es
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

Ir al canal en Telegram
1 474
Suscriptores
Sin datos24 horas
-37 días
-2130 días
Archivo de publicaciones
ሞዴል ብሎኮችን የመፍጠር ሥራችን ምቹ ከተማ ለመፍጠር መሠረት ነው!” በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች በተቀናጀ የብሎክ ልማት ንቅናቄ የለሙ ሞዴል ብሎኮች ተመረቁ፡፡ በክፍለ ከተማው ወረዳ 2፣ 4፣ 6፣ 7 እና 14 የሚገኙት ሞዴል ብሎኮች በተመረቁበት ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ባደረጉት ንግግር ከለውጡ ማግሥት በአዲስ አበባ ከተማ ከተከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ጽዱ፣ውብ እና ሰላማዊ የመኖሪያ አካባቢዎችን መፍጠር አንዱ መሆኑን አውስተው፣ በዚህ ተግባር የቦሌ ክፍ ከተማ በልዩ ልዩ ዘርፎች ባከናወነው እንቅስቃሴ ከቀዳሚዎቹ ክፍለ ከተሞች መካከል አንዱ ለመሆን መብቃቱን ገልጸዋል፡፡ የተቀናጀ የብሎክ ልማት ፕሮጀክት ነዋሪውን ኅብረተሰብ እና አደረጃጀቶችን በማስተባበር በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት የሚካሄድ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልጸው፣ “በቦሌ ክፍለ ከተማ የተከናወኑ የተቀናጀ ብሎክ ልማት ሥራዎች ኅብረተሰቡ በባለቤትነት መንፈስ ከአመራሩ ጋር ተቀናጅቶ በመሥራት ለውጤት እንዲበቁ ማድረጉ በአርአያነት የሚጠቀስና ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ በበኩላቸው በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ወደ ሌሎች ከተሞችና ክልሎችም በመስፋፋት ውብ፣ ምቹ እና ለጉብኝት ተመራጭ ሥፍራዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ አውስተው፣ ይህንን ተግባር ተከትሎ እስከ ብሎክ ድረስ የዘለቀ የተቀናጀ ልማት እንቅስቃሴም በከተማዋ ተመራጭና ምቹ ብሎኮችን ለመፍጠር ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ በተቀናጀ የብሎክ ልማት ፕሮጀክት ያስመዘገበው ስኬት የሚደነቅ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ የክፍለ ከተማው አስተዳደር ለፕሮጀክቱ መሳካት በቅንጅት በመሥራት ላሳየው ውጤታማነት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በክፍለ ከተማው የሚገኙ ሁሉንም ብሎኮች በሁሉም ዘርፍ ሞዴል ለማድረግ እየተሠራ እንደሚገኝ የገለጹት የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር እሸቱ ለማ፣ “ዛሬበመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የብሎክ ልማት ፕሮጀክት በእያንዳንዱ ወረዳ የተመረጡ አምስት ብሎኮች በድምሩ 55 ብሎኮችን አልምተን ስናስመርቅ ለክፍለ ከተማችንና ለከተማችን ገጽታ ተጨማሪ ግብዓት ከማድረግ ባሻገር በቀጣይ ለሚለሙ ብሎኮቻችን መነሳሳትን ለመፍጠር ያለው ሚና ከፍተኛ ነው” ብለዋል፡፡ Bole Communication- ቦሌ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager ህዳር 8/2018

የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርና መናበብ ከተማዋ ለምታደርገው የዘመናዊነት ጉዞ መሰረት ከመሆን ባሻገር መንግስትን ሀብት ከብክነት መታደግ መቻሉ ተገለፀ። #Ethiopia #AddisAbaba #linkAddis #AMN #media

በመዲናችን አዲስ አበባ የስማርት ሲቲ ግንባታ አካል የሆነው የስማርት መሠረተ ልማት ዝርጋታ በተቋማት ቅንጅት፣የአለምአቀፍ ተወዳዳሪነትና የጥራት ደረጃን ባሟላና ዘላቂነትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተከናወነ ነው ሲሉ በም/ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ አስገነዘቡ። ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ ይህን ያስገነዘቡት በዛሬው እለት የከተማ አስተዳደሩ 15 ተቋማትን ያካተተውን የመሠረተ ልማት ተቋማት ቅንጅት ያለፉት ሶስት ወራት የስራ አፈጻጸም በዛሬው እለት በተገመገመበት ወቅት ነው። ኢንጅነር ወንድሙ በዚሁ ወቅት በመዲናችን በአሁኑ ወቅት የስማርት መሠረተ ልማት አስተዳደራዊ ስርአትን መሠረት ባደረገ መልኩ አየተገነቡ ያሉ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች የከተማችን የእድገት ፍጥነት መሠረት ያደረገና ዛሬን ሳይሆን መጪውን ትውልድ ታሳቢ በማድረግ ለቀጣዮቹ 30 እና 40 አመታት እንዲያገለግል ሆኖ እየተገነባ ያለ ነው ብለዋል። አክለውም በከተ፣ማችን የመሠረተልማት ተቋማት በቅንጅት የመስራት ባህላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና እየተጠናከረ በመምጣቱ ከዚህ በፊት ተቋማቱ በተናጠልና ባልተናበበ መንገድ ሲገነቡ በነበረበት ወቅት ያጋጥም የነበረውን የህዝብ ሃብትና ንብረት ከብክነት መታደግ መቻሉንም አስገንዝበዋል። በመዲናችን በተለይም ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ የመሠረተ ልማት ተቋማት በቅንጅት መስራት በመቻላቸው እጅግ ዘመናዊ የሆነና የህብረተሰባችንን የላቀ የመሠረተ ልማት ፍላጎት መመለስ መቻሉን ኢንጅነር ወንድሙ አመልክተው እነዚህን የመንገድ፣ የውሃ፣ የመብራት፣የጎርፍ መከላከልና መሰል አገልግሎት የሚሰጡ መሠረተ ልማቶችን በዘላቂነት ህብረተሰቡ ሊንከባከባቸውና በአግባቡ ሊጠብቃቸው ይገባል ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሕይወት ሳሙኤል በበኩላቸው የሀብት ብክነትና የአገልግሎት መቆራረጥ ሳይኖር ሕዝባችንን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል በምንችልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተን ከስምምነት ላይ ደርሰናል ብለዋል፡፡ በአንደኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ የሥራ አፈጻጸም ምን ጥሩና ምን ክፍተቶች ነበሩ ብለን በጋራ ከለየን በኋላ በተለይ ወደኋላ የቀሩ የልማት ሥራዎቻችንን ለማፍጠን በጋራ በቅንጅትና በመናበብ መሥራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊና ጥልቅ ውይይት አድርገናል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡ የመሠረተ ልማት ቅንጅት ተቋማት የአዲስ አበባ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን፣ የውሃና ፍሳሽና የመንገዶች ባለስልጣን፣ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤቶች ልማት ቢሮ፣ የመብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣንን ጨምሮ 15 ተቋማትን ያካተተ ነው። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

Inistitiyuutiin Artifiishaal Intelejensii Itoophiyaa Waajjirasaa muummee bakka duraan turerraa jijiiruudhaan gara magaalaa gidduu, gamoo Korporeeshinii Broodkaastiingii Itoophiyaa diraaniitti jijjiireera. Waggaa tokko keessatti jijjiirama ijaarsaa ajaa'ibsiisaafi bakka hojii mijaawaa ta'e ogummaadhaan hojjettootasaaf uumuu danda'eera. Dhaabbatichi waggoota shan keessatti jireenya keenya saffisaan bocuu keessatti bakka artifiishaal intelejensiin qabu haala mul'isuufi akkaataa biyyi keenya dorgommii teknooloojii idil-addunyaa kana keessatti dammaqinaan hirmaachuu dandeessu mirkaneessuun bakka olaanaarra gaheera. Inistitiyuutich gama fayyaa, qonna, damee tajaajilaatiin gumaacha hooggantummaa bahaa kan jiru yoo ta'u, gama kilaawud kompiitiingi, gama kuusaawwan odeeffannoo gurguddoo, barbaacha odeeffannoo, roobootiksiifi teknooloojiiwwan immersiivitiin humnasaa gabbifataa jira. Giddugalli istaarti aappii artifiishaal intelejeensii dhiyeenyatti eegalamemmoo haala kana caalaatti ni cimsa. Lammiileen yaada duwwaa qabatanii dhufuudhaan prootootaayippii uumuuf, baay'isuuf, darbees invastaroota damee dhuunfaa waliin akka walargan carraa ni mijeessa. Hamma yoonaatti amoonni yaada uuman 200 carraa kanatt fayyadamaniiru. The Artificial Intelligence Institute, having relocated from its former site, is now housed in the former Ethiopian Broadcasting Corporation premises in the heart of the city. The complex AII moved into has undergone an extraordinary infrastructural transformation in less than a year, resulting in an ergonomically advanced and highly conducive work environment for its employees. In just five years, the Institute has reached remarkable heights, reflecting the rapid pace at which AI is shaping every aspect of our lives, and underscoring the importance of ensuring that our nation actively participates in this global technological race. The Institute is driving AI interventions across health, agriculture, and the service sector, while also developing capabilities in cloud computing, large-scale data centers, data mining, robotics, and immersive technologies. A newly launched AI startup center further strengthens this ecosystem, enabling individuals to enter with only an idea and receive support to prototype, incubate, and connect with private-sector investors; already, 200 innovators have benefited from this opportunity

የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና መስሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል። ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል። Inistitiyuutiin Artifiishaal Intelejensii Itoophiyaa Waajjirasaa muummee bakka duraan turerraa jijiiruudhaan gara magaalaa gidduu, gamoo Korporeeshinii Broodkaastiingii Itoophiyaa diraaniitti jijjiireera. Waggaa tokko keessatti jijjiirama ijaarsaa ajaa'ibsiisaafi bakka hojii mijaawaa ta'e ogummaadhaan hojjettootasaaf uumuu danda'eera. Dhaabbatichi waggoota shan keessatti jireenya keenya saffisaan bocuu keessatti bakka artifiishaal intelejensiin qabu haala mul'isuufi akkaataa biyyi keenya dorgommii teknooloojii idil-addunyaa kana keessatti dammaqinaan hirmaachuu dandeessu mirkaneessuun bakka olaanaarra gaheera. Inistitiyuutich gama fayyaa, qonna, damee tajaajilaatiin gumaacha hooggantummaa bahaa kan jiru yoo ta'u, gama kilaawud kompiitiingi, gama kuusaawwan odeeffannoo gurguddoo, barbaacha odeeffannoo, roobootiksiifi teknooloojiiwwan immersiivitiin humnasaa gabbifataa jira. Giddugalli istaarti aappii artifiishaal intelejeensii dhiyeenyatti eegalamemmoo haala kana caalaatti ni cimsa. Lammiileen yaada duwwaa qabatanii dhufuudhaan prootootaayippii uumuuf, baay'isuuf, darbees invastaroota damee dhuunfaa waliin akka walargan carraa ni mijeessa. Hamma yoonaatti amoonni yaada uuman 200 carraa kanatt fayyadamaniiru. The Artificial Intelligence Institute, having relocated from its former site, is now housed in the former Ethiopian Broadcasting Corporation premises in the heart of the city. The complex AII moved into has undergone an extraordinary infrastructural transformation in less than a year, resulting in an ergonomically advanced and highly conducive work environment for its employees. In just five years, the Institute has reached remarkable heights, reflecting the rapid pace at which AI is shaping every aspect of our lives, and underscoring the importance of ensuring that our nation actively participates in this global technological race. The Institute is driving AI interventions across health, agriculture, and the service sector, while also developing capabilities in cloud computing, large-scale data centers, data mining, robotics, and immersive technologies. A newly launched AI startup center further strengthens this ecosystem, enabling individuals to enter with only an idea and receive support to prototype, incubate, and connect with private-sector investors; already, 200 innovators have benefited from this opportunityየኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና መስሪያ ቤቱን ቀድሞ ከነበረበት በመለወጥ መሃል ከተማ ወደ ቀድሞው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሕንፃ አዛውሯል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የግንባታ ለውጥ እና ዘመናዊ የመሥሪያ ሥፍራ ጥበብን በማሳየት ለሠራተኞቹ እጅግ ምቹ የሆነ ስፍራንም መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሕይወታችንን በፍጥነት በመቅረጽ ውስጥ ያለውን ስፍራ በሚያንፀባርቅ እና ሀገራችንም በዚህ አለምአቀፍ የቴክኖሎጂ ውድድር በንቁነት መሳተፏን በሚያረጋግጥ መንገድ ከፍታ ላይ ደርሷል። ኢንስቲቲዩቱ በጤና፣ በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እያደረገ ያለው የመሪነት አስተዋፅኦውን እየተወጣ ሲሆን በክላውድ ኮምፒውቲንግ፣ ትላልቅ የመረጃ ቋቶች፣ የመረጃ ፍለጋ፣ ሮቦቲክስ እና ኢመርሲቭ ቴክኖሎጂዎች አቅሙን በማጎልበት ላይ ይገኛል። በቅርቡ የተጀመረው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ስታርት አፕ መዐከል ደግሞ ይኽንን ከባቢ የበለጠ ያጠናክረዋል። ዜጎች ሀሳብ ብቻ ይዘው በመምጣት ፕሮቶታይፕ ለመፍጠር፣ ለማባዛት ብሎም ከግሉ ዘርፍ ኢንቬስተሮች ጋር እንዲገናኙ እድል ያመቻቻል። እስከ አሁን 200 ሀሳብ ፈጣሪዎች በዚህ እድል ተጠቅመዋል።

"ህዳር ሲታጠን በሽታ አይጠፋም!… See more

እያንዳንዱ የፅዳት እርምጃችን ለከተማችን ፅዳት ብቻ ሳይሆን ለጤናችንም ዋስትና ነው! ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የዘንድሮው "ህዳር ሲፀዳ" ከተማአቀፍ የጽዳት ንቅናቄ ይፋዊ ማስጀመሪያ መረሐግብር በምስል ሲቃኝ:-… See more

የኮሪደር ልማቱ ትሩፋቶች የሆኑት የንግድ ቤቶች እና ፕላዛዎች ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና የዲፕሎማቶች መነሃርያ እንደመሆንዋ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ ውብ ፅዱና ማራኪ እንዲሁም የቱሪዝም መናገሻና ተወዳዳሪ ለማድረግ ደረጃዋን የጠበቀች ውብ ከተማ በመገንባት ሂደት በኮሪደር ልማት በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል :: የኮሪደር ልማቱም ካስገኛቸው ትሩፋቶች መካከል የንግድ ቤቶች እና ፕላዛዎች በዋናነት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በዚህ በኮሪደር ልማቱ ብቻ 5200 የንግድ ሱቆች እና ፕላዛዎች ተገንብተዋል ፡፡ ከነዚህም ውስጥ 4972 ለተጠቃሚዎች ተላልፈው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ:: የተሟላ ብልጽግናን ለማረጋገጥና ከከተሜነት እድገት ጋር የተሳሰረው የኮሪደር ልማት ያስገኛቸው እነዚህ ንግድ ቤቶች እና ፕላዛዎች ከዚህ ቀደም ለመገልገልም ሆነ ለእይታ ምቹ ያልነበሩ ንግድ ቤቶች ተነስተው በምትካቸው የአካባቢውን ውበት በቀየሩ እና እይታን በሚስቡ ዘመናዊ ሱቆች እና ፕላዛዎች በመተካታቸው ለከተማዋ ተጨማሪ ድምቀት ከመሆን ባለፈ በዋናነት የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው:: እነዚህ የንግድ ሱቆቹ የከተማዋን ኢኮኖሚ በማነቃቃት ፤ የኑሮ ውድነትን በመቅነስ እና ገበያውን በማረጋጋት ረገድም የጎላ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡ ቀሪዎቹ 228 ሱቆችም በቀጣይ ጥቂት ቀናት ወደ ስራ የሚገቡ ይሆናል፡፡ ለከተማችን እድገትና ለህዝባችን ተጠቃሚነት እንተጋለን!!!

ፅዱና ምቹ የመኖሪያ አካባቢን መፈጠር የከተሜነት መገለጫ ከሚባሉ መለኪያዎች ውስጥ አንዱ በመሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች የመኖሪ አካባቢያቸውን ፅዱና ጤናማ የማድረግ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ አሳሰቡ፡፡ #Ethiopia #AddisAbaba #linkAddis #AMN #media