የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Ir al canal en Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Mostrar más2 631
Suscriptores
+624 horas
+267 días
+4830 días
Archivo de publicaciones
+9
የመስቀል ደመራ በዓል መስከረም 16/2017 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፣ የኢፌዴሪ ኘሬዝዳንት ወ/ሮ ሣህለወርቅ ዘውዴ ብጹአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመንግስት ባለስልጣናት የተለያዩ አቢያተ ክርስቲያን ተወካዮች እንግዶች ሕዝበ ክርስቲያን እና ሌሎችም በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 16 ቀን 2017ዓ.ም.
©የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
“እስመ ነገረ መስቀሉሰ ዕበድ ውእቱ በኀበ ኅጉላን ወበኀቤነሰ ለእለ ድኅነ ኃይለ እግዚአብሔር ውእቱ፤ የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ነው፤ ለኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው”(1ቆሮ. 1÷08)፤
በመስቀሉ ኃይል ከፍዳ ኃጢአት ያዳነን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት በዓለ ቅዱስ መስቀል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
ጌታችን በዚህ ዓለም በተገለጸበት ዘመን የግሪካውያን ፍልስፍና ሰፊ ስፍራ አግኝቶ በመካከለኛው ምሥራቅ በሰሜን አፍሪካና በአውሮፓ የተስፋፋበት ዘመን ነበር፤ የግሪካውያን ባህልና ፍልስፍና የተመሠረተው በግዙፉ ቁስ ላይ እንደመሆኑ በግዙፉ መሳሪያ ላይ የሚተማመን ነበረ፤ ይህ ዓይነት አስተሳሰብ ሥር ሰዶ በነበረበት ጊዜ ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈሳዊ ኃይል በዚህ ዓለም ተገለጠ፤ ጌታችን በሰው መካከል ተገኝቶ አጋንንትን ወደ ጥልቁ ሲያሰምጥ፣ ልዩ ልዩ በሽታና ደዌ ያላቸውን ሲያድን፣ ሙታንን ሲያነሣ፣ ብዙ ተአምራትንና አስደናቂ ነገሮችን ሲያሳይ በመንፈሳዊ ኃይል እንጂ በቁሳዊ ኃይል አልነበረም፤ በመሆኑም በወቅቱ በዓለም ውስጥ ቁሳዊ ኃይልና መንፈሳዊ ኃይል ተብለው የሚታወቁ እነዚህ ሁለት ኃይላት እርስ በርስ ይጋጩ ነበር፤ ዓለም በቁሳዊ ኃይል ተማምኖ በጉልበት የሚያደቀውን በመሳሪያ የሚቀጠቅጠውን ሲሻ፣ መንፈሳዊው ኃይል ደግሞ ከቊሳዊ ኃይል በላይ የሆነውን መለኮታዊ ኃይል በመጠቀም የሰውን ሁለንተና ሕይወት ለማዳን ይሰራ ነበር፤
እነዚህ ኃይሎች ከሥር መሠረቱ አነሣሣቸው፣ አመጣጣቸውና የኋላ ጀርባቸው የተለያየ በመሆኑ የሚጣጣሙ አልነበሩም፤ በዚህ ዓለም ጥበብ ወይም ፍልስፍና የሚተማመኑቱ ግሪካውያን የመስቀሉን ቃል ሲሰሙ እንደ ሞኝነትም እንደ ድክመትም አድርገው ይመለከቱ ነበር፤ ወልደ እግዚአብሔር በሥጋ በዚህ ዓለም ተገለጠ፤ በለበሰው ሥጋም በኛ ፈንታ ቤዛ ሆኖ በመስቀል ላይ ሞተ፤ በሞቱም እኛን ከረቂቁ ፍዳ ኃጢአት አዳነን የሚለውን የመስቀሉ ቃል ወይም አስተምህሮ ቁሳውያን እንደሞኝነትም እንደ ደካማነትም በመመልከታቸው ለጊዜውም ቢሆን የመስቀሉ ቃል ጠጥሮአቸዋል፡፡
ይህም በመሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመስቀሉ ቃል ሞኝነት መስሎ ለሚታያቸው የመጨረሻ ዕድላቸው መጥፋት ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ የመስቀሉ ቃል ሰውን ለማዳን የተደረገ የእግዚብሔር ኃይል እንደሆነ አምነው ለሚቀበሉና ለሚኖሩበት የመጨረሻ ዕድላቸው መዳን ነው በማለት የሁለቱም ዕድል አነጻጽሮ ይገልጻል፤ የቊሳውያን ግንዛቤ በቊሳዊው ዓለም የተገደበ ስለሆነ ስለ መንፈሳዊው ዓለም የሚያውቁት ባለመኖሩና ለማወቅም ተነሳሽነቱ በማነሱ፣ በሌላም በኩል መንፈሳውያኑ ደግሞ ከቊሳዊው ዓለም ባለፈ መንፈሳዊው ዓለም መኖሩና ዘላቂና ወሳኝ ኃይልም ያለው መንፈሳዊው ዘንድ ነው ስለሆነም ሰው በቊሳዊ ኃይል ሳይሆን በመንፈሳዊ ኃይል ዘላቂ ድኅነትን ያገኛል ብለው በማስተማራቸው ልዩነቱ ተፈጥሮአል፤ ከዚህ አንጻር የችግሩ ዋና ማጠንጠኛ የመንፈሳዊው ኃይል መኖርና አለመኖር ማወቅ ወይም ማመንና አለማመን ነበረ፤ ይህ እሳቤ ዛሬም ሳይቀር የዓለምን እሳቤ እንደሰነጠቀ ነው፤
ይሁን እንጂ በንጹህ ኅሊና በቅን ሰብእና እንደዚሁም በጥልቅ አእምሮ ለሚያስተውለው ሰው፣ ሓቁ ብዙም የራቀና የረቀቀ አይደለም፤ ምክንያቱም ዓለም እየተመራ ያለው በሚታየው ግዙፍና ደካማ ቊስ ሳይሆን በማይታየውና በረቂቁ መንፈሳዊ ኃይል እንደሆነ ሥነ ፍጥረት ይመሰክራልና ነው፤ በዓለማችን ለሚከናወኑት ቊሳዊና መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ሙሉ መልስ ያለው መንፈሳዊው ኃይል እንጂ ቊሳዊው ኃይል አይደለም፤ እንዳልሆነም ኅሊናችን ይመሰክርልናል፡፡ ዛሬ በከፍተኛ ሃይማኖታዊ ሥነ በዓል የምናከብረው የቅዱስ መስቀል በዓልም ከዚህ በላይ የጠቀስነው የሁለቱ አካላት ግጭት የፈጠረው ክሥተት ነው፤ መንፈሳዊው ሰው ከመስቀሉ በቀር ከፍዳ ኃጢአት እድንበታለሁ የምለው ሌላ ትምክህት የለኝም ብሎ የመስቀሉን ዘላቂ አዳኝነትን ከፍ አድርጎ ሲዘምር፣ ቊሳዊው ኃይል አልተመቸውም፤ ዝም ብሎ ማየትም ምርጫው አልነበረም፤ ስለሆነም ባለው ዓቅም ሁሉ ተንቀሳቅሶ መስቀሉን ከገጸ ምድር በማስወገድ በእሱ ላይ የተመሠረተውን አስተምህሮና እምነት እንዳይነሣም እንዳይወሳም በማሰብ መስቀሉን ቀበረ፤ ቊሳውያን መስቀሉን ቢቀብሩትም የመስቀሉን ቃል ሊቀብሩ አልቻሉም፤
ምክንያቱም የመስቀሉ ቃል ቊሳዊ ሳይሆን መንፈሳዊ፣ ውጫዊ ሳይሆን ውስጣዊ፣ ምድራዊ ሳይሆን ሰማያዊ፣ ሰብአዊ ሳይሆን መለኮታዊ፣ ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላለማዊ ነውና፤ ይህም በመሆኑ ቊሳዊ የሆነው ዕፀ መስቀል ቢቀበርም እሱ የተሸከመው ቃለ ድኅነት በረቂቁ የሰው አእምሮ ተቀርጾና ተዘግቦ ስለሚኖር ተቀብሮ ሊቀር አልቻለም፤ በሂደትም ያልተቀበረው የመስቀሉ ቃለ ድኅነት በንግሥት ዕሌኒ አእምሮ ውስጥ የእምነት ኃይል አቀጣጥሎ የተቀበረውን ዕፀ መስቀል በዛሬው ዕለት ከጥልቅ ጉድጓድ አውጥቶአል፤ በዚህም አሸናፊነቱን አረጋግጦአል፤ ዛሬ የምናከብረው በዓልም ይኸው ኃይለ እግዚአብሔር ለማሰብና በሱ ያለንን እምነት ለማስጠበቅና ቃለ ድኅነቱን ለማሥረጽ ነው፤ መስቀል ኃያልና አሸናፊ ቢሆንም ረቂቁንም ሆነ ግዙፉን ጠላት የሚያሸንፈው በሐቅና በሰላም፣ ኅሊናን በመርታትና በማሳመን እንጂ እንደ ቊሳዊ ኃይል አይደለምና እነሆ ዕፀ መስቀሉ በዛሬው ዕለት በኃይለ እግዚአብሔር በታጀበ ጢሰ-ዕጣን ከተቀበረበት ጉድጓድ በሰላም ሊወጣ ችሎአል፡፡
የመስቀሉ ቃል ዛሬም ተቃራኒ ኃይል አላጣም፤ ዛሬም ለመስቀሉ ቃል ጀርባቸውን የሚሰጡ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ከዚህም የተነሣ ስጋቱ ጭንቀቱ ግጭቱ አለመተማመኑ በዓለማችን ከምን ጊዜውም በላይ ተንሰራፍቶአል፤ ሀገራችንም ከዚህ የተለየች ልትሆን አልቻለችም፤ በዓለ መስቀሉን ከማንኛውም ክፍለ ዓለም በተለየ ሥነ ሥርዓት ብናከብርም የመስቀሉ ሰላም ግን በሀገራችንና በሕዝባችን እየተነበበ አይደለም፤ ይህንን ለማስገንዘብ የሚተላለፈው መልእክትም እየተደመጠ አይመስልም፤ የመስቀሉ ቃል ማለት ሰዎች በነፍሳቸውም ሆነ በሥጋቸው የተሟላ ደኅንነት ያግኙ ማለት ነው፤ የመስቀሉ ቃል ማለት የሰዎች ሃይማኖታዊ ነጻነት ይከበር፤ በሕይወት የመኖር ሰብአዊ መብታቸውም ይጠበቅ ማለት ነው፤ የመስቀሉ ቃል ማለት ሰዎች በዚች ምድር በእኩልነት በአንድነት በመተጋገዝ በመረዳዳት በፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል በሰላም በፍቅር በስምምነት በመተባበር ይኑሩ ማለት ነው፤
የመስቀሉ ቃል ማለት የሰው ሕይወት በዚህ ዓለም የተገደበ አይደለም ዘላለማዊ በሆነው መንፈሳዊ ዓለምም ሕይወት በቀዋሚነት ይቀጥላልና እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ለእርሱም ታዘዙና ተገዙ ማለት ነው፤ የመስቀሉ ቃል ማለት በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በፈሰሰው ደም የመዳን ዕድል ተከፍቶላችኋልና በደሙ ታጥባችሁ ወደ እግዚብሔር መንግሥት ግቡ ማለት ነው፤ ይህንን የመስቀል ቃል ዓለም ብትቀበለው ኖሮ በየጊዜው እያንዣበባት ያለው ስጋት ሁሉ ቦታ አይኖረውም ነበር፤ አሁንም በመስቀሉ ስም ለዓለም ሕዝብም ሆነ ለሀገራችን ዜጎች ሁሉ የምናስተላልፈው ዓቢይ መልእክት የመስቀሉ ቃል ሁላችንንም በእኩልነትና በፍቅር የሚያስተናግድ ነውና እሱን እንቀበል፤ የዓለም ስጋቶች በሙሉ ሊቀረፉ የሚችሉ በመስቀሉ ቃል ብቻ ነውና የሚል ነው፡፡
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ በዓል ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!! አሜን::
እጸ መስቀል
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ::
ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት።
ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡
ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡
ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡
መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት
የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የተከበራችሁ የባለ ትዳር ጉባኤ አባላት በሙሉ
አምላካችን በሰላም በፍቅር በጤና ጠብቆ ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ ስላሸጋገረን ክብርና ምስጋና ይድረሰው።
🌹 ዕድሜ ለንስሃ ፤ዘመን ለፍስሐ የተሰጠን የንስሃ ፍሬ አፍርተን መንግስቱን እንድወርስ ነውና ፈጣሪያችን ልንማጸነው ይገባል።
የ 2017 ዓ.ም የመጀመሪያው የባለ ትዳር ጉባኤ የፊታችን እሑድ መስከረም 19 ከ5:30-7:00 የሚከናወን በመሆኑ ሁላችሁም እንድትገኙ በክብር ተጠርተዋል።
የባለ ትዳር ጉባኤ ክፍል።
ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ጠቅላላ ጉባኤ
⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
“ እርስ በእርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።” ፩ኛ ተሰሎንቄ ፭፥፲፩
የዕለቱ የጉባኤው አጀንዳ
"የ2017ዓ.ም የአገልግሎት ዘመን ምክክር ስለ ማድረግ"
🗓እሑድ
መስከረም 26/2017ዓ.ም
⏰ ከምሽቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ
💒በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ
ጠቅላላ ጉባኤው ላይ በመገኘት መልዕክቱን የሰማችሁ ላልሰሙት ጥሪውን በማዳረስ የአባልነት ግዴታዎን ይወጡ ።
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ተገኝተው ከምዕራብ ክፍለ ከተማ ገዳማትና አድባራት ተዋጣጥተው ለመስቀል ደመራ በዓል በዝግጅት ላይ ለሚገኙት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት መልእክትና አባታዊ ቡራኬ አስተላለፉ።
በመልእክታቸውም ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እግዚአብሔር ለአገልግሎት ጠርቶ ስላከበራችሁ ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን እንኳን ደስ አላችሁ ብለው ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቿ ተከብራ በልዩ ጣዕመ ዜማ ታጀባ በማንኛውም ክብረ በዓል ላይ እግዚአብሔር ሲመሰገን ማየት እጅግ ደስ ያሰኛልና በዓሉ የሰላም በዓል የድኅነት በዓል እንደመሆኑ ለሰላም ትልቅ ትኩረት በመስጠት ከሚመለከታቸው ክፍሎችም ጋር በጋራ በመስራት ሁላችን ዐይን እና ጆሮ ሆነን በስማችን ክፉ ሥራን በመስራት የቤተክርስቲያንን ስም የሚያጠለሽ እንዳይኖር እየዘመርንም ተግቶ ሥራ መሥራት ይገባል ብለዋል። የአደባባይ በዓል በመሆኑም የሚመጣውም ሁሉ የሚማርበት እንዲሆን የአደራ መልእክታቸውንም አክለዋል።
© የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የተከበራችሁ የባለ ትዳር ጉባኤ አባላት በሙሉ
አምላካችን በሰላም በፍቅር በጤና ጠብቆ ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ ስላሸጋገረን ክብርና ምስጋና ይድረሰው።
🌹 ዕድሜ ለንስሃ ፤ዘመን ለፍስሐ የተሰጠን የንስሃ ፍሬ አፍርተን መንግስቱን እንድወርስ ነውና ፈጣሪያችን ልንማጸነው ይገባል።
የ 2017 ዓ.ም የመጀመሪያው የባለ ትዳር ጉባኤ የፊታችን እሑድ መስከረም 19 ከ5:30-7:00 የሚከናወን በመሆኑ ሁላችሁም እንድትገኙ በክብር ተጠርተዋል።
የባለ ትዳር ጉባኤ ክፍል።
ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የቅዱስ መስቀል ደመራ በዓል ፍፁም መንፈሳዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል የሚጠበቅበትን ሁሉ እንዲያደርግ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም ጥሪ አቀረቡ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ፳፻፲፯ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁና የቅድመ ጥንቃቄ መልእክት አስተላለፉ።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በዚሁ መልዕክታቸው ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ካሉ በኋላ በዓሉ በድምቀት፣ባማረና በሰመረ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በንቃትና በሕብረት በመሆን ከጸጥታ አካላትና ቤተክርስቲያኒቱ ለዚሁ ዓላማ ካቋቋመቻቸው የኮሚቴ አባላት ጭምር በመተባበር እንዲሰራ አደራ ብለዋል።
የመንግሥት የጸጥታ ተቋማት በዓሉ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር ተከብሮ መዋል እንዲችል ከጠቅላይ ቤተክህነት ዐቢይ ኮሚቴ ጋር በጥምረት እየሰራ እንደሚገኝ የጠቀሱት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በበዓሉ ወቅት ለሚደረግ ፍተሻ ፍፁም ክርስቲያናዊ ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል።የጸጥታ አስከባሪዎችም ጨዋነት በተምላና ክብርን በሚገልጽ አግባብ የፍተሻ ሥርዓቱን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።
ከበዓላችን መንፈሳዊ ሥርዓት ውጪ የሆኑ መልዕክቶች፣ አለባበሶች እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱ መገለጫ ከሆኑ ዓርማዎች ውጭ እንዳይዙ በዓሉ ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ እንደመሆኑ ቤተክርስቲያኒቱን ከማይገልጹ ሆታዎችና ጭፈራዎች እንዲርቁ በአጠቃላይ ያልተፈቀዱ ነገሮችን ሁሉ የመስቀል ደመራ በሚከበርባቸው ቦታዎች ሁሉ ይዞ መገኘት ፍጹም መንፈሳዊ የሆነውን በዓላችንን የሚያደበዝዘው ስለሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቻችን ከሚያቀርቡት መንፈሳዊ ትርኢትና ዝማሬ ጎን ለጎን አካባቢያቸውን በመቆጣጠር በዓላችንን በሰላም እንዳናከብር የሚያደርጉ ሁኔታዎች እንዳይፈጠሩ በጥንቃቄ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በሌላ መልኩም የሌሎች እምነት ተከታዮችም በነበረውና በኖረው የመከባበርና የመደማመጥ የአብሮነት ስሜት በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንዲወጡ የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የበዓሉ ዝግጅት በየደረጃው በተቋቋሙት የበዓል አዘጋጅ ኮሚቴዎች ጥረት በጥሩ ሁኔታ በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን የገለፁት ብፁዕነታቸው ከንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት ወዲህ ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሦስተኛ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓልን በድምቀት ማክበር የሚያስችል የስቴጅ፣የድምጽ ማጉያና የክብር እንግዶች ማስተናገጃ ቦታዎችን በማዘጋጀት የሚያደርገውን ተሳትፎ ያደነቁት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ላለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ በራሳቸውና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክን ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በመጨረሻም በዓሉን ስናከብር ፍቅር ሰላምንና አንድነትን እንዲሁም መግባባትን መርህ ባደረገ አግባብ መሆን አለበት ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በዓሉ ሥጋዊ ፈቃዶቻችንን የምንፈጽምበት ሳይሆን ንስሐ ያልገቡ ንስሐ የሚገቡበት የተጣሉ የሚታረቁበት የተለያዩ አንድ የሚሆኑበት የተራራቁ የሚቀራረቡበት ፍፁም የደስታና የሰላም በዓል ሆኖ እንዲከበር ማድረግ ይኖርብናል በማለት መልዕክታቸውን አጠናቀዋል።
ዘገባው የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት ያለፈው ቅዳሜና እሑድን በደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ የመስቀል ጥናት ስታጠኑ የነበራችሁ አባላት ከዛሬ ማክሰኞ ጀምሮ ልብሰ ስብሐት የሚሰጥ በመሆኑ መጥታችሁ እንድትወስዱ እያሳሰብን ሐሙስ መስከረም 16/2017ዓ.ም የምንችል አባላት 5:00 ላይ በደብራችን ጎላ ተገናኝተን አብረን የምንሄድ ይሆናል በሰዓቱ ጎላ መገኘት የማትችሉ አባላት ግን ግዴታ 6:00 ላይ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ መድረስ ይኖርብናል።
ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
