es
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Ir al canal en Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የጥበብ ማዕድ

El canal የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 880 suscriptores, ocupando la posición 5 407 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 116 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 880 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 628, y en las últimas 24 horas de 31, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 2.61%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.09% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 415 visualizaciones. En el primer día suele acumular 332 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 880
Suscriptores
+3124 horas
+1507 días
+62830 días
Archivo de publicaciones
(በዉቀቱ ስዩም) ተገልጋዩን በተመለከተ የምናገረው በጣም አጭር ነው፤ ሲጀመር ጉንዳንን የምናውቀው በታታሪነቱ እንጂ በድህነቱ አይደለም፤ ጉንዳን የቺስታ ምልክት ሆኖ አያውቀም፤ ጠቢቡ ሰለሞንም “አንተ
(በዉቀቱ ስዩም) ተገልጋዩን በተመለከተ የምናገረው በጣም አጭር ነው፤ ሲጀመር ጉንዳንን የምናውቀው በታታሪነቱ እንጂ በድህነቱ አይደለም፤ ጉንዳን የቺስታ ምልክት ሆኖ አያውቀም፤ ጠቢቡ ሰለሞንም “አንተ ታካች ወደ ገብረጉንዳን ሂድ “ ሲል ባተሌነቱን ፥አርአያ አድርግ ማለቱ መሰለኝ፤ “ሁላችንም ራቁታችንን ነው የመጣነው” እምትለዋ የቸከች አባባል ትምጣብኝ፤ እውነት ነው፤ ሱፍ ገበርዲን ለብሶ የተወለደ የለም፤ ይሄ ማለት ፥ በዚች ምድር ለሁሉም ሰው ኑሮውን የሚያሸንፍበት አንድ አይነት መወዳደርያ ሜዳ አለው ማለት አይደለም፤ ራቁታችንን መምጣታችን አይደለም ችግሩ፤ የሚቀበሉን ወላጆች ርቃናችንን የመሸፈን አቅም አላቸው ወይ ? በእራፊ ጨርቅ የሚጠቀለል አለ፤ በሀር ጨርቅ የሚጠቀለል አለ፤ የአላሙዲ ልጅ እና ጎዳና ላይ የሚወለደው ያንዲት የኔ ብጤ ልጅ እኩል ናቸው፤? የመጀመርያው ሁለተኛውን ቀድሞት ቢከብር ፥ ሁለተኛው "ባመሉ እና ባመዱ"ምክንያት ደኸየ ሊባል ነው? በዚህ አገር ላይ ስንፍና እና ስለታታሪነት ማውራት ያለባቸው በትክክል
በልፋታቸው የሚኖሩ ሰዎች ናቸው ፤ ገበሬው፥ ጠረፍ ጠባቂው፥ ሀኪሙ መምህሩ ነጋዴው ፤ ሾፌሩ፤ ግንበኛው ፤ አናጢው ወዘተረፈ
፥ በአንጻሩ
“ እግዚአብሄር ነገረኝ “ በማለት እየተበረነነ በአማኝ ህዝብ ድጋፍ ደልቶት የሚኖር ሰው ፥ ስለ ስለትጋትና ስለስንፍና የማውራት ሞራል የለውም፤
የሀይማኖት መሪዎች ሰባኪዎች ህብረተሰቡ ብዙ መስዋእትነት እንድትከፍሉለት አይጠብቃችሁም! ሀብታሞች ለእናንተ ከሚሰጡት መባና ስጦታ ቆንጥረው በብዙ ምክንያት ለተቸገረ እንዲረዱ ካሳሳባችሁ ትልቅ ውለታ ነው፤

ሹመቴ... ሺ  ሞቴ .... እሱም እንደ ልቡ ... እኔም እንዳሞቴ ባይልም ዳሞቴ ... እንደክራሞቴ                  ቢፈቅደኝ ... ሊያሞኘኝ ....                 ቢያቅደኝ .... ቢመኘኝ ..... እኔ ምን ተዳዬ ...ሁሉም ያሻውን ቢሆን ...     ስንቄን እና ትጥቄን ሳይሰጠኝ ... ላይሸኘኝ ዓለሜን ብየ ካደርኩ .... ምን አለ የሚሳነኝ አሀዱ ለፍቅር  ... ለሰላም ሽልማት ምን አለ ልዕልና ..  ከጣር ከህማማት           እድሜ እየነገረ ...  ልብ እየሰገረ ....          እጅ እየጋገረ ... ቀን እየማገረ .... ቢሾሙም ..... ጥንስስ ነው ሲመጡም .... እንጥስ ነው ቢሄዱም ... ብጥስ ነው ቢኖሩም ..... ቅንጥስ ነው        አሁ .... ተነፈስኩ       ፈሰስኩ ....       እንደደም ባልረጋም ......       ካልተሾምኩ አልሰጋም 📒 የባለ ቅኔ ምህላ

📚ርዕስ:- ጥበብ ቅፅ 2 ስብስብ ስራዎች (ጥበብ : እየሱስ -የሰው ልጅ ጲላጦስ) 📝ደራሲ:- ከጲላጦስ(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ) 📅ዓ ም:- 2012 📖የገፅ ብዛት:- 581 ═════════════════

📚ርዕስ:- ጥበብ ከጲላጦስ 📝ድርሰት:- ሃይለጊዮርጊስ ማሞ 📜ይዘት:- ፍልስፍና 📆የመጀመሪያ ዕትም:- 1997 📖የገፅ ብዛት:- 208

በህይወት ከአጣናቸው አርቲስቶች መካከል ሁሌም ትዝ የሚሏቹና የሚናፍቋቹ በቀዳሚነት እነማን ናቸው? ለትውስታ………

የኃይለየሱስ ማሞን ጥበብ ከጲላጦስ የሚለውን መፅሐፍ እየኮመኮምኩ ፅሁፎቹ ጣፍጠው ምላሴን ከረሜላ እንደበላ ሰው "ጣ"! እያልኩ  እያነበብኩ ነው ። በጣም! ከጣፈጠኝና ለብቻዬ ከማጣጥም ለናንተም ይቺን ቅንጫቢ ላስኮምኩማቹ ወደድኩ :- ➥ አንድ ቀን የእስራኤል ልጆች ወደ ሙሴ ተሰብስበው መጥተው እግዚአብሔርን እራት ሊጋብዙት እንደሚፈልጉና ይኼንኑም እንዲነግርላቸው ሙሴን ጠየቁት ። በዚህ የድፍረት ጥያቄ የሙሴ ቁጣ ነደደ ። "እግዚአብሔር የሰውን ምግብ አይመገብም ፤ ወደ እናንተ የራት ግብዣም አይመጣም " አላቸው ። የእስራኤል ልጆችም እያዘኑ ተመለሱ ። በነጋታው ምሽት ላይ ሙሴም እንደለመደው ከእግዚአብሔር ጋር ሊነጋገር ወደ ተራራ ወጣ ። ወደ ተራራው ጫፍ ላይ ሲደርስ እግዚአብሔር ቁሟል ። እግዚአብሔርም " ባሪያዎቼ የእራት ግብዣ አድርገውልኝ ለምንድነው አሳፍረህ የመለስክብኝ ..." በማለት በሀዘኔታ ጠየቀው ። ሙሴም " ጌታ ሆይ የሰው ምግብ አትበላም ብዬ ነበር ። እንዲህ አይነቱን የሞኝ ግብዣም አትቀበልም የሚል እምነት አድሮብኝ ነው ..."  አለ ። እግዚአብሔርም አዘዘው "  ሂድና ለህዝቤ ንገረው ። ነገ ማታ ለእራት እመጣለሁ ፤ ግብዣውንም ተቀብያለሁ ..."። ሙሴም በለሊት ወደ ህዝቡ ተመልሶ እግዚአብሔር የእራት ግብዣቸውን እንደተቀበለ አበሰራቸው ። "  ማታ እራት ከእናንተ ጋር ነኝ ተዘጋጁ ብሏል "  አላቸው ። ህዝቡም ድግሱን ማዘጋጀት ጀመሩ ። በእስራኤል ምድር ታላቅ የተባለው ግብዣም ተዘጋጅቶ መሰናዶው ወደ መጠናቀቁ በተቃረበበት ሰዓት አንድ በረሃብ የከሳና የጠወለገ ሽማግሌ ድንገት ወደ ድንኳኑ ደጃፍ ተጠግቶ " እባካቹ ተርቤአለሁ ... ከድግሱ የምበላውን ትንሽ ስጡኝ " በማለት ልመና አቀረበ ። ህዝቡ ግን እያዳፉና እየጮሁ አስወጡት ... " እኛ የደገስነው ከእግዚአብሔር ጋር ለመብላት ነው ..."  በማለት አባረሩት ። የዚያን ቀን ማታ እግዚአብሔር ሳይመጣ ቀረ ። ሙሴም እጅግ አፈረ ፤ ብዙዎቹም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሬ መጣሁ የሚለን ውሸት በማለት ጠረጠሩት ። በነጋታው ምሽት ላይ ሙሴ በሲናይ ተራራ ወጥቶ እግዚአብሔርን መጠበቅ ጀመረ ። እግዚአብሔርም በሰዓቱ መጣ ። ሙሴም በሐዘን " ጌታ ሆይ የራት ግብዣቸውን እንደተቀበልክ ለህዝብህ ነግሬ ነበረ አንተ ግን ቀርተኽ አሳፈርኸኝ ..." አለ ። እግዚአብሔርም " ሙሴ በራት ግብዣችሁ ላይ ቀድሜ ነበር የተገኘሁት ነገር ግን ገፍትራቹ አባረራችሁኝ " አለ ። ሙሴም :- " እኛ ያባረርነው ደሃ ሽማግሌ ነው ፤ ሌላ ያባረርነው ሰው የለም " አለው ። እግዚአብሔርም ጠየቀው "  ያን ደሃ ሽማግሌስ ማን ፈጠረው ?" ሙሴም " አንተ ነህ ጌታ ሆይ !" በማለት መለሰ። ይኸን ግዜ እግዚአብሔር :- " ታዲያ በፈጠርኩት ውስጥ መኖሬን ትጠራጠራለህ ?" አለው ። ሙሴም አላስተባበለም ። ከታናናሾቹ ለአንዱ ያደረጋችሁት ለእኔ እንዳደረጋችሁት እቆጥረዋለሁ እንደማለት ነው ። ✍Henok

አለማደጋችን አይገርመኝም ማደግ የስራና የጥረት እንዲሁም የእድል ውጤት ነው! ሚያስገርመኝ ያደገና በማደግ ላይ ያለ ሰው ላይ ያለን አሉታዊ ምቀኝነት ነው!!!

. ኣለማመን መቼም የተሻለ ሚሆንበት ኣግባብ የለም። ግን ኣምነን ማንኖረውና ልንኖርበት የማንጥረው ማመንም ካለመመን ሊሻል ኣይችልም።ኣፍ ላይ ያለ በሄድንበት ጥብቅና የምንቆምለት የልብን መታደስ ያላመጣ ትልቅ በማመን ስም የተሸፈነ ኣለማመን......ኣለ   .

ረጅም የነዳጅ ሰልፍን ከኋላ ሶስት ቀን ሙሉ ተሰልፎ አንድ ቦቲ ቢመጣ እንደማያዳርሳቸው እያወቀ አማራጭ ባይኖረውም በትዕግስት የሚጠብቅን ሹፌር ማክበር አስፈላጊ ነው።

በጋራ በምትጠቀመው መንገድ አደጋ ካንተ ብቻ አይመጣም!

ዛሬ ደግሞ እስቲ ስለ Hercules  እናወራለን :- Hercules / Heracles  በግሪክ እና በሮማ history ላይ  የታወቀ ታላቅና ኃይለኛ ጀግና ነው ። Hercules የአማልክት ንጉስ ዙስ ልጅ ነበረ ። so ከሰዎች ሁሉ በላይ ኃይል ነበረው ። እሱ አስደናቂ ጦርነቶችንና ጀብዶችን ይሰራ ነበረ በወሬና በቃል ደረጃ ትዕዛዝ መስጠት ሳይሆን በተግባር ፊት ይመራ ነበር ። ሄርክለስ እጅግ ከባድ የሚባሉትን ነገሮች እንዲሰራ ይጠየቅ ነበረ ለምሳሌ :- አንበሳ መግደል ፣ አስፈሪ የሚባሉትን እንስሳቶችን በነፍስ መቆጣጠር ፣ ከባባድ ተግባሮችን መፈፀም ፣ ሃይድራ መግደል ይሄ ማለት ብዙ ራስ ያሉትን እባቦች አንድባንድ መግደል ፣ የወርቅ እግር ያለው አጋዘን መያዝ ፣ የኤሪማንቶስን አሳማ መያዝ .... ብዙ ጀብዶችን የሰራ ታላቅ ሰው ነው ። ሄርክለስ አባቱ አምላክ ( ዙስ ) እናቱ ደግሞ የሰው ልጅ ናት ስለዚህ ሄርክለስ ግማሽ አምላክ / ግማሽ ሰው ነበር (demigod ) ይባላል ። ስለ ሄርክለስ በትንሹ ይህን ብያለሁ በቀጣይ ስለ አባቱ ዙስ እነግራችኋለሁ     ✍ Henok

ወላይታ ሶዶ — ሚያዝያ 23. 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር በመርካቶ ክፍለ ከተማ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የቦሳ ቶጎጎ ድልድይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በ
ወላይታ ሶዶ — ሚያዝያ 23. 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር በመርካቶ ክፍለ ከተማ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የቦሳ ቶጎጎ ድልድይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በትላንትናው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ሚሊዮን ምነው ለሌላው ረክሰሽ ለኛ ተወደድሽ!😒

መፍትሔ አለን አልቻሉም በቃ ብለው እንዲዳከሙ ነው እንጂ።

ንቀት ( scorn ) ንቀት ማለት ሌላው ሰው እንደ አንተ እኩል መብት ወይም እሴት አለው የሚባለውን ነገር መከላከል ነው ። ነገር ግን ንቀት ክፉ ነገር ነው ። በውስጠኛው አስተሳሰብ ታስቦ ወደ ውጨኛው ወይም የባህሪ መቀያየርን የሚያመጣ ነገር ነው ። የውስጥ ባህሪ ያልኩት ሰው ሲናቅ ብዙ ነገሮችን ያስባል ። ለምሳሌ :- "  እኔ ከእርሱ እበልጣለሁ " ፣  "  ይሄ ለእርሱ አይገባውም " ፣ "  ለምን እሱን ብቻ ይወዱታል " ፣ "  ማን ስለሆነ " ፣ "  እሱ ትንሽና ደካማ ነው " "  ይሄ የሚያሳየው ትክክለኛ ክብርን አሳልፎ የራስን ክብርና ዝና ማስጨመር ነው ። የውጨኛው ደግሞ :-  በአሽሙር መሳደብ ፣  መቀለድ ወይም ማሾፍ ( mocking ) ፣ አስቀያሚ የሆነ facial expression ማሳየት ፣  እየተናገረ በመሃል ማቋረጥ .... ።  እነዚህ በውጨኛው ባህሪ የሚታይ የንቀት ምልክት ነው ። Freiderich Neitzsche  ንቀትን  " ደካማ ስሜት "  ይለዋል ይህን ለማለት የፈለገው ሰው ራሱን ሲክብና ሲያተልቅ ሌላን ሰው ያሳንሳል ። አንዳንድ ሰው የራሱን ድክመት የሚሸፍን ሌላውን በመናቅ ወይም በማሳነስ የራሱን ዋጋ ይጨምራል so ይሄ ደሞ የሚያሳየው የስሜትን ደካማነት ነው ። Arthur Schopenhauer ደግሞ ንቀትን እንደ እውነተኛ ጥላቻ ይመለከታል ። ንቀት በ Arthur እይታ ሰው ሁኖ ሰዎችን የሚንቅ ሰው ክፉም አይደለም መጥፎም አይደለም ግን ትክክለኛ ጠላት ነው ይላል ።    ✍ Henok

በቀላል አገኙት በቀላል ጠፋባቸው።

Pandora ፓንዶራ የሚለው ቃል የመጣው ከግሪክ ታሪክ Mythology የመጣ ነው ።  ፓንዶራ የሚለው ቃል በብዙ ሁኔታ የሚገለፅ ቢሆንም ቃሉ ከምን እንደመጣ እነግራችኋለሁ ። Pandora መጀመሪያ ሴት ነበረች ማለትም ተራ የሰው ልጅ ነበረች ተብሎ ይታሰብ ነበረ ። አማልክቶች ሁሎችም ስጦታ ስለሰጧት"  Pandora " ተብላ ተጠራች ። pandora  ማለት ( ሁሉን ስጦታ ያገኘች ማለት ነው ።)  እሷን አንድ ሳጥን እንዳትከፍት ተነግሯት ነበረ ። እሷ ግን" እምቢ "  ብላ ከፈተችው ። በዚያ ሳጥን ውስጥ ያሉ ነገሮች ክፉ ነበሩ። ( ህመም ፣ መከራ ፣ ሞት ፣ ጨለማ ... ) በውስጡ ይዞ ነበረ ግና እሷ ስትከፍተው እነዚያ ክፉ ነገሮች ወደ ዓለም መጡ ። እነዚህ ሁሉ ከወጡ በኋላ ሳጥኑ ውስጥ የቀረው #ተስፋ ብቻ ነበር ። ከዚያ ግዜ በኋላ ያንን ሳጥን " Pandora's box "  በማለት መጠራት ተጀመረ ። ምን አልባትአሁንም ሰዎች ስለ  pandora box ሲያወሩ ግራ እንዳይገባቹ ቃሉን ዛሬም ድረስ ሰው ይጠቀማል ። pandora box  ዛሬም የሚጠቅመንና የሚያስተምረን ነገር :- ለመክፈት ቀላል የሆነ ግና ለመመለስ የማይቻል ነገር ፣ ለመግባት ቀላል የሆነ ግና ለመውጣት ከባድ የሆነ ፣ ነገሩን ከስሩ ሳናረጋግጥ የምንወስነው ውሳኔ ህይወታችንን ፍዳ ሲያበላው ፣  መጀመሪያ ላይ ለማድረግ ቀላል ሁኖ በመጨረሻ መመለስ ማይቻል ከሆነ Pandora's box እንላለን ።       ✍ Henok

ጥሩ ነገር ራሱ እንዲበረክት አያያዝ ይፈልጋል!

ወድቆ የተነሳ          እግዜርን ሲያነሳ                        ህመሙን ረሳ!

የመንጋ እሳቤን ለመቅረፍ የምመክራቹ ነገር ቢኖር Dark Psychology መፅሐፍ አነፍንፎ ማንበብ ነው። እናም እነዚህን avoid  ለማድረግ የሚረዱትን ግንዛቤ ( awarness)  አሳያችኋለሁ :-  1 ( School proof ) የሚባለው  :- ጓደኛ  ፣ ወንድም ፣  ወይም የሆነ ታዋቂ ሰው በመመልከት እነሱ በሚወስኑት ዉሳኔ ጥገኛ ሁኖ የሚኖር ማለት ነው ። በአጭሩ ሌሎችን በመመልከት የሚወሰን ውሳኔ ይህ ደግሞ በራስ መተማመንን እንደ ብል ምጥጥ አድርጎ ይበላል ። 2 ( Social media ) አንድ ሰው በማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚጠቅምም ይሁን የማይጠቅም ነገር post  አድርጎ ብዙ view  ካገኘ  "  ብዙ ሰው ስላየው ምርጥ ነው "  ብለን እንወስናለን ። ይህ ጥሩ አይደለም አሪፍ ነገር post  አረገ ወይም የሚያስጠላ ነገር post  አረገ ለማለት አእምሯችን እንዲያስብ postun በራሳችን እንገምግመው ። ኣእምሯችን ይንቀሳቀስ !። 3 ( investment )  አንድን ነገር ስንገዛ ሌላ ሰው የገዛውን ወይም በሌላ ሰው ላይ የሚያምርበትን ነገር አንግዛ ። በራሳችን እንወስን ። ምን ዓይነት ልብስ እንደሚሆነን አውቀን decide እናድርግ ። ጠቅለል ሳረገው የመንጋ እሳቤ ሁሉ በሮጠበት አትሩጥ ከፊት ለፊት ገደል ሊኖር ስለሚችል ቆም ብለህ አስብ ። በመንጋ እሳቤ ምትመራ ከሆነ የህይወትህን መሪ ሌላ ሰው ነው ሚቆጣጠረው ። Gustave Le Bon  ያለውን አስታውስ እሱ እንዲ ይላል "  ሰው በቡድን ውስጥ ሲገባ የራሱን አእምሮ ያጣል " ።     ✍ Henok

ትልቁ ቁም ነገር መናገር አይደለም አድማጭ ማግኘቱ ነው። ለመናገርማ እብድ'ም ካለ አድማጩ ብዙ ተናጋሪ ነው!!!