Prince Faysul
Ir al canal en Telegram
5 928
Suscriptores
-124 horas
-177 días
-1430 días
Archivo de publicaciones
5 928
እናታችን ሀጀር በሶፍና በመርዋ መሀል ስትወጣና ስትወርድ የነበረው ተስፍዋ ትንሽየ ጥሞን የምታስታግስበት ውሀ ፈልጋ አላህ ግን የዘምዘም ውሃን እስከዛሬ ድረስ ያላለቀ ምንጭ ወፈቃት የአላህ ብስራት ፈረጃም ሲመጣ እንደዚሁ ነው ።
5 928
ነብዩላህ ዩሱፍ አለይሂ ሰላም እስር ቤት ውስጥ አብረውት ሁለት ወጣቶች ነበሩ ዩሱፍ ከሁለቱም በልብ ጥራት ይበልጥ ነበር ቢሆንም ግን አላህ እነሱን ቀድሞ ከእስር አወጣቸው ። አንደኛው የወጣው ሰራተኛ ለመሆን ሲሆን ሁለተኛው ለመገደል ነበር ከእስር የወጣው ነብዩላህ ዩሱፍ ደሞ ከአመታት ብኋላ የንጉሱ አማካሪ ለመሆን ከእስር ነፃ ተባለ እናልህ ወዳጄ ምኞታችን ሊዘገይ ይችላል ስጧታው ሊበዛ ሲል....❤
5 928
ህይወት በውጣ ውረድ ስትሞላ፣ ቀናቶቿም አሰልቺ በሆነ የድካም ስሜት ሲደነዝዙ... ነፍስ ጥቂት የራስዋን የጸጥታ ስፍራ ትሻለች። አሻግረን ለማየትና የነገን ብሩህ ተስፋ ለመሰነቅ፣ ለራሳችን የምንሰጣት ጥቂት ክፍተት ያስፈልገናል።
ሁልጊዜ በአንድ አይነት አሰልቺ መንገድ እየተጓዙ፣ የተለየና አዲስ መዳረሻን መመኘት በፍፁም አይቻልም። እስኪ ቆም በልና አስተውል... ባለፍከውና ዛሬም በምትሮጠው የህይወት ትንቅንቅ ውስጥ "የኔ" የምትላቸው ትርጉም ያላቸው ነገሮች እየራቁህ ይሆን?
ችግሩ በተፈጠረበት በዚያው በጠበበው አስተሳሰብ ውስጥ ሆኖ መፍትሄን ማለም ዘበት ነው።ስለዚህ... አንድ አፍታ ወስደህ ለራስህ ጥቂት ጊዜ ስጥ…
መልካም ጁመዓ!
5 928
መንገድ ላይ ሰወችን የሚያሰቃዩ ችግሮችን ማስወገድ የኢማን ክፍል ከሆነ...የልቦችን ስቃይ ማቅለልና ማስወገድስ የትኛው ከፍ ያለ የኢማን ክፍል ሊሆን እንደሚችል አስብት ...
የልብ ስሜት ከእግር ይበልጣልና
5 928
ኢላሂ ነብዩላህ ሙሳ የጠየቀውን ጥያቄ ተቀበልከው ልብ የፈለገውንም አደረክለት
እኔ ደሞ ሙሳ አይደለሁም ብትሩም የለኝም እንዲሁም የተለያዩ ተዓምራትን ማድረግ እንድችል አልተደረኩም ነገር ግን አንተ "አላህ ነህ "...
5 928
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ ወንድምና እህቶቼ
የፊታችን ሐሙስ የሙሐረም 10ኛ ቀን (የዐሹራ ዕለት) መሆኑ ይታወቃል። ይህ ቀን አላህ (ሱ.ወ) ነቢዩላህ ሙሳንና ሕዝቦቻቸውን ከፊርዐውን ግፍ ያዳነበት፣ ታላቅ የድልና የምስጋና ቀን ነው።
✨ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንን ቀን መጾም የባለፈውን የአንድ ዓመት ወንጀል እንደሚያስምር አስተምረውናል።
ስለሆነም፦
ረቡእና ሐሙስን ማለትም(9ኛውንና 10ኛውን ቀን) በመጾም የዚህን ታላቅ ምንዳ ተቋዳሽ እንድንሆን አድራ እንላለን።
5 928
ሴቶችና ዕድሜ
ለፈገግታ
ሁለት ሴቶች ተጨቃጨቁና ፍርድ ቤት ዳኛ ፊት ቀረቡ፤ ዳኛው፦ ከሁለታቹ በዕድሜ ትልቋ ቀድማ ችግሩን ትናገር አላቸው። የሚናገር ጠፋ በመሀከላቸው ሰላምም ሰፈነ መዝገቡም ተዘጋ አሉ።
5 928
አንተ ሀብታም አይደለህም
አላህ ሰቶህ እንጂ
አንተ የምችል አልነበርክም
አላህ ስላገዘህ እንጂ
አንተ አዋቂ አልነበርክም
አላህ አሳወቀህ እንጂ
ስኬቶችን የራስህ አታድርግ እያንዳንዱ ነገርህ የአላህ ትሩፍት እንደሆነ አትርሳ ።
5 928
አሰላሙ አለይክ ለሚያሙህ ቁስለኛው ልብህ
ቢስሚላህ ባደረከው ዱዓ እስክትደሰት
የሙሳ እናት ልጆን ብቻውን ወንዙ ላይ ጣለቺው ..አላህ የአንድ ባሪያ ዱዓ እንደማይተው በደንብ እርግጠኛ ስለነበረች አላህ ልቦን ጠገነላት
5 928
በልብህ ውስጥ መቼም የማይተኙ 4 ሌቦች እንዳሉ ታውቃለህ?
ኢማም አል-ገዛሊ (ራ. ዓ)እንዳብራሩት እነዚህ ሌቦች መሣሪያ አይታጠቁም፣ ነገር ግን የልብህን ብርሃን በዝምታ ይሰርቁታል። እነሱም: —
1.ስሜት (ሻህዋ)፦ ደስታን ቃል ይገባል፣ ግን መቼም አይረካም።
2.ቁጣ፦ በፍጥነት ካልጠፋች ቀድማ ያንተን ልብ የምታቃጥል እሳት ናት።
3.የዝና ፍቅር፦ ለአላህ የሚሰራን ንጹህ ስራ ይሰርቃል፤ የሰዎችን አድናቆት ብቻ እንድትሻ ያደርጋል።
4.የሀብት ፍቅር፦ ገንዘብን መሣሪያ ማድረግ ሲገባህ የልብህ ግብ ሲሆን ባሪያ ያደርግሃል።
★መፍትሄው
እነዚህ ሌቦች የውስጥ ሰላምን ያውካሉ፣ ኢባዳን የተራራ ያህል ያከብዳሉ። ፈውሳቸው ዘወትር ራስን መመርመር ሲሆን፥ ይህም ስሜትን በመቃወም፣ ቁጣን በትዕግስት በመስበር፣ ክብርን ለአላህ ብቻ በመስጠት እና ሀብትን በእጅ እንጂ በልብ ውስጥ ባለማስቀመጥ ይገለጻል።
[በሰለዋት የደመቀ በመልካም ስራ የታጀበ ጁምዓ ይሁንልህ የኔ መልካም💖]
