1 480
Suscriptores
-124 horas
-47 días
-1530 días
Archivo de publicaciones
1 480
ቀን:- ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም
ጉዳዩ:- የተማሪ ትራንስፖርት ይመለከታል።
በትራንስፖርት ጉዳይ መረጃ የምትፈልጉ ወላጆች በዚህ ስልክ በመደወል መረጃ መግኘት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን።
👉091 205 3876 ቴዲ
ት/ቤቱ
1 480
Good News and Congratulations from Joint Vision Success Academy!
🎉🎉🎉🎉🎉🌸🌸🌸
Dear Parents and Legal Guardians of our school community,
Congratulations! 🏆🎉👏
First and foremost, our entire school community gives thanks to the Almighty for bringing us to this great day. 🙏🙏🙏🙏🙏
Our 2018 E.C. ( 2025/26) University Entrance Examination, Grade 12 national exam candidates worked tirelessly day and night to achieve highly impressive results. Among the students who took the exam, 78% have passed to university with excellent scores. The rest 22% will join remedial class.
Our school’s highest score is 540 out of 600, achieved by student Eyosiyas Girma. Thank you, you made us proud! 👌👏👏👏
This grand success is the result of:
The immense effort of our students
The continuous support of our teachers
The unreserved guidance and follow-up of our parents
The success of our students is the fruit of your hard work and a source of pride. Therefore, the entire Joint Vision Success Academy community wishes to say congratulations to you, and congratulations to us all, for this brilliant achievement!
We sincerely wish our children a beautiful and highly successful journey in their upcoming higher education and future endeavors. 💫🌾👏👏👏👏👏🌾🌾🌾🌾
Our cooperation for knowledge; our vision for success.
Joint Vision Success Academy
Kabajamtoota Maatii/Guddistoota Barattoota Mana Barumsaa Keenyaa፤
Congratulations!!!
🏆🏆🏆🏆🏆🎉🎉🎉🎉🎉👏🌾🌾
Dursa hundi hawaasni mana barumsaa keenyaa guyyaa guddaa kanaaf nu geesseef Uumama galateeffata.
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Qormaanni Biyyaalessaa Kutaa 12ffaa Bara 2018 barattoonni keenya halkan fi guyyaa cimanii hojjechuun bu'aa baay'ee gaarii galmeessaniiru. Barattoota qoraman keessaa 78% ta'an qabxii gaariin gara Yuunivarsiitiitti darban. Qabxiin mana barumsaa keenya olaanaan 540/600 yeroo ta'u, barataa Iyoosyaas Girmaatiin galmeeffame. Galatoomaa, itti gammaduu qabdu! 👌👌👌👌👌👌👌👌👌👌
Milkaa'inni guddaan kun kan argame:
Carraaqqii olaanaa barattoota keenyaatiin,
Deeggarsa walitti fufaa barsiisotaatiin, fi
Deeggarsaafi hordoffii maatii isa hin dhumneen dha.
Milkaa'inni barattoota keenyaa bu'aa hojii keessaniifi boonsaa keessaniis. Kanaafuu, bu'aa miidhagaa galmeeffameef hawaasni mana barumsaa Joint Vision Success Academy hundi "Baga gammaddan, baga nuuf gammade" jechuu ni barbaada.
Jireenyi barnoota olaanaa fuulduraafi imalli borii ijoollee keenyaa caalaatti miidhagaafi milkaa'aa akka ta'u garaa guututti hawwina.
💫💫💫💫💫🌾🌾🌾🌾👏👏👏👏
Tumsi keenya Beekumsaaf፤ Mul'anni keenya Milkaa'inaaf።
Joint Vision Success Academy
የእንኳን ደስ አላችሁ የምስራች መልዕክት ከጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ!
ክቡራን የትምህርት ቤታችን ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች፤
Congratulations!!!
🏆🏆🏆🏆🏆🎉🎉🎉🎉🎉👏🌾🌾
በመጀመሪያ መላው የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ ለዚህ ታላቅ ቀን ስላደረሰን ፈጣሪን ያመሰግናል።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ማጠናቀቂያ ፈተና ተማሪዎቻችን ሌት ተቀን በትጋት አጣምረው በመስራት እጅግ በጣም አመርቂ ውጤት አስመዝግበዋል። ከተፈተኑት ተማሪዎች መካከል 78% ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲ በጥሩ ውጤት ያለፉ ሲሆን የቀሩት ደግሞ በሪሚድያል ይካተታሉ። የት/ቤታችን ከፍተኛ ውጤት 540/600 በተማሪ ኢዮስያስ ግርማ ነው። እናመሰግናለን ኮርቶንባሀል!!!👌👌👌👌👌👌👌👌👌👌
ይህ ታላቅ ስኬት የተገኘው፦
በተማሪዎቻችን ከፍተኛ ጥረት ፥ የመምህራን ተከታታይ እገዛ እና
ባልተቆጠበ የወላጅ ድጋፍ እና ክትትል ነው።
የተማሪዎቻችን ስኬት የእናንተም የስራችሁ ፍሬ እና ኩራት ነው። በመሆኑም ለተመዘገበው ደማቅ ውጤት መላው የጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ፤ ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
የልጆቻችን ቀጣይ የከፍተኛ ትምህርት ህይወት እና የወደፊት ጉዟቸው ይበልጥ ያማረና የተሳካ እንዲሆን ከልብ እንመኛለን።
💫💫💫💫💫🌾🌾🌾🌾👏👏👏👏
ትብብራችን ለእውቀት፤ ራዕያችን ለስኬት።
ጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ
1 480
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
1 480
ለ2019ዓ.ም ት/ት ዘመን ልጆን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች ምዝገባ ስለተጠናቀቀ በአስቸኳይ መልቀቂያ እንድት ወስዱ አንገልፃለን ።
ት/ቤቱ
1 480
አቡነ ባስሊዮስ ክላስተር ማዕከል የምትማሩ የ11&12ክፍል ተማሪዎች ነገ ነሃሴ 1/12/2018ዓ.ም የክፍል ውስጥ ኪዉዝ ስለሚሰጥ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
1 480
ለወላጅ ወይም አሳዳጊዎች በሙሉ
የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ የዘጠነኛ ክፍል የጨረስን ሲሆን:ሌሎች ክፍል ላይ ውስን ቦታዎች ብቻ የቀሩን መሆኑን እንገልፃለን።ሁለተኛ ደረጃ
1 480
Repost from Joint vision success academy 1-8
The four pillars of education
(አራቱ የትምህርት አምዶች)
📚📚📚📚
✍️ 1. ለማወቅ መማር
✍️ 2. ለመሥራት መማር
✍️ 3. አብሮ ለመኖር መማር
✍️ 4. ለመሆን መማር
📚 የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) በጃክ ዴለርስ በሚመራው ኮሚሽን አማካኝነት የዘረጋቸው አራቱ የትምህርት አምዶች (Four Pillars of Education) ለ21ኛው ክፍለ ዘመን ትምህርት መሠረት ናቸው።
👉 እነዚህ አምዶች ትምህርት ዕውቀትን ብቻ ሳይሆን፣ ክህሎትንና ስብዕናን ማዳበር እንዳለበት ያመለክታሉ።(Skill plus Attitude)
✍️ 1. ለማወቅ መማር
(Learning to Know)
ይህ አምድ ትኩረት የሚያደርገው መሠረታዊ ዕውቀትን ከማግኘት ባለፈ፣ እንዴት መማር እንዳለብን መማር (Learning how to learn) ላይ ነው።
🎯 ዋና ዓላማ
🕯 ተማሪዎች ዓለምን እንዲረዱ፣ የማወቅ ጉጉታቸውን እንዲያሳድጉ እና የማስታወስ፣ የማሰብ እንዲሁም የማተኮር ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ ማስቻል።
🔑 ቁልፍ ነጥብ
👉 ዕውቀት በየጊዜው ስለሚለወጥ፣ አንድ ተማሪ በራሱ አዳዲስ መረጃዎችን የመፈለግና የመረዳት ፍላጎት እንዲኖረው ማድረግ ነው።
✍️ 2. ለመሥራት መማር (Learning to Do)
ዕውቀትን ወደ ተግባር መለወጥ ላይ ያተኩራል። ይህም ተማሪዎች የተማሩትን ነገር በተግባራዊ ሕይወታቸውና በሥራ ዓለም ላይ እንዲጠቀሙበት ያዘጋጃቸዋል።
🎯ዋና ዓላማ
🕯የሙያ ክህሎትን ማዳበር ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ችግር ፈቺነት፣ ከሰዎች ጋር በቡድን የመሥራት ብቃት እና በሥራ ላይ የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን የመቋቋም ችሎታን ማዳበር ነው።
🔑 ቁልፍ ነጥብ
👉 በአሁኑ ዘመን "ለመሥራት መማር" ሲባል በእጅ ከሚሠራ ሥራ (Manual Labor) ባለፈ፣ መረጃን የመተንተንና የፈጠራ ሥራዎችን የመሥራት ብቃትን ይጨምራል።
✍️ 3. አብሮ ለመኖር መማር (Learning to Live Together)
ይህ አምድ በዘመናዊው ዓለም ውስጥ እጅግ አስፈላጊው እንደሆነ ይታመናል። ትኩረቱም በሰዎች መካከል ሰላምን፣ መቻቻልንና መግባባትን መፍጠር ነው።
🎯ዋና ዓላማ
🕯 የሌሎችን ታሪክ፣ ባህልና እሴት ማክበር፣ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እና የጋራ ግቦችን ለማሳካት በጋራ መሥራትን መልመድ ነው።
🔑 ቁልፍ ነጥብ
👉 በትምህርት ቤት ውስጥ የሚከናወኑ የቡድን ሥራዎችና ውይይቶች ለዚህ አምድ ተግባራዊነት ትልቅ ድርሻ አላቸው።
✍️ 4. ለመሆን መማር (Learning to Be)
ይህ አምድ የሰውን ልጅ ሁለንተናዊ ዕድገት (Physical, Intellectual, Emotional, and Spiritual) የሚመለከት ነው።
🎯ዋና ዓላማ
🕯 እያንዳንዱ ግለሰብ የራሱ የሆነ ነፃነት፣ የማመዛዘን ችሎታ፣ የሥነ-ምግባር ጥንካሬ እና ኃላፊነት እንዲኖረው ማድረግ ነው።
🔑 ቁልፍ ነጥብ
👉 ትምህርት የአንድን ሰው የተደበቀ ተሰጥኦ (Potential) አውጥቶ ለራሱና ለማኅበረሰቡ የሚጠቅም ሙሉ ሰው እንዲሆን መርዳት አለበት።
ባጭሩ፦
✍️✍️✍️✍️ እነዚህ አራቱ አምዶች እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው። ለማወቅ መማር መሣሪያ ሲሆን፣ ለመሥራት መማር ተግባር ነው፣ አብሮ ለመኖር መማር ማኅበራዊ መሠረት ሲሆን፣ ለመሆን መማር ደግሞ የሦስቱም የመጨረሻ ውጤት ወይም ድምር ነው።
@Lifelong learner
🎯📌👇
Bloom's taxonomies of education
1.Cognitive domain
(Knowledge/HEAD)
2.Affective domain
(Attitude /HEART)
3.Psychomotor domain
(Skill/HAND)
1 480
ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ወላጆች እና አሳዳጊዎች።
የተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው ከ ሀምሌ 19_24 /2018ዓ.ም ሲሆን ልጆን በሰዓቱ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብ ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ለሚመጡ ወላጆች ቦታው በሌላ ተማሪ የሚያዝ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።
1 480
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች አሳዳጊዎች
የ2019ዓ.ም መደበኛ 11እና 12የሆኑ ተማሪዎች ክረምት የመማር ግዴታ እንዳለባቸው በተለያዩ ግዜያት የገለፅን መሆኑ ይተወቃል ።በመሆኑም የልጀመረችሁ በአሰቸኳይ እንድት ጀምሩ የማትጀምሩ በግዜ መሸኛ እንድትወስዱ በአክብሮት እንገልፃለን ።
1 480
ለወላጅ እና አሳዳጊዎች በሙሉ
በ21/10/2018ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው የተማሪዎች ውጤት መግለጫ ወይም ካርድ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ28/10/2018ዓ.ም የተለወጠ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
1 480
የክረምት ወቅት ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ልጆች ረጅም የዕረፍት ጊዜ የሚያሳልፉበት ወቅት ነው። ይህ ጊዜ ልጆች ዓመቱን ሙሉ ከነበረባቸው የትምህርት ጫና አዕምሯቸውን የሚያሳርፉበት ቢሆንም፣ ወላጆች በአግባቡ ካልመሩት ግን ጊዜያቸውን ያለአግባብ በስልክ፣ በቲቪ እና በቪዲዮ ጌሞች ብቻ በማሳለፍ አሰልቺ ሊሆንባቸው ይችላል።
ክረምትን ለልጆችዎ ሁለገብ ዕድገት (አካላዊ፣ አዕምሯዊ እና ማኅበራዊ) ጠቃሚና የማይረሳ ለማድረግ የሚከተሉትን ተግባራት ቢያቅዱ ይመረጣል፡-
1. አዳዲስ ክህሎቶችን ማዳበር
የመደበኛው ትምህርት መዘጋቱ ልጆች የሕይወት ክህሎቶችን እንዳይማሩ ሊያግዳቸው አይገባም። እንደውም ይህ ጊዜ አዳዲስ ነገሮችን ለመለማመድ ምቹ ነው።
• የዕድሜያቸውን ያህል በቤት ውስጥ ማሳተፍ፦ ምግብ ማብሰል፣ ቤት ማፅዳት፣ ልብስ ማጠፍ እና የአትክልት ቦታን መንከባከብ የመሰሉ የዕለት ተዕለት ተግባራትን እንዲለምዱ ያድርጉ። ይህ በራሳቸው የመተማመን ስሜትን ይገነባል።
• የእጅ ሥራዎች እና ስዕል፦ ልጆች የፈጠራ ችሎታቸውን እንዲያወጡ የስዕል፣ የዕደ-ጥበብ ወይም የልብስ ስፌት/ሹራብ ስራዎችን እንዲለማመዱ ግብዓቶችን አቅርቡላቸው።
2. የማንበብ ልምድን ማሳደግ
በትምህርት ቤት ቆይታቸው የማንበብ ልምዳቸው በመማሪያ መፃህፍት ላይ ብቻ የተገደበ ሊሆን ይችላል። በክረምት ግን ይህንን መቀየር ይቻላል።
• ከልጆችዎ የዕድሜ ክልል ጋር የሚመጥኑ፣ አስተማሪና አዝናኝ ታሪኮችን የያዙ መጻሕፍትን (በአማርኛም ሆነ በሌሎች ቋንቋዎች) ይግዙላቸው።
• በየቀኑ የተወሰነ ሰዓት (ለምሳሌ ከምሳ በኋላ ወይም ከመተኛታቸው በፊት) የጋራ የንባብ ሰዓት በማድረግ አብረው ያንብቡ፤ ካነበቡትም ምን እንደተረዱ እንዲያጫውቱዎት ያበረታቷቸው።
3. አካላዊ እንቅስቃሴ እና ስፖርት
ልጆች ቀኑን ሙሉ ተቀምጠው እንዲውሉ ማድረግ ለአካላዊና ለሥነ-ልቦና ጤንነታቸው መልካም አይደለም።
• የስፖርት ማዕከላት፦ አቅም በፈቀደ መልኩ ልጆችን በዋና፣ በኳስ ጨዋታ፣ በካራቴ ወይም በሌሎች የስፖርት ማሰልጠኛዎች ማሳተፍ።
• ጨዋታዎች፦ ከሰፈር ልጆች ጋር በአግባቡ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ እንዲሮጡ፣ ብስክሌት እንዲነዱ እና እንዲጫወቱ መፍቀድ ማኅበራዊ ግንኙነታቸውን ያጠናክረዋል።
4. መንፈሳዊና ስነ-ምግባራዊ እሴቶችን ማስተማር
የእረፍት ጊዜን ከሃይማኖታዊ እና ከባህላዊ እሴቶች ጋር ማገናኘት መልካም ስብዕና ያላቸው ልጆችን ለማሳደግ ወሳኝ ነው።
• በየእምነታቸው መሠረት ወደ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች (ሰንበት ትምህርት ቤት፣ ቁርዓን መቅሪያ ወዘተ) እንዲሄዱ ማድረግ።
• ረዳት የሌላቸውን መርዳት፣ ታላላቆችን ማክበር እና መልካም ስነ-ምግባርን በተግባር እንዲለማመዱ ማድረግ።
5. የዲጂታል መሣሪያዎች አጠቃቀምን መገደብ
በክረምት ወቅት ለወላጆች ትልቁ ፈተና የሚሆነው ልጆች ቀኑን ሙሉ ስልክ ወይም ቲቪ ላይ መጣበቃቸው ነው።
• ግልጽ ሕግ ማውጣት፦ በቀን ውስጥ ለስክሪን የሚፈቀደውን ሰዓት (ለምሳሌ 1 ወይም 2 ሰዓት ብቻ) መወሰን።
• ቴክኖሎጂን ለጠቃሚ ነገር መጠቀም፦ ጨዋታዎችን ብቻ ከመጫወት ይልቅ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ክህሎቶችንና ቋንቋዎችን እንዲማሩ ወይም ጠቃሚ ሳይንሳዊ ዶክመንተሪዎችን እንዲመለከቱ ማበረታታት።
#የማጠቃለያ_መልእክት
ልጆች ክረምቱን በአግባቡ እንዲያሳልፉ የወላጆች የቅርብ ክትትልና አብሮነት ወሳኝ ነው። ሁሉንም ነገር በዕቅድ መምራት (Schedule ማውጣት) ልጆቹ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ይረዳቸዋል። ከሁሉም በላይ ግን፣ የሥራ መደራረብ ቢኖርብዎትም፣ ከልጆችዎ ጋር ጥራት ያለው ጊዜ (Quality Time) በማሳለፍ፣ በመጫወትና ስሜታቸውን በማዳመጥ የቤተሰብ ፍቅርን የሚያጠነክሩበት ወቅት እንዲሆን ይመከራል።
መልካም የክረምት ዕረፍት ለልጆችዎ!
ከር/መ/ር መስፍን አሰፋ
1 480
በሁለተኛ ጀረጃ ቀጣይ የክንውን ሰሌዳ :
ሰኔ 17 ለሁሉም ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ውጤት ይሰጣል።
ሰኔ 21 የዓመቱ ትምህርት መዝጊያና የተማሪዎች ካርድ ይሰጣል።
ሀምሌ 6/2018ዓ.ም የቀጣይ ዓመት ምዝገባ ይጀምራል ።
ሀምሌ 6/2018ዓ.ም የክረምት ትምህርት ይጀምራል ነሀሴ 15/2018ዓ.ም.ያበቃል።
ዘወትር አርብ መሸኛ የሚወሰዱ ተማሪዎች የስተናገዳሉ።
1 480
ለጆይንት ቪዥን ሰክሰስ አካዳሚ ተማሪዎች በሙሉ። ከከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ በተላለፈ መመሪያ ከሰኞ ግንቦት24,2018- ረቡዕ ግንቦት 26, 2018 ዓ/ም ድረስ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እየገለፅን ሀሙስ ግንቦት 27,2018 ዓ/ም መደበኛ ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እናስታውቃለን።
