወደ አለም ባንክ መስመር) ፠ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በጎንደር አቡነ አረጋዊ ቤ.ክ. (ብሉኮ አካባቢ)

#ዳሕምሞ_ #ደብረ_ዳሞ_ መላእክትም ለአረጋዊ እንደባልንጀራ አንደ ጓደኛ ሆኑት፤ እሳቸውን ለመጐብኘትና በረከት ለማግኘት አባቶች ብቻ ሳይሆኑ ንጉሡ አጼ ገብረመስቀልም ወደእሳቸው ይመጣ ነበር፡፡ እሱም እሰከዛሬ ምስክር ሁኖ የሚገኘውንና በእመቤታችን ስም የተሰየመውን ድንቅ ገዳም ሲያንጽ ለእንሳሳቱ መመላለሻ እንዲሆን ተራራን አሠራ፤ ሕንጻው ቅዱስ ያሬድ በተገኘበት ተመረቀች፤ ኋላ ግን ንጉሡ ከአረጋዊ ተባርኮ ሲመለስ ‹‹ተራራውን ላፍርሰው፤ ወይስ ልተወው?›› አለ፤  አቡነ አረጋዊም በግዕዙ ‹‹#ዳሕምሞ_›› አሉት፡፡  በአማርኛ ቋንቋ ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አካባቢው ዳሞ ገዳሙ ደግሞ ደብረዳሞ ተባለ፡፡ አቡነ አረጋዊም ንጉሡን ‹‹ስለዘንዶው ጅራት ፈንታ ሰዎች ይወጡበት ዘንድ ገመድ አብጅ፡፡ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆንና ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ፡፡›› አሉት፤ ለመወጣጫ ይሆን ዘንድ ገመድ ተሰራለት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ገመዱ የታሠረበት ግንድ እስካሁን ከ1500 ዓመታት በላይ አለ፤ ኋላ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለ12 ዓመታት በደብረ ዳሞ ቆይተው በዚሁ ገመድ ሲወርዱ ነው ሰይጣን ቀንቶ ገመዱን ቢበጥስባቸው እግዚአብሔር አምላክ ክንፍ የሰጣቸው፡፡ ደብረዳሞ ዙርያው ገደል ሆኖ የጠረጴዛ ቅርጽ ያለው ያለው አምባ ሲሆን 500*1000 ሜትር የሚሆን ስፋት አለው፡፡ ከባህር ወለልም በላይ 2216ሜ. ከፍ ይላል፡፡ ወደ ገዳሙ መውጣት አና መውረድ የሚቻለው 16ሜ. በሚረዝመው በአምሳለ ዘንዶ በተሰራው ገመድ ብቻ ነው፡፡    ንጉሡም ከተራራው እንደወረደ እንደታዘዘው አፈረሰ፡፡ አሁን የምናየው ዓይነት ገመድንም አዘጋጅቷል፤ የገመዱም ስመ ‹‹ዘንዶ›› ይባላል፡፡ በዚህ ገዳም ሴቶች በአፀደ ሥጋ እያሉ አይገቡም፤ ካረፉ በኋላ ግን እንደ አባ ጳኩሚስ ገዳምና ሥርዓት ከተከዜ ማዶ ከሚኖሩ የሴት መነኮሳት መካከል አንዲቱ የሞተች እንደሆነ ወደ ወንድሞች መነኰሳት አምጥተው በነሱ ዘንድ በሚገኘው የመቃብር ቦታ ይቀብሯቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የአቡነ አረጋዊ እናት የነበረችው ልጂ በሕፃንነቱ ሳለ መመንኰሱን አውቃ ከልጇ ሕይወቱን ተምራ ገና ከመጀመሪያ ወደ አባ ጳኵሚስ ገዳም ሄዳ መንኵሳ ነበርና በቅድስና በትሕትና ደናግሉ በፍቅር ስታስተዳድር ኖራ መንፈሳዊ ግዳጇን በጐ አገልግሎቷን ፈጽማ ጥር 4 ቀን ስታርፍ ለመቀበሪያዋ ይሆን ዘንድ አባታችን አቡነ አረጋዊ ባሰራላት አዲስ መቃብር ተቀብራለች፡፡