es
Feedback
ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር

ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር

Ir al canal en Telegram

ኦ አሐውየ እለ አፈቅረክሙ ጸልዩ ዲበ ድካምየ ከመ ይዕቀበኒ እግዚእ በዐቢይ ሣህሉ በሃይማኖት ርትዕት እስከ ፍጽሜ ደሓሪት እስትንፋስ። ወዝንቱ ውእቱ ባሕቲቱ ተስፋየ። ወስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ለዓለመ ዓለም አሜን። ሃይ. አበ. ዘቴዎዶስ. ፹፫፡፵፬ https://t.me/joinchat/SWWiqKcuci79Brh9

Mostrar más
2 137
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+2830 días
Archivo de publicaciones
ነገረ ትንሣኤ.pdf9.18 KB

"ኢየሱስ ክርስቶስ የይሁዳ እግርን ጨምሮ የሁሉም ደቀ መዛሙርቱ እግሮችን ካጠበ በኋላ የደቀ መዛሙርቱን እግሮች ባጠበበት ውኃ የራሱን እግሮች በራሱ እጅ ዐጥቧል።" "ኦ ትሕትና ዘመጠነ ዝ ትሕትና"

ዛሬ በዓለ እግዚአብሔር ነው። ዕለቱም የሕማማት ሁለተኛ ቀን ማክሰኞ ነው። ለእግዚአብሔር የሚገባውን የአምልኮ ስግደታችሁን ስገዱ!

Repost from N/a
ሆሣዕና.pdf4.47 KB

ሆሣዕና.pdf4.47 KB

ዛሬ መጋቢት ፳፫/፳፻፲፰ ዓ/ም በመጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ የተዘረፈ ሙሉ ቤት ቅኔ👇 ፩. ግእዝ ጉባኤ ቃና • ዘሥራይ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ አሕመሞ፥ • በሌሊት መንፈስ እስመ ይትረአዮ ቀዊሞ። ፪. ዕዝል ጉባኤ ቃና • ለእመ ኒቆዲሞስ አብ ምንትኑ ለኒቆዲሞስ ሕይወቱ፥ • እንዘ ወይነ ትምህርት ይሰቲ አምስዮ እስመ በሌሊት የአቱ። ፫. ዘአምላኪየ • ከመ መሐድምት ዘይብል ውስተ ባህለ አበው አእላፍ፥ • በሞጸፍ አሓዱ ክልኤቲ አዕዋፍ፥ • ቦ አዕዋፍ ክልኤቲ በኒቆዲሞስ ሞጸፍ። ፬. ሚ በዝሑ • ለዘእምኔከ ርሕቁ ትጸልኦሙ ለምንት ወትትቃወሞሙ ለምንትኑ፥ • ኒቆዲ ልብከ ዘክፉል በበ ዘመኑ፥ • አምጣነ ይቤ መጽሐፍ ጕየይ እኍ እምነ ዘክልኤ ልሳኑ። (አረ. መን. ፍና. ፲፰) ፭. ዋይ ዜማ • ጕይ ኒቆዲሞስ እስመ ዐማኑኤል ዘንም እስመ ኒቆዲሞስ ጕንድ፥ • መጽአ ስቡረ ኵለንታ ዐማኑኤል ዑድ፥ • አመ ከርመ ወንጌል ኮነ በቀመረ እሉ አይሁድ፥ • አመ መብረቀ ጽድቅ በረቀ ምስለ ነጐድጎድ፥ • ሃይማኖት ዘጴጥሮስ ሞገድ። ፮. ሐፂር ዋይ ዜማ • ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስሀ ዐማኑኤል ዑቅ፥ • ዐማኑኤልሀ ተወከፍ ከመ ዘተገድፈ ደ። • (ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስሀ ዐማኑኤል ዑቅ።) ፯. መስኮት ዋይ ዜማ • ዐማኑኤል በመትከፍትከ ኒቆዲሞስሀ ዘወድቀ እመልዕልተ ኦሪት ምርፋቅ፥ • ሱቅ፦ ወእንከ ኄሩ ወእንከ ሊቅ፥ • ወዲቤሁ ለፀርከ ደቅ። ፰. ሥላሴ • ኒቆዲሞስ ለኢየሱስ ወለኒቆዲሞስ ኢየሱስ እንተ ኒቆዲሞስ ቀርበ ወእንተ ኢየሱስ ኢርሕቀ፥ • እመ ኮነ ወለእመ ኮነ መርድአ ወሊቀ፥ • እመንበረ ኦሪት ተትሕተ ወዲበ ርእሰ ሕግ ረፈቀ፥ • እስመ ኢጠየቀ ወጠየቀ፥ • እንተ ኢየሱስ ጠየቀ ወጽሑቀ ጽሕቀ፥ • ወዘዝክቱ ኒቆዲሞስ ዖቀ። ፱. ዘይእዜ • መራር ብእሲት ቃለ ወንጌል ዘለመደት ጸብአ ወአሠነየት ሁከተ፥ • ምስለ ኒቆዲሞስ ብእሲሃ ሌሊተ ተንሢኣ ትትበአስ ሌሊተ፥ • ወበቃለ ወንጌል ብእሲት ሰላመ ወዕረፍተ፥ • ኒቆዲሞስ ኀጥአ እስከ አመ ሞተ፥ • ቃለ ሕገ ወንጌል ብእሲቱ አምጣነ ኢኮነት ኄርተ። • (ኒቆዲሞስ ኀጥአ እስከ አመ ሞተ፥) ፲. ሣህልከ • እመኒ ኢዘንመ ውስተ ሀገር፥ • ዝናመ ምሕረት ሰላም ምሉአ በረከት ቍር፥ • ሳዐ ክረምተ ጽልእ ድሕረ ተዘርአ መጽለወ እስከ አመ የብሰ ልበ ሰብእ ማዕረር። ፲፩. ሐፂር ሣህልከ • ነዊሕ ኦም ኒቆዲሞስ፥ • ለኀበ ክልኤ ተሰብረ በትምህርተ ወንጌል ነፋስ። • (ነዊሕ ኦም ኒቆዲሞስ፥) ፲፪. መወድስ • ሱባዔ ሀብተ ጽድቅ ፀሓይ እምድሕረ ሠረቀ እስመ እመጠኑ ፈድፈደ ሐሩረ ቃለ ጽድቅ ዘበድካም፥ • እለ ውስተ ገዳም ሀለዉ ለተግባረ ኵሉ ዓለም፥ • ግብረ እደዊሆሙ ሐዲጎሙ አጽለሉ ኀበ ዘለምለመ ጾመ ወልድ ኦም፥ • ምጽላለ ሕይወት እስመ ኮኖሙ ውእቱ ኦም ዘወልደ አምላክ ጾም። • ሶበሂ ተፈጸመ ሰዓተ ቅዳሴ ግሩም፥ • ለጸናጽለ ወርቅ ወከበሮ መሀይምናኒሁ ለበለዓም፥ • በብሂለ ስብሐት ዘጸግበ ላእከ ደብረ ሲና ምቅዋም፥ • አብሖሙ እንዘ ይብል እትዉ በሰላም። ፲፫. ኵልክሙ መወድስ • ኦ ዕሙቅ ብዕለ ስብሐቲሁ ለፈጣሬ ኵሉ ፍጡር እንተ ቅድምናሁ ምስለ ተድሕሮ፥ • እመ ለፀሓይ ጴጥሮስ አመ ጎሐ ጽባሕ ገብሮ፥ • አምጣነ ለወርሕ ኒቆዲሞስ ከመ ያብርህ ሰዓተ ሌሊት በሌሊት ፈጠሮ፥ • ወሌሊተ አኰነኖ እመ በሰማያት ይቁም አስተዳለወ መንበሮ። • መኑሂ ዘየኀሥሥ ምክረ ልበ ሰብእ ይምክሮ፥ • ወመኑ ዘይፈቅድ በተጥባበ ነገር ከመ ያእምሮ፥ • ከመ ልማደ ሰብእ ኢንርሳዕ በህላዌሁ አንክሮ፥ • ለሊሁ እስመ ረሰየ ጽልመተ ምስዋሮ፥ • መኑሂ ኢይኅሥሥ ለህላዌሁ ዐሠሮ። • (ለሊሁ እስመ ረሰየ ጽልመተ ምስዋሮ፥) ፲፬. ሐፂር ኵልክሙ መወድስ • ከመ ነሥአ ዝስኰ ጸብሐ ሕገ ኦሪት ቀሊል፥ • ተሰብረ ለኀበ ክልኤቱ ኒቆዲሞስ ጻሕል። ፲፭. ሐዋርያቲሁ ከበበ • ኅብስተ ሕይወት ወልድ፥ • ዘበዕፀ መስቀል ማእድ፥ • ውሑደ ኮነ ኀበ አይሁድ እንዘ ለካልኣን ፍድፉድ። ፲፮. ሕንጼሃ • አእምሮ ዘኒቆዲሞስ ዳሕንኑ፥ • መንፈቀ ሌሊት ይጐይይ አኮኑ።

ዛሬ ማታ በዚህ https://t.me/kineyared የቅኔ ዘረፋ ይኖረናል። ሰዓት 2:30

ደብረ ዘይት.pdf4.51 KB

ክርስቶስ ዳግም ስለ መምጣቱ የተናገራቸው ፲፬ ምልክቶች ሰፊ ጊዜ ሰጥተው ሊያነቡት የሚገባ አስተማሪ ጽሑፍ ከላይ ያለውን Pdf አንድ ጊዜ ጠቅ አድርገው ከፍተው ያንብቡ!

...የቀጠለ ክፍል ፬ “ደዌ ዘለግሕደተ ክብረ እግዚአብሔር” “ደዌ ዘለግሕደተ ክብረ እግዚአብሔር” ከኃጢአት ጋር የሚያያይዝ አንድም ምክንያት የሌለው ሲሆን እግዚአብሔር ክብርን ሲሻና የአምላክነቱን ሥራ በመግለጥ በራሱ፣ አልያም በቅዱሳን/ት አማካኝነት የማዳኑን ሥራ ለማሳየት ሲፈልግ ብቻ አልፎ አልፎ የሚከሠት በሽታ ነው። የበሽታውም ዓይነት በተለያየ መልኩ ሊከሠት የሚችልና የየራሱ የሆነ የሕመም ስሜት ያለው  ሲሆን ለሞት ሊዳርግም ላይዳርግም የሚችል በሽታ ነው። “ደዌ ዘለግሕደተ ክብረ እግዚአብሔር” ማለትም ቀጥታ ዐማርኛዊ ፍቺው ‹‹ለእግዚአብሔር ክብር መገለጥ የሚሆን በሽታ›› ማለት ነው። የዚህ በሽታ ክሥተትንም ከቅዱስ መጽሐፍ እንደሚከተለው በጥልቀት እንመለከታለን፦ ፩. #አልዓዛርን እስከ ሞት ድረስ ያደረሰ በሽታ፦ “የማርያምና የእኅቷ ማርታ መንደር በሚሆን በቢታንያ ስሙ አልዓዛር የሚባል የታመመ አንድ ሰው ነበር። . . . እኅቶቹም ‹‹ጌታችን ሆይ! እነሆ የምትወደው ታሟል›› ብለው ወደ ጌታችን ኢየሱስ ላኩ። ጌታችን ኢየሱስም ሰምቶ እንዲህ አለ፦ ‹‹ይህ ደዌ በእርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም›› . . . ጌታችን ኢየሱስም ወደ ቢታንያ ሄደ፤ ከዚያም በደረሰ ጊዜ ከተቀበረ አራት ቀን ሆኖት አገኘው። . . . ይህንም ብሎ በታላቅ ቃል ጮኸና ‹‹አልዓዛር አልዓዛር ና! ወደ ውጭ ውጣ!›› አለ . . . ሞቶ የነበረውም እንደ ተገነዘ እጁና እግሩንም እንደ ታሰረ፥ ፊቱም በሰበን እንደ ተጠቀለለ ወጣ፤ ጌታችን ኢየሱስም እንግዲህስ ‹‹ፍቱትና ተዉት ይሂድ!›› አላቸው።" ዮሐ. 11፡1-44። ፪. #ዕውር ሆኖ የተወለደው ሰው፦ “ከዚያም ሲያልፍም ዕውር ሆኖ የተወለደውን ሰው አየ። ደቀ መዛሙርቱም ‹‹መምህር ሆይ! ይህ ሰው ዕውር ሆኖ የተወለደው በማን ኀጢአት ነው? በራሱ ነውን? ወይስ በወላጆቹ?›› ብለው ጠየቁት። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ ‹‹የእግዚአብሔር ሥራ ሊገለጥበት ነው እንጂ እርሱ አልበደለም፤ ወላጆቹም አልበደሉም።” ዮሐ. 9፡1-3። ፫. #የስራጵታይቱ ሴት ወንድ ልጇን ለሞት ያበቃው ከባድ በሽታ፦ "እርሷም ኤልያስን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ! ከአንተ ጋር ምን አለኝ? ኃጢአቴንስ ታሳስብ ዘንድ፥ ልጄንስ ትገድል ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን? አለችው . . . እግዚአብሔርም የኤልያስን ቃል ሰማ፤ የብላቴናው ነፍስ ወደ እርሱ ተመለሰች፤ እርሱም ዳነ።" 1ኛ ነገ. 17፡17-24። ፬. #የሱናማዊቷ ሴት ወንድ ልጇን ለሞት ያበቃው የራስ ምታት በሽታ፦ “አባቱንም ‹‹ራሴን ራሴን›› አለው። እርሱም ሎሌውን ተሸክመህ ወደ እናቱ ውሰደው አለው። አንሥቶም ወደ እናቱ ወሰደው፤ በጕልበቷም ላይ እስከ ቀትር ድረስ ተቀመጠ፥ ሞተም . . . ኤልሳዕም ወደ ቤት በገባ ጊዜ እነሆ፥ ሕፃኑ ሞቶ በአልጋው ላይ ተጋድሞ ነበር። ኤልሣዕም ወደ ቤት ገብቶ በሩን በሁለቱ ላይ ዘጋ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጸለየ። መጥቶም በሕፃኑ ላይ ተኛ፤ አፉንም በአፉ፥ ዐይኖቹንም በዐይኖቹ፥ እጆቹንም በእጆቹ ላይ አድርጎ ተጋደመበት፤ የሕፃኑም ሰውነት ሞቀ። ተመልሶም በቤቱ ውስጥ አንድ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተመላለሰ፤ ደግሞም ወጥቶ ሰባት ጊዜ በሕፃኑ ላይ ተጋደመ፤ ከዚያም በኋላ ሕፃኑ ዐይኖቹን ከፈተ . . .” 2ኛ ነገ. 4፡17-37። ፭. #ዶርቃስ የተባለችውን ደግ ሴት ለሞት ያበቃ በሽታ፦ “በኢዮጴም ሀገር ‹‹ጣቢታ›› የሚሏት አንዲት ደቀ መዝሙር ነበረች፤ በትርጓሜውም ‹‹ዶርቃስ›› ይሏታል፤ ፌቆ ማለት ነው፤ እርሷም ብዙ ደጋግ ሥራ ትሠራ ነበር፤ ምጽዋትም ትሰጥ ነበር፤ ያን ጊዜም ታማ ሞተችና በድኗን አጥበው በሰገነት አስተኟት . . . ጴጥሮስም ሁሉን ካስወጣ በኋላ ተንበርክኮ ጸለየ፥ ወደ በድኗም መለስ ብሎ ‹‹ጣቢታ ሆይ! ተነሽ!›› አላት። እርሷም ዐይኖቿን ገለጠች። ያን ጊዜም ጴጥሮስን ዐየችው። ቀና ብላም ተቀመጠች። እጁንም ለእርሷ ሰጥቶ አስነሣት፤ ቅዱሳንንና ባልቴቶችንም ጠርቶ እርሷን አድኖ ሰጣቸው።” ሐዋ. 9፡36-37። ፮. #ልምሾ ሆኖ የተወለደው ሰው፦ “ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ እግሩ ሽባ ሆኖ የተወለደ አንድ ሰው ነበረ፤ ወደ መቅደስም ከሚገቡት ምጽዋት ይለምን ዘንድ፥ ሁልጊዜ እየ ተሸከሙ መልካም በሚሏት በመቅደስ ደጃፍ ያስቀምጡት ነበር . . . ጴጥሮስም ከዮሐንስ ጋር ትኵር ብሎ ተመለከተውና ‹‹ወደ እኛ ተመልከት!›› አለው፤ ወደ እነርሱም ተመለከተ፤ . . . በቀኝ እጁ ይዞም አስነሣው፤ ያን ጊዜም እግሩና ቍርጭምጭምቱ ጸና ፤ ዘሎም ቆመ ፤ እየ ሮጠና እየ ተራመደም ሄደ። እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ከእነርሱ ጋር ወደ መቅደስ ገባ።” ሐዋ. 3፡1-10። ይህ በሽታ ከላይ ባየነው መሠረት እግዚአብሔር ክብሩን ለመግለጽ እስከ ፈለገበት ቀን ብቻ የሚቈይ በሽታ ሆኖ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ የሚወገድ በሽታ ነው። ለሞት ቢያበቃም ከሞት በኋላ ተመልሶ በአካለ ሥጋ መዳን የሚቻልበት መንገድ አለው። ስለ ሆነም  ወደ ፊት ጊዜው ባልታወቀ የሚፈወሱበት ዕለት እንዳለ በመገንዘብ እግዚአብሔር የማዳን ሥራውን በመሥራት ድንቅ ተአምር በርስዎ ሕይወት እስከሚገልጥበት ዕለት ድረስ ተስፋ ባለመቍረጥ በሕገጋተ እግዚአብሔር ተጠብቆ መቈየት ግድ ይላል።

…የቀጠለ ክፍል ፫. #ደዌ_ዘንጽሕ ይህ በሽታ ቅዱሳን/ት ከመንፈሳዊ ተጋድሏቸው፣ ከጾማቸውና ከዘወትር ጸሎታቸው ብዛት የተነሣ የሚመጣ በሽታ ሲሆን የሕመሙ ስሜት እንደ በሽታው ዓይነት ሊለያይ ይችላል። ይህ በሽታ ቅዱሳን/ት መንፈሳዊ ተጋድሏቸውን ከጀመሩበት ዕለት ማግሥት ጀምሮ በመዋዕለ ተጋድሏቸው ሁሉ አብሯቸው ሊጓዝ ይችላል። በዚህም በሽታ ያለፉ ቅዱሳን አባቶቻችንን እንመለከታለን፦ ፩. ቅዱስ #ጢሞቴዎስ፦ “ወኢትስተይ ማየ ዕራቆ ኅዳጠ ወይነ ቶስሕ በእንተ ሕማመ ከብድከ ወበእንተ ደዌከ ዘዘልፍ - ስለ ሆድህ በሽታና ስለ ዘወትር ደዌህ ጥቂት ወይን ጨምር እንጂ ውኃ ብቻ አትጠጣ።” ፩ ጢሞ. ፭፡፳፫። ፪. ቅዱስ #ያዕቆብ፦ “ከአራቱ የጠራቢው ዮሴፍ ልጆች መካከል የመጨረሻው ልጅ የሆነ፥ የጌታ ወንድም ተብሎ የሚጠራው፥ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ ሆኖ የተሾመው ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ በጾምና በጸሎት ተወስኖ አብዝቶ ከመቆሙ የተነሣ ከዚህ ዓለም በአካለ ሥጋ በሞት እስኪለይ ድረስ እግሮቹ #ዐብጠው እጅግ ይታመም ነበር። አዘውትሮም ይሰግድ ስለ ነበረ ግንባሩ የግመል ጕልበት ይመስል ነበር። ገድለ ሐዋርያት፤ ድርሳነ ዮሐንስ አፈ ወርቅ። ፫. #ቅዱሳን_ባሕታውያን፦ “…ወዔሉ በሠቅ ወበሐሜለት ወበዘብድወ ጠሊ፤ ተጸነሱ፤ ተመንደቡ፤ #ሐሙ፤ ርኅቡ፤ ጸምኡ። እሉ እሙንቱ ዘኢይደልዎሙ ዓለም፤ ወዔሉ ውስተ ገዳም፤ ወውስተ አድባር ወበዓታት ወግበበ ምድር = ማቅን ለብሰው፣ መጠምጠሚያቸውን ጠምጥመው፣ የፍየልን ሌጦ ለብሰው ተቸገሩ፤ #ታመሙ፤ ተራቡ፤ ተጠሙ፤ ዓለም ያልተገባቸው እነዚህ ናቸው። በየዱሩ፣ በየተራራዎችም፣ በየዋሻዎችም በየምድር ፍርኩታ ዞሩ”። ዕብ. 11፡36-38። ሲል ቅዱስ ጳውሎስ የመሰከረላቸው በየገዳሙ ስለ ጽድቅ ብለው በፈቃዳቸው የሚታመሙ አባቶቻችንና እናቶቻችን ጥቂት የሚባሉ አይደሉም። በመሆኑም ደዌ የነበረባቸውን ብዙዎቹን ሰዎች በልብሱ ቍራጭ ሲያድን የነበረው ቅዱስ ጳውሎስ በሆድ ሕመም ይሠቃይ ለነበረው ደቀ መዝሙሩ ጢሞቴዎስ የላከለት የልብሱን ቍራጭ ሳይሆን “በሌሎችም ኃጢአት አትተባበር፤ ራስህን በንጽሕና ጠብቅ፤ ስለ ሆድህና ስለ #በሽታህ ብዛት ጥቂት የወይን ጠጅ ጠጣ እንጂ፥ ወደ ፊት ውኃ ብቻ አትጠጣ።” በማለት ጊዜያዊ መፍትሔ ሊሆን የሚችልን ምክር ነበር የነገረው። 1ኛ ጢሞ. 5፡22-23 ፡፡ ስለ ሆነም ይሄ በሽታ ከጠነከረ መንፈሳዊ ተጋድሎ ሊመጣ የሚችል እንደ መሆኑ መጠን ጽድቅን በማይጋፋ መልኩ ጊዜያዊ መፍትሔዎችን መጠቀሙ አይከፋም። ፬. #ደዌ_ዘዕሴት “ደዌ ዘዕሴት” በመጀመሪያ በነበረው በጎ ስጦታ ላይ ዕጥፍ ድርብ በጎ ዋጋን የሚያሰጥና በክብር ላይ የክብር መጐናጸፊያን የሚያጐናጽፍ በሽታ ነው። ይህም በሽታ ከሰዎች ኃጢአት፣ ከበደልም ሆነ ከጥፋት ሁሉ የሚያያዝ የኃጢአት ውጤት አይደለም። ይህ በሽታ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሊሽርም ይችላል። እስከ ወዲያኛው እስከ ሥጋዊ ሞትም ዐብሮ ሊቈይ ይችላል። የበሽታውም ስሜት “የተወሰነ ከፊል የሰውነት ክፍል፣ አሊያም ሙሉ የሰውነት ክፍል ቍስል፣ ዕብጠትና ወዘተርፈ… የውስጥም የውጭም የሕዋስን ክፍል የሚያጠቃ በሽታ ሊሆን ይችላል። ይህንም በሽታ ተቋቍመው ያለፉ ሰዎችን እንደ ምሳሌ እንመልከት፦ ፩. #ኢዮብ፦ “ሰይጣንም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ፥ ኢዮብንም ከእግሩ ጫማ ጀምሮ እስከ አናቱ ድረስ #በክፉ-ቍስል መታው።” ኢዮ. 2፡7። ኢዮብ የታመመው አምላኩ እግዚአብርሔርን በድሎ፥ ኃጢአት ሠርቶ ሳይሆን ሰይጣን ባቀረበው ፈተና ነበር። ኢዮብም በበሽታው ጽናት ዘመድ፥ አዝማድ፣ የቅርብ ወገን፣ ጎረቤት ተለይተውት ከራሱ ጸጕር እስከ እግሩ ጥፍር ድረስ መላ ሰውነቱ ሁሉ ቈስሎ ተልቶ፥ እየ ተቈራረጠ በዐመድ ላይ ተኝቶ ራሱ ታማሚ፥ ራሱ አስታማሚ ሆኖ ለዘመናት የእግዚአብሔርን ምሕረት ደጅ ይጠና ነበር። ደግሞም የዓሥሩ ልጆቹ መሞትና የቤቱ ንብረት ሁሉ ውድመት ለኢዮብ ሌላኛው ሕመሙ ነበረ። ነገር ግን ኢዮብ ይህን ሁሉ ፈተና በትዕግሥት ተሸክሞ እግዚአብሔርን አጥብቆ ከመለመን በቀር በእግዚአብሔር ላይ በክፉ አፉን እንኳን አልከፈተም። ለብዙ ዘመናት ደጅ ከጸና በኋላም እግዚአብሔርም ደረሰለት፤ ፈወሰውም። በተጨመረለት ዕድሜም በሞቱት ልጆቹ ልክ ዓሥር ልጆችን እንዲወልድ አደረገው፤ ከቀድሞውም ሀብቱ ይልቅ ሁለት ዕጥፍ አድርጎ ሀብት ሰጠው። ከድኅነቱ በኋላም ኢዮብ ይባል የነበረው ስሙ ኢዮባብ ተብሏል፡፡ ኢዮ. 1፡1-22፣ 2፡1-9፤ 42፡10-17፤ ተግ. ዘዮሐ. አፈ. ወር. ፳። ፪. #አልዓዛር፦  ይህ አልዓዛር የተባለው ሰው ምንም የሌለው ምስኪን ድሃ ሰው ነበረ፥ የበሽታውም ዓይነት ልክ እንደ ኢዮብ የቍስል ደዌ ነበረ። አልዓዛርም በሕመሙ ጊዜ ጧሪ፥ አስታማሚ ስላልነበረው ነዌ በተባለ ንፉግ ባለጠጋ ቤት ጥግ ሆኖ ፍርፋሪን ለመብላት ይመኝ ነበር። ውሾችም የደረቀውን ቍስሉን እየላሱ ሲያስታምሙት ንፉጉ ባለጠጋ ነዌ ግን ከማዕዱ የሚወድቀውን ፍርፋሪውን እንኳን አልሰጠውም። አልዓዛርም በሥጋ ከሚሠቃይበት #በሽታው በተጨማሪ ረኃብ ተደራርቦበት በበሽታው የሕመም ስሜትና በረኃብ ምክያት ከዚህ ዓለም በአካለ ሥጋ በሞት ተለይቷል። ሆኖም ግን ይህ የእግዚአብሔር ሰው አልዓዛር በዚሁ ከባድ ቍስል ተይዞ፥ በዚያውም ላይ የሥጋ ረኃብ ተደራርቦበት በአካለ ሥጋ እስኪሞት ድረስ እግዚአብሔርን ከማመስገን አንደበቱን አልገታም። ሉቃ. 16፡19-31። በልዩ ልዩ የበሽታ ሕመም/ሥቃይ ውስጥ ያላችሁ ወገኖች ሆይ! በልዩ ልዩ በሽታ ምክንያት የምትታመሙት መታመም እግዚአብሔር  የትዕግሥታችሁን ውጤት አይቶ በኋላ ላይ ዕጥፍ ድርብ የሆነ፥ በሕመማችሁ ጊዜ የመታገሣችሁን ዋጋ ሊሰጣችሁ ዐስቦ የኢዮብ በሽታ ዓይነት በሽታ እንደ ሆነ ማን ያውቃል? በመሆኑም በተለያዩ የበሽታ ዓይነቶች በምንታመምበት ጊዜ እንደ ኢዮብ ኢዮባውያን ሆነን በትዕግሥት የእግዚአብሔርን የምሕረት እጅ ደጅ መጽናት እንጂ ክፉ ቃልን ማሰማትና ማማረር ተገቢ አይደለም። ማማረርም ከማማረር አልፎ ይበልጥ ራስን ከመጕዳት በቀር የሚያመጣው ለውጥ የለም። ይልቁንም “ወንድሞች ሆይ! የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታም ስም የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ፤ እነሆ የታገሡትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ የኢዮብን ትዕግሥት ሰምታችኋል፤ እግዚአብሔርም የፈጸመለትን አይታችኋል፤ የእግዚአብሔር ቸርነቱ ብዙ ነውና፤ ይቅር ባይም ነውና።” በተባለው አምላካዊ ቃል መሠረት መፍትሔ ሊሆን የሚችለውን፥ በመንፈሳዊ ጕዞ የታጀበ ትዕግሥትን ገንዘብ ማድረግ ነው። ያዕ. 5፡10-11፤ ራእ. 2፡19። “አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው? እግዚአብሔር አይደለምን? ትዕግሥቴም ከአንተ ዘንድ ነው። ከኃጢአቴ ሁሉ አድነኝ፥ ለሰነፎችም ስድብ አታድርገኝ። አንተ ሠርተኸኛልና ዝም አልሁ፤ አፌንም አልከፈትሁም። መቅሠፍትህን ከእኔ አርቅ! ከእጅህ ብርታት የተነሣ አልቄአለሁና። በተግሣጽህ ስለ ኃጢአቱ ሰውን ዘለፍኸው፥ ነፍሱም እንደ ሸረሪት ድር ታልቃለች፤ በእውነት ሰው ሁሉ ከንቱ ነው። አቤቱ! ጸሎቴን ስማ! ጩኸቴንም አድምጥ! ልቅሶዬንም ቸል አትበለኝ! ፤ እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝና፥ እንደ አባቶችም እንግዳ ነኝና። ወደማልመለስበት ሳልሄድ ዐርፍ ዘንድ ተወኝ!” እያሉ ዘወትር መጸለይም ይገባል፡፡ መዝ. 38፡7-13፡፡ በመቀጠልም ክፍል ፬ የመጨረሻ ይቀጥላል... ጦማሪ፦ መጋቤ ምስጢር ያሬድ  ዘርአ-ቡሩክ ዩቲዩብ👇 https://www.youtube.com/@Yared-Zeraburuk ቴሌግራም ቻናል https://t.me/yaredzer

• በተቅዋመ ብርሃን ብርሃነ እምከመ የኀቱ ሊቀ ካህናት አሮን ገፋዔ ገፋዒ ዮርማሮዴቅ፥ • እምነ መቅደስ አውፅአ ጸናጽለ ወርቅ ረቂቅ፥ • ከመ ይቁም መዝሙረ ምሳሌ ኢሳይያስ ሊቅ፥ • እስመ ይትራድእዎ ቀዊሞሙ በቤተ ከበሮ ሳሙኤል ወሙሴ በዐምደ ወርቅ። • ማኅሌትሂ ተነብይ እምቅድመ ይኅልቅ፥ • ሕዝቅኤል መዘምር ዖደ በምሥራቅ፥ • ብሂሎ ሚልክያስ ይቀጽበኒ በጽድቅ፥ • አምጣነ ፈቀደ ልቡናሁ በቤተ ልሔም ከመ ይርፍቅ። መወድስ ቅኔ ዘመምህር ገብረ ጊዮርጊስ ገብረ እግዚእ - ዘእስቴ መካነ ኢየሱስ - ዘአኵስም ጽዮን

“በምድር ላይ ረኃብ፥ ወይም ቸነፈር፥ ወይም ዋግ፥ ወይም አረማሞ፥ ወይም አንበጣ፥ ወይም ኩ ኵብኩባ ቢሆን፥ የሕዝብህም ጠላት የሀገሩን ቀበሌዎች ከብቦ ቢያስጨንቃቸው፥ መቅሠፍትና ደዌ ሁሉ ቢሆን፥ ማናቸውም ሰው የልቡን ሕመም ዐውቆ ጸሎትና ልመና ቢጸልይ፥ እጆቹንም ወደዚህ ቤት ቢዘረጋ በማደሪያህ በሰማይ ስማ፥ ይቅርም በል፤ አንተ ብቻ የሰውን ልጆች ሁሉ ልብ ታውቃለህና ልቡን ለምታውቀው ሰው ሁሉ እንደ መንገዱ ሁሉ መጠን ክፈለውና ስጠው!” (1ኛ ነገ. 8፡37-40) ብሎ ጠቢቡ ሰሎሞን በመቅደሱ ዐደባባይ ተንበርክኮ ሲጸልይ እንደ ተናገረም በሰዎች ምልአተ-ኃጢአት ምክንያት ከመጣው ከደዌ ዘመቅሠፍት ለመዳን በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተገኝቶ፥ እደ ልቡናን ዘርግቶ ፍጹም ጸሎትን በፍጹም ሕሊና ማቅረብ ነው። ወዳጄ ሆይ! ቅዱስ መጽሐፍ “ሕዝቤ ሆይ! ና! ወደ ቤትህም ግባ!፥ ደጅህን በኋላህ ዝጋ! ቍጣ መቅሠፍት እስኪያልፍ ድረስ ጥቂት ጊዜ ተሸሸግ!” ይልሃል። ኢሳ. 26፡20-21። “ወደ ቤትህ ግባ!” ሲልህም በድንጋይ፣ በብሎኬት፣ በብረትና በሲሚንቶ አልያም በጭቃና በዕንጨት የተሠራውን፥ ዛሬ አልያም ነገ ጥለኸው የምታልፈውን ምድራዊ ቤትህን እየ ጠቈመህ እንዳልሆነ ልብ በል! ይልቁንም ከኰበለልክበት የኃጢአት ዓለም የዘለዓለም ቤትህ ምሳሌ ወደ ሆነችው፣ የመንፈስ ቅዱስን ልጅነት ወደ ተቀበልክባት፣ ቅዱስ ሥጋው ወደሚፈተትባት፥ ክቡር ደሙ ወደሚሰጥባት፣ ወደ እናትህ፣ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በንስሓ ተመልሰህ ግባ! ሲልህ ነው። አንድም፦ ‹‹ደጅህን በኋላህ ዝጋ!›› ሲልህ የዚያች ምድራዊት ቤትህ በር እየ ጠቈመ ‹‹እጅህንና እግርህን ዐጣጥፈህ ተኛ!›› ያለህ አይምሰልህ! ይልቁንም የእግዚአብሔርን ሕገጋት እስከ ዛሬ ድረስ የሻርክበትን፣ ያፈረስክበትን፣ የጣስክበትን የኃጢአት በር በንሥሓ ዐጥር ዐጥረህ የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም በመቀበል መዝጊያ ዝጋ!  ሲልህ ነው። አንድም፦ “ቍጣ እስኪያልፍ ድረስ ጥቂት ጊዜ ተሸሸግ!” ቢልህ በበደልህ ምክንያት የመጣው ቍጣ እስኪመለስ ድረስ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደትና በሱባዔ ቈይ! ሲልህ ነው። በኃጢአትህም ምክንያት ከመጣብህ ከደዌ ዘመቅሠፍት ትድን ዘንድ ካንተ ልመና በተጨማሪ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድልህና የሚለምንልህ ከቅዱሳን መካከል እንደ ሙሴ ያለ ራሱን ስላንተ አሳልፎ የሚሰጥ፥ በእግዚአብሔር ፊትም ለምልጃ የሚቆም ቅዱስ አማላጅ ያስፈልግሃል። ዘፀ. 32፡31-33። ስለ ሆነም ወዳጄ ሆይ!  ያንተ በንስሓ መመለስና ጸሎት እንዳለ ሆኖ ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቅህና ምሕረት ሊያሰጥህ በሚችል በአካለ ሥጋም በአካለ ነፍስም ባሉ የቅዱሳን ምልጃና ጸሎት ያለ መጠራጠር ታመን! በመቀጠልም ክፍል ፫ ይቀጥላል… ጦማሪ፦ መጋቤ ምስጢር ያሬድ  ዘርአ-ቡሩክ ●➖●➖●➖● ቅኔን በቴሌግራም ለመማር👇 https://t.me/kineyared ቴሌግራም ቻናል https://t.me/yaredzer ዩቲዩብ👇 https://www.youtube.com/@Yared-Zeraburuk ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/1Gw4Rx8hAC/