የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Ir al canal en Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Mostrar más2 634
Suscriptores
+124 horas
+227 días
+5430 días
Archivo de publicaciones
‛‛በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል’’
ሰላም ለሚካኤል መሓሪ ውእቱ ወተአዛዚ ለሰብእ በዲበ ሠናይቱ፤ ለቀርነ ዝንቱ መልአክ በድምፀ ንፍኀቱ ፣ በከመ ኮነ ቀዳሚ ውስተ ሰማያት ዕርገቱ ፣ ለእግዚአብሔር ይከውን ዳግመ ምጽአቱ።
‛‛በቸርነቱ ላይ ለሰው ታዛዥ ለሆነውና በይቅር ባይነቱ ለታወቀው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሰላም እላለሁ። አስቀድሞ የእግዚአብሔር ወደሰማይ ማረግ በዚህ መልአክ የመለከት ድምጽ መነፋት እንደታወቀ ዳግመኛም በሚመጣበት ጊዜ እንዲሁ ይሆናል ’’
እንኳን ለዓመታዊው የሰኔ ቅዱስ ሚካኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓሉ በደብራችን ታቦተ ሕጉ በመንበረ ክብሩ ወጥቶ በታላቅ ድምቀት የሚከበር በመሆኑ ሁላችሁም በጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ተገኝታችሁ በረከት እንድትካፈሉ ተጠርታችኋል።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የክረምት ኮርስ ለሕጻናት እና ለማዕከላውያን
እድሜያቸው ከ5 - 13 የሆኑ ሕጻናትን እና
እድሜያቸው ከ 13- 18 የሆኑ ማዕከላውያንን በመጪው የክረምት ወራት የቤተክርስቲያንን ትምህርት እንዲማሩ በማስመዝገብ ወላጆች ትውልድን የማነጽ ኃላፊነታችሁን ተወጡ።
ቦታው:- ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ትምህርቱ ሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ይጀመራል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የተከበራችሁ የሰኔ ቅዱስ ሚካኤል እና የበዓለ ጰራቅሊጦስ ዘማርያን አባላት በሙሉ በበዓሉ እለት ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች
1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)
2.ቅንድብመቀንደብ
3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ
4.አላስፈላጊ ሜካፕ .....
5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ተግባራትን አትጠቀሙ።
መልካም በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ጥሪ ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አይሲቲ (ሚዲያ ክፍል) ለ15 አባላት ከታች በተጠቀሱት ሙያዎች ስልጠና መስጠት ይፈልጋል።
የመጀመሪያ ዙር 👉በግራፊክስ
በመቀጠል 👉ኤዲቲንግ
እንዲሁም 👉ፎቶና ቪዲዮ ቀረጻ ሲሆኑ
ስልጠናውን ለመውሰድ ከሰልጣኞች የሚጠበቁ መስፈርቶች
> የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነ።
> ከስልጠናው በኋላ በተፈለገው የሰንበት ት/ት ቤታችን ሚዲያ ክፍል በሚፈልግበት ስራ ላይ በንቃት ማገልገል የሚችል( ለማገልገል ፍላጎት ያለው/ያላት)።
> ስልጠናው ጊዜ ስለሚፈልግ ጊዜ ያለው ከመ/ራኑ ጋር በመወያየት አመቺ ጊዜ ይወሰናል።
> የምዝገባ ጊዜ ከ ሰኔ15 እስከ ሰኔ 20 ቀን 2016 ዓ·ም።
> መመዝገቢያ @AfeworkBe12
ቴሌግራም ላይ ቀድመው ለተመዘገቡ አስራ አምስት አባላት ስልጠናውን እንሰጣለን።
. ስም
. ስልክ
. የሚያገለግሉበት ክፍልን በመጥቀስ
መልእክት በመላክ መመዝገብ ይቻላል።
ማስታወሻ :-ስልጠናው ቀድመው ለተመዘገቡ 10 አባላት የምናስቀድም ሲሆን እንደየ አመዘጋገባችሁ ቅደም ተከተል ለቀጣይ ዙር ስልጠና አመቻችተን የምናዘጋጅ ይሆናል።
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ሚዲያ ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የተከበራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ከሚዲያ ክፍላችን ጋር ተባባሪ በመሆን ለማገልገል የምትፈልጉ አባላት በተለይ ሙያው ያላችሁ / ሙያው ከሌላችሁ ደግሞ ስልጠና በመውሰድ ልታገለግሉ የምትችሉ ፍላጎት ያላችሁ እንድታሳውቁን እና በጋራ እንድናገለግል ጎላ መምጣት ባትችሉም ባላችሁበት ሆናችሁ በተለይ የግራፊክስ ፣ የኤዲቲንግ ስራዎችን እንድታግዙን በትህትና እንጠይቃለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የተከበራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ከሚዲያ ክፍላችን ጋር ተባባሪ በመሆን ለማገልገል የምትፈልጉ አባላት በተለይ ሙያው ያላችሁ / ሙያው ከሌላችሁ ደግሞ ስልጠና በመውሰድ ልታገለግሉ የምትችሉ ፍላጎት ያላችሁ እንድታሳውቁን እና በጋራ እንድናገለግል ጎላ መምጣት ባትችሉም ባላችሁበት ሆናችሁ በተለይ የግራፊክስ ፣ የኤዲቲንግ ስራዎችን እንድታግዙን
በትህትና እንጠይቃለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ዕርገተ እግዚእ
"እስከ ቢታንያም አወጣቸው። እጆቹንም አንስቶ ባረካቸው። ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ። ወደ ሰማይም ዐረገ። እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ።
"ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።" አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።"
" ደግሞም፦ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።" (የሐዋርያት ሥራ 1፥11)
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
አስቸኳይ የስራ ማስታወቂያ
የስራ ዓይነት፦ ካፌ ሱፐርቫይዘር
የስራ ቀናት፦ በሳምንት 6 ቀን
የስራ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 1:00 - እስከምሽቱ 12:00
ፆታ፦ ሴት
የስራ ቦታ፦ ብስራተ ገብርኤል አካባቢ
ተፈላጊ ችሎታ፦ 10ኛ ክፍልና በንቃት መስራት የምትችል
ደምዝ፦ በወር 6500 ብር
ማሳሰቢያ:- የሰንበት ት/ትቤታችን አባላት የሆናችሁና የስራ ዕድል ሲመጣልን እንድናገናኝዎ የምትፈልጉ ወይም ይህ መረጃ የሚያደርሳቸውና የሚያስፈልጋቸውን አባላት የምታውቁ ከታች በተቀመጡ ስልኮች በመደወል እንዲያስመዘግቡ በትህትና እንጠይቃለን
093114-44-44 ሙሉጌታ ሰማን
0966-25-87-38 ዮሐንስ ትዳሩ
0912-48-65-04 ታምሩ ማሬ
የበጎ አድራት ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ውድ የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤታችን አባላት እንኳን ለታላቁ መልዐክ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል በሰላም አደረሳቹ እያልን ለበዓሉ ልብሰ ስብሀት(ዩኒፎርም) የሚሰጥበት ቀን የሂሳብና ንብረት አስተዳደር ክፍል ያወጣ ስለሆነ በተመደበው ቀን መጥታቹ እንድትወስዱ በቅዱስ ሚካኤል ስም እንጠይቃለን
ለህፃናት..07/10/2016
ለማዕከላዊያን..08/10/2016
ለወጣት ...09/10/2016
ለባለትዳር...09/10/2016/ 10/10/2016
መሆኑን እየገለፅን ከዚህ ቀን ውጪ የሚመጣ ማንኛውንም አባል የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።https://t.me/finotebirhan12
ውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ
ለ/ሰ/ት/ቤታችን አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ቀን ደረሰ!!
ወርኃዊ መዋጮ እስከ ሰኔ 10 ድረስ ይክፈሉ። አገልግሎታችንን እናሳድግ መንፈሳዊ የአባልነት ግዴታችንን እንወጣ። 1000555650594 በአካውንታችን ሲያስገቡ (ወርሐዊ አስተዋጽኦ ) ብለው ይጻፉበት።
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ልማት ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ቁርባን )በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ የመጨረሻ ክፍል ሊሰጥ አንድ ቀን ቀረው ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ አባላትም በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ቅዱስ ሲኖዶስ በግብረ ሰዶማዊነትና በተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ምን ወሰነ ?፦
➛ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣
➛ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ #የተከለከለ፣
➛ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣
➛ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣
➛ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ አጥብቆ #እንደሚያወግዝ ገልጿል።
#የተመሳሳይ_ጾታ_ጋብቻ እና #የግብረ_ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱሳን አበው ሐዋርያት ትውፊት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በርካታ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ውይይት ሲያካሄድ ሰንብቷል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1.በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤
2.በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን ያቀርባል፤
3.በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያናችን ይዞታዎች የከተማ አስተዳደሩ ምትክ ቦታ በመስጠትና ቤተ ክርስቲያናችን ወደ መልሶ ማልማት እንድትገባ ድጋፍ በማድረግ፤ በተለይም ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በፈረሰው የጽርሐ ምኒልክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃ ምትክ በከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጭ ተጨማሪ ምድር ቤትና የቦታ ስፋት ያለው B+G+4 ሕንፃ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል በመግባትና የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ኃላፊ አባቶች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ እንዲጣል ማድርጋቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ከምስጋና ጋር የተቀበለው ሲሆን በተሰጠን ምትክ ቦታ ላይም የከተማው ፕላን በሚፈቅደው መሠረት የመልሶ ማልማት ሥራው እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
4.የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ መረዳት እንደሚቻለው ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው እናት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
5.የብፁዓን አባቶች የዝውውርና የአህጉረ ስብከት ሥያሜን አስምልክቶ የቀረቡ ጥያቄዎችን ምልዐተ ጉበኤው ተመልክቶ ተገቢውን ውሳኔ አሳልፏል፤
6.የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በረቂቅ አዋጁ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ያመነባቸውን የማሻሻያ ሐሳቦች በማዘጋጀት ለሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም እንዲላክና ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተሰጡት የማሻሻያ ሐሳቦች በረቂቁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
7.በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑ ቢታወቅም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተከሰቱትን ወቅታዊ ችግሮች አስመልክቶ እየተላለፉ ያሉ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ መልእክቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸውና በጥብቅ የሚቃወማቸው መሆኑን እየገለጸ ወደፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ለማድረግ ይቻል ዘንድ ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
8.ግብረ ሰዶማዊነትና የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ እያወገዘ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና የግብረ ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
9.በደቡብ የሀገራችን ክፍል የቤተ ክርስቲያኒቱን አብነት ትምህርት ከማስፋፋትና ከፍ ያለ መዐርግ ከመስጠት አንፃር የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዝጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት ማስመስከሪያ ትምህርት ቤት እንዲሆን በቀረበው ጥናት መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ለምሥክር ጉባኤ ቤቱ ዕውቅና በመስጠት ወደ ትግበራ እንዲገባ ወስኗል፡፡
10.ከሀገራችን ውጭ ባሉ አህጉረ ሰብከት መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚላኩ አገልጋዮች በክፍሉ ሊቀጳጳስ ሲጠየቅ በሙያ ብቃታቸው፣ በምግባራቸውና በመንፈሳዊነታቸው የተመሰከረላቸው አገልጋዮች ከሁሉም አህጉረ ስብከት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አቅራቢነት በውድድር እየተለዩ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
11.የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚሁም መሠረት ለአፈጻጸሙ ያመች ዘንድ በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን መዋቅራዊ አደረጃጀት በማጽደቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
12.በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ2017 ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት ፳፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
+1
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
በዛሬው እለት ግንቦት 25 /2016 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ሰይፉ አየለ እና መቅደስ ፍትህአወቅ የአብርሃምን እና የሣራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ወላዲተ አምላክ በሰጋዊ ሳይሆን በመንፈሰ አይኖቻችን ለማያት ከልባችን ጓጉትን እንሻለን እና ለዚያ ክብር ታብቃን።
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ቁርባን )በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ ሊሰጥ ሦስት ቀን ቀረው ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ አባላትም በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ደብረ ምጥማቅ
ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።
እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም። ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል። አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ።
ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል ።
ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው። ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል። ሁለተኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ።
ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር።
እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳዪኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች። ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል።
እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል። ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ።
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
+4
የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናውኗል።
ምንጭ: የኢኦቴቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
