1 474
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2130 días
Archivo de publicaciones
ትላንት ሌሊት በሎሚ ሜዳ ኢንዲስትሪ መንደር ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል።
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሎሚ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከሌሊቱ 7:06 ሰዓት ገደማ በኢንደስትሪ
መንደሮች ባሉ ቬዶች ላይ አጋጥሞ የነበረው የእሳት አደጋ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ።
በእሳት አደጋው ሶስት አነስተኛ ሼዶች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን
እሳቱ ወደሌሎች በርካታ ሼዶች ላይ ተዛምቶ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል ።በአደጋው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission አስታውቋል።
በኢንዱስትሪ መንደር የሚገኙ ሼዶች የአደጋ ደህንነት መስፈርት ያልጠበቁ በመሆናቸው ለእሳት አደጋ የተጋለጡ ናቸው ::
በመሆኑም በኢንዱስትሪ መንደሩ ስራዎቻቸውን የሚያከናውኑ ማህበራት ለእሳት አደጋ የሚያጋልጡ አሠራሮችን ማስወገድና ከኮሚሽኑ ባለሞያዎች የሚሰጡ የሙያ ምክሮችን በመተግበር አደጋን አስቀድሞ መከላከል ይጠበቅባቸዋል ሲል ኮሚሽኑ አሳስቧል።
ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥሙ አደጋዎች የአደጋ ጊዜ ተሽከርካሪ መግቢያ መንገዶችን ነጻ ማድረግና የአደጋ መቆጣጠር ስራውን ምቹ ማድረግ እንደሚገባቸው ኮሚሽኑ አሳስቧል ።
ለእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!
ህዳር 10 /2018 አ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ሞዴል መንደሮችን እንፈጥራለን ለነዋሪዎቿ ምቹ ውብ የሆነችና ሰላሟ የተረጋገጠ ጉለሌን እንገነባለን !! "
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 እና ወረዳ 2 አስተዳደር ከቀበና ወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ተያይዞ የሚገኙ አካባቢዎች የተቀናጀ ዲዛይን ተኮር የሆነ ስማርት የሆነ ብሎክ መፍጠር በሁሉም ጨለማ ቦታዎች መብራት በማውጣት ወንጀልን መከላከል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጎዴቦ ፣ የከተማ ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
በምልከታው ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንደተናገሩት በከተማ አስተዳደሩ የተሰሩ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ስራዎች የከተማውን ገፅታ ቀይሮ የንግድ ስርዓቱን ያነቃቃ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ የቻለ በመሆኑ፣ ከዚህ ጋር የተመጣጠነ የተቀናጀ ብሎክ በመፍጠር የማህበረሰቡ ንፁህ እና ጤናማ በሆነ አከባቢ የመኖር መብት ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ለመፍጠር በንቅናቄ እየተሰራ ያለው ተግባር፣ ብሎኮችን ንፀህና ከጨለማ ነፃ በማድረግ ውብ ፣ ንጹህና ማራኪ የተረጋጋ ሰላምና ፀጥታ የሰፈነበት ለማድረግ ፋይዳው የላቀ እንደሆነ ገልጸው ይህንን ተግባር በትኩረት ለመሩ ፣ ለሰሩና ላስተባበሩ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው የክፍለ ከተማውን ሁለንተናዊ ሰላም ብልጽግና በማረጋገጥ ስራዎች በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛል በተለይም ህብረተሰቡን የልማቱ ዋነኛ ባለቤት እንዲሆን በማድረግ የተቀናጀ ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር የነዋሪውን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል በተለይም የሚፈጸሙ ወንጀሎች በመቀነስ ፣ የህብረተሰቡን ጤና በመጠበቅ የነገ ሃገር ተረካቢ ትውልድ ንጹህ አካባቢ በማውረስ የታዩ ለውጦች ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል።
ህብረተሰቡ የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ለመፍጠር ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለማልማት እያደረጉት ያለ አስተዋፆኦ ምስጋና አቅርበው በቀጣይም አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ይትባረክ ህብረተሰቡን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር አካባቢውን በማልማት ጽዱ ውብ በማድረግ ሰላሙን በማስጠበቅ ላይ ይገኛል ለዚህም ማሳያ የዛሬው የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ጉብኝት አንዱ አካል ነው ብለዋል።
ዜጋ ተኮር መሰረተ ልማት ቀዳሚ የትኩረት አቅጣጫችን ነው!!
ፒያሳ እና ካዛንቺስ እጅግ በተጨናነቁና ለመኖር አስቸጋሪ በሆኑ መንደሮች ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ነዋሪዎች በተለይም በተጣበቡና በተጎሳቆሉ፣ ለኑሮ ምቹ ባልሆኑ የሰውን ክብር በማይመጥኑ ቤቶች ዉስጥ ህይወትን መግፋት ለበርካቶች የዕለት ተዕለት ህይወት መሆኑ አይዘነጋም፤ ዛሬ ግን ታሪክ ሆኖ አልፏል!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ከተማን ማልማት፣ መሰረተ ልማትን መገንባት ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን ህይወት ማሻሻል ነዉ!” ብሎ በፅኑ በማመን እና ለልማት ተነሺዎች ፤ለተለያዩ ችግሮች ለተጋለጡ፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለአገር ባለውለታዎች እና በወንዝ ዳርቻዎች ለአደጋ ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያማከለ የቤት አማራጮችን በመዘርጋት በርካታ ቤቶችን ገንብቶ ለነዋሪዎች ማሰረከብ ችሏል፡፡
የተገነቡት ቤቶች የከተማዋን ጎስቋላ ገፅታ የቀየሩ ፣ የዜጎችን እምባ ያበሱ፣ ሰፋፊ የስራ ዕድል የፈጠሩ እና አገልግሎቶችን ያሳለጡ ከመሆናቸውም በተጨማሪ የህብረተሰቡን ገቢ ማሳደግ የቻሉ ገፀ-በረከቶችም ናቸው፡፡
ሁለገብ የጥገና ማዕከል ግንባታ በሚከናወንበት ቦታ ላይ ጉብኝት ተካሄደ
የአዲስ አበባ ከተማ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች ሁለገብ የጥገና ማዕከል ግንባታ ለማከናወን በመሰራት ላይ ያሉ ስራዎችን አስመልክቶ የመስክ ላይ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡
በየባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰብስብ ሁሴን ባለስልጣኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ቀልጣፋ፣ በይበልጥ ተደራሽና ዘመናዊ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
እየተከናወኑ ካሉት ስራዎች አንዱ ተቋማዊ አቅም በመፍጠር አገልግሎቱን ወደ ህብረተሰቡ ቅርብ ለማድረግ የሚያስችለውን የሁለገብ የጥገና ማዕከል ግንባታ መሆኑን አንስተው ስራው አሁን ላይ የደረሰበትን አፈፃፀም ከአመራሩ ጋር በጋራ መመልከት መቻሉን ገልፀዋል።
ከከተማ አስተዳደሩ ተረክቦ በጀሞ ሶስት መስታወት ፋብሪካ አካባቢ የሚገነባው ይህ ማዕከል በቀጣይ የመብራት ፖሎችን ለመጠገንና ለማምረት እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም ባለስልጣኑ የሚያስተዳድራቸውን ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች በራስ አቅም የተሟላ ጥገና በማድረግና ወደ ስራ በማሰመራት፤ የባለስልጣኑን አቅም በማሳደግ ከተማዋ ላይ ለሚከናወኑ ዘርፈ ብዙ የመብራት መሠረተ - ልማት ስራዎች ውጤታማነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ሲሉ ገልፀዋል።
አያይዘውም ዋና ዳይሬክተሩ በቀጣይ ይህን መሰል የሁለገብ የማዕከል ግንባታ ስራ በሌሎች ክፍለ ከተሞች በተመረጡ ቦታዎች ላይ ይቀጥላል ብለዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ህዳር ሲፀዳ አዲስ አበባ ጤና!
ንፁህ አካባቢ - ጤናማ ማህብረሰብ!
#ህዳር #ሲጸዳ
#Addis #ababa #Clean #City
Addis Ababa City Manager's Office
የአዲስ አበባ ከተማ የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ Addis Ababa Cleansing Management Agency
በመዲናችን አዲስ አበባ የስማርት መሠረተ ልማት አስተዳደራዊ ስርአትን መሠረት ባደረገ መልኩ አየተገነቡ ያሉ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች የከተማችን የእድገት ፍጥነት መሠረት ያደረገና ዛሬን ሳይሆን መጪውን ትውልድ ታሳቢ በማድረግ ለቀጣዮቹ 3… See more
በካዛንቺስ ፤ በአራት ኪሎ ፤ በአምስት ኪሎ እና በሽሮ ሜዳ በኮሪደር ልማቱ የተገነቡ እና ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ንግድ ቤቶች እና ፕላዛዎች ምስል በከፊል
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በቂርቆስ ክ/ከተማ የህብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበሩ የመንገድ መብራቶችን ማብራት መቻሉ ተገለፀ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን ባለፉት አራት ወራት ውስጥ በቂርቆስ ክ/ከተማ የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበሩ በርካታ መንገዶችን ከጨለማ ወደ ብርሀን ማምጣት ተችሏል ሲሉ የባለስልጣኑ የኦፕሬሽንና ጥገና ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ እንከንየለሽ አለሙ ገልፀዋል፡፡
ይህን የገለፁት በክፍለ ከተማው የተከናወኑ የመንገድ መብራት ስራዎችን አስመልክቶ የመስክ ምልከታና የማጠቃለያ ሪፖርት ለባለድርሻ አካላት ባቀረቡበት መድረክ ላይ ነው፡፡
በዚህም ባለስልጣኑ ባለፉት ወራት ከዋሺንግተን አደባባይ - ቡልጋሪያ፣ ከቄራ - ጎተራ፣ ከመስቀል አደባባይ-ጎተራ፣ ከቄራ - ጨርቆስ፣፣ ኢሴይ አከባቢ፣ ሰላም መንገድ፣ ከደንበል - ባንቢስ፣ ከለገሐር- ቂርቆስ፣ ከዋሺንግተን አደባባይ- መስቀል ፍላወር፣ ከመስቀል ፍላወር - ጎርጎሪዮስ- ሩዋንዳ፣ ለገሀር ታክሲ ተርሚናል፣ ጨርቆስ፣ በውስጥ ለውስጥና ሌሎችም መንገዶች ላይ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩ የመንገድ መብራቶች ላይ አስፈላጊውን የመንገድ መብራት ጥገና፣ ዝርጋታና ተከላ ስራዎችን በማከናወን ለህብረተሰቡ የምሽት እንቅስቃሴ ብሩህ፣ ምቹና ሰላማዊ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል፡፡
በተከናወነ የመንገድ ማብራት ስራ፤ ከተማችን አዲስ አበባ የቀን ብቻ ሳትሆን በምሽትም ሰፊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቅስቃሴዎችን የምትከውን በማድረግ ረገድ የጀመረችውን የለውጥ ጉዞ ማጠናከሩን አንስተዋል፡፡
የህብረተሰቡንም የምሽት እንቅስቃሴ ሰላማዊ፣ ጤናማና ምቹ ከማድረግ ባለፈ ጨለማን ተገን ተደርጎ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ከመከላከል አኳያ ለፀጥታ መዋቅሩ ምቹ ሁኔታን መፍጠር ማስቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
