ar
Feedback
Prince Faysul

Prince Faysul

الذهاب إلى القناة على Telegram
5 928
المشتركون
-124 ساعات
-177 أيام
-1430 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

እናታችን ሀጀር በሶፍና በመርዋ መሀል ስትወጣና ስትወርድ የነበረው ተስፍዋ ትንሽየ ጥሞን የምታስታግስበት ውሀ ፈልጋ አላህ ግን የዘምዘም ውሃን እስከዛሬ ድረስ ያላለቀ ምንጭ ወፈቃት የአላህ ብስራት ፈረጃም ሲመጣ እንደዚሁ ነው ።

ነብዩላህ ዩሱፍ አለይሂ ሰላም እስር ቤት ውስጥ አብረውት ሁለት ወጣቶች ነበሩ ዩሱፍ ከሁለቱም በልብ ጥራት ይበልጥ ነበር ቢሆንም ግን አላህ እነሱን ቀድሞ ከእስር አወጣቸው ። አንደኛው የወጣው ሰራተኛ ለመሆን ሲሆን ሁለተኛው ለመገደል ነበር ከእስር የወጣው ነብዩላህ ዩሱፍ ደሞ ከአመታት ብኋላ የንጉሱ አማካሪ ለመሆን ከእስር ነፃ ተባለ እናልህ ወዳጄ ምኞታችን ሊዘገይ ይችላል ስጧታው ሊበዛ ሲል....❤

ህይወት በውጣ ውረድ ስትሞላ፣ ቀናቶቿም አሰልቺ በሆነ የድካም ስሜት ሲደነዝዙ... ነፍስ ጥቂት የራስዋን የጸጥታ ስፍራ ትሻለች። አሻግረን ለማየትና የነገን ብሩህ ተስፋ ለመሰነቅ፣ ለራሳችን የምንሰጣት ጥቂት ክፍተት  ያስፈልገናል። ​ሁልጊዜ በአንድ አይነት አሰልቺ መንገድ እየተጓዙ፣ የተለየና አዲስ መዳረሻን መመኘት በፍፁም አይቻልም። እስኪ ቆም በልና አስተውል... ባለፍከውና ዛሬም በምትሮጠው የህይወት ትንቅንቅ ውስጥ "የኔ" የምትላቸው ትርጉም ያላቸው ነገሮች እየራቁህ ይሆን? ​ችግሩ በተፈጠረበት በዚያው በጠበበው አስተሳሰብ ውስጥ ሆኖ መፍትሄን ማለም ዘበት ነው።ስለዚህ... አንድ አፍታ ወስደህ ለራስህ ጥቂት ጊዜ ስጥ… ​መልካም ጁመዓ!

መንገድ ላይ ሰወችን የሚያሰቃዩ ችግሮችን ማስወገድ የኢማን ክፍል ከሆነ...የልቦችን ስቃይ ማቅለልና ማስወገድስ የትኛው ከፍ ያለ የኢማን ክፍል ሊሆን እንደሚችል አስብት ... የልብ ስሜት ከእግር ይበልጣልና

ኢላሂ ነብዩላህ ሙሳ የጠየቀውን ጥያቄ ተቀበልከው ልብ የፈለገውንም አደረክለት እኔ ደሞ ሙሳ አይደለሁም ብትሩም የለኝም እንዲሁም የተለያዩ ተዓምራትን ማድረግ እንድችል አልተደረኩም ነገር ግን አንተ "አላህ ነህ "...

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ ወንድምና እህቶቼ የፊታችን ሐሙስ የሙሐረም 10ኛ ቀን (የዐሹራ ዕለት) መሆኑ ይታወቃል። ይህ ቀን አላህ (ሱ.ወ) ነቢዩላህ ሙሳንና ሕዝቦቻቸውን ከፊርዐውን ግፍ ያዳነበት፣ ታላቅ የድልና የምስጋና ቀን ነው። ✨ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንን ቀን መጾም የባለፈውን የአንድ ዓመት ወንጀል እንደሚያስምር አስተምረውናል። ስለሆነም፦ ረቡእና ሐሙስን ማለትም(9ኛውንና 10ኛውን ቀን) በመጾም የዚህን ታላቅ ምንዳ ተቋዳሽ እንድንሆን አድራ እንላለን።

የማይመለከትህን አትመልከት መመልከቻህን ታጣለህና!

ልክ እንደ ባብር ሁን ያልጠበቀህን አጠብቅ!

የሚወደውን ነገር በዝምታ እንደሚተው ሰው ግን ጀግና የለም !!

ሴቶችና ዕድሜ ለፈገግታ ሁለት ሴቶች ተጨቃጨቁና ፍርድ ቤት ዳኛ ፊት ቀረቡ፤ ዳኛው፦ ከሁለታቹ በዕድሜ ትልቋ ቀድማ ችግሩን ትናገር አላቸው። የሚናገር ጠፋ በመሀከላቸው ሰላምም ሰፈነ መዝገቡም ተዘጋ አሉ።

በእጅህ ያለው ገንዘብ ምንም ሳይቀንስ ለሌሎች የምትሰጠው ውብ እና ምርጥ ስጦታ ቢኖር "መልካም_ንግግር" ነው።

አንተ ሀብታም አይደለህም አላህ ሰቶህ እንጂ አንተ የምችል አልነበርክም አላህ ስላገዘህ እንጂ አንተ አዋቂ አልነበርክም አላህ አሳወቀህ እንጂ ስኬቶችን የራስህ አታድርግ እያንዳንዱ ነገርህ የአላህ ትሩፍት እንደሆነ አትርሳ ።

እዝነትህ ሁሉንም ነገር ያካበበ ነው እኔ ደሞ ግዛትህ ውስጥ ትንሽየ ነገር ነኝና ጌታየ ሆይ ብቻየን አትተወኝ

አሰላሙ አለይክ ለሚያሙህ ቁስለኛው ልብህ ቢስሚላህ ባደረከው ዱዓ እስክትደሰት የሙሳ እናት ልጆን ብቻውን ወንዙ ላይ ጣለቺው ..አላህ የአንድ ባሪያ ዱዓ እንደማይተው በደንብ እርግጠኛ ስለነበረች አላህ ልቦን ጠገነላት

ተመርጦ post ከተደረገ ህይወት ጋር የራሳችሁን እውነት አታወዳድሩ ... “ ከቲክቶክ መንደር ”
ተመርጦ post ከተደረገ ህይወት ጋር የራሳችሁን እውነት አታወዳድሩ ... “ ከቲክቶክ መንደር ”

🌙✨ የሙሀረም ጨረቃ በመታየቷ አዲሱ አመት ነገ 1 ብሎ ይጀምራል እንኳን ለ1448 ዓ.ሂ በሰላም አደረሳቹህ‼
🌙✨ የሙሀረም ጨረቃ በመታየቷ አዲሱ አመት ነገ 1 ብሎ ይጀምራል እንኳን ለ1448 ዓ.ሂ በሰላም አደረሳቹህ‼

የወንድም የእህት ዱዓ ይደርሳል ከልባቹህ ዱዓ አድርጉልኝ እስኪ

በልብህ ውስጥ መቼም የማይተኙ 4 ሌቦች እንዳሉ ታውቃለህ? ኢማም አል-ገዛሊ (ራ. ዓ)እንዳብራሩት እነዚህ ሌቦች መሣሪያ አይታጠቁም፣ ነገር ግን የልብህን ብርሃን በዝምታ ይሰርቁታል። እነሱም: — 1.​ስሜት (ሻህዋ)፦ ደስታን ቃል ይገባል፣ ግን መቼም አይረካም። 2.​ቁጣ፦ በፍጥነት ካልጠፋች ቀድማ ያንተን ልብ የምታቃጥል እሳት ናት። 3.​የዝና ፍቅር፦ ለአላህ የሚሰራን ንጹህ ስራ ይሰርቃል፤ የሰዎችን አድናቆት ብቻ እንድትሻ ያደርጋል። 4.​የሀብት ፍቅር፦ ገንዘብን መሣሪያ ማድረግ ሲገባህ የልብህ ግብ ሲሆን ባሪያ ያደርግሃል። ★​መፍትሄው ​እነዚህ ሌቦች የውስጥ ሰላምን ያውካሉ፣ ኢባዳን የተራራ ያህል ያከብዳሉ። ፈውሳቸው ዘወትር ራስን መመርመር ሲሆን፥ ይህም ስሜትን በመቃወም፣ ቁጣን በትዕግስት በመስበር፣ ክብርን ለአላህ ብቻ በመስጠት እና ሀብትን በእጅ እንጂ በልብ ውስጥ ባለማስቀመጥ ይገለጻል። [በሰለዋት የደመቀ በመልካም ስራ የታጀበ ጁምዓ ይሁንልህ የኔ መልካም💖]

በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ ማንም ሊደርስባት የማይችል የብቸኝነት ጎጆ አለች ።