486
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች
ቀደም ብለን በገለጺነዉ መሰረት ነገ ሰኞ፥ መስከረም 7፥2016 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30 ጀምሮ መሆኑን በድጋሚ እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች
በቅድሚያ እንኳን ለ 2016 ዓ.ም የት/ት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ!
መልካም የትምህርትና የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁም ልባዊ ምኞታችን ነው፡፡
በመቀጠልም፦
1. የዓመቱ መደበኛ ትምህርት በሁሉም የተቋሙ ግቢዎች መስከረም 07/2016 ዓ.ም ይጀመራል፡፡
2. የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) ተማሪዎችን በተመለከተ፦
ሰኞ የሚገቡት ጀማሪዎች (Pre-KG) ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ የሁለተኛ ዓመት (LKG) እና የሦስተኛ ዓመት (UKG) ተማሪዎች የሚመጡት ማክሰኞ መስከረም 08/2016 ዓ.ም ይሆናል፡፡
3. ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30 ጀምሮ ይሆናል፡፡
4. ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲመጡ እንደተለመደው የደንብ ልብሳቸውን (Uniform) ለብሰው እንዲመጡ ይጠበቃል፡፡
5.ቀደም ሲል እንደገለጽነው ከመንግሥት የቀረቡልንን መጻሕፍት በማስተላለፍ ላይ የምንገኝ መሆናችንን እያሳወቅን ትምሕርት ከመጀመሩ በፊት እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለ ቪዥን ወላጆች
👉 ለ2016 የትምሕርት ዘመን ከ1ኛ -8ኛ ክፍል ለመማር ማስተማር የሚውሉ ለየክፍል ደረጃው የተዘጋጁ የመንግስት መጽሐፍት ት/ቤቱ ያቀረበ ስለሆነ ልጆቻችሁ በሚማሩበት ግቢ በመሔድ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት እንድትገዙ እናሳስባለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር!
ውድ ወላጆች
👉 የ2016 ዓ.ም ምዝገባ የመጨረሻ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም መሆኑን ባሳወቅነው መሠረት አብዛኛው ነባር ወላጅ ተመዝግቧል፡፡
ጥቂት ነባር ወላጆች በተለያየ ምክንያት ያለመመዝገባቸውን ስለተገነዘብን ምዝገባውን ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ዐርብ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም ያራዘምን መሆኑን እየገለጽን፣
ምዝገባውም
ጠዋት ከ2፡30 – 6፡30
ከሠዓት በኋላ ከ8፡00 – 10፡00
የሚካሄድ መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
ለወላጆች በሙሉ
የ2016ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፣ የመጨረሻው የምዝገባ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም ሲሆን
👉 ከሰኞ - ዓርብ ከ2፡30 – 10፡00
👉 ቅዳሜ ከ2፡30 – 6፡00 መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባችሁን እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡
📩ማሳሰቢያ ሰለ ክረምት ትምህርት
📌ነገ ስኞ፣ ሐምሌ 10, 2015 ይጀመራል።
📌ከ ት/ቤት መውጫ ስዓት🕰 6:45 ይሆናል
📌ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሶ መምጣት ይጠበቅባቸዋል።
መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንላችሁ!
የት/ቤቱ አስተዳደር!
📩በ2016 ለ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች
ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ሰኞ ሐምሌ 10 2015 ዓ.ም.ስለሚጀመር ሁሉም የ6ኛና8ኛ ክፍል ተማሪዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው በእለቱ እንዲገኙ እናሳስባለን።
👉ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ይጠበቃል።
👉ትምህርቱ የሚሰጠው በግማሽ ቀን መርሀ ግብር (እስከ 6:45🕰)መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች
ቀደም ሲል ባሳወቅነው መሠረት የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 3 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ነባር ተማሪዎችን የምናስተናግድበት የመጨረሻው ቀን ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባ እንድታካሂዱ እያሣሠብን ከሐምሌ 15 በኃላ የሚመጣ ወላጅ የማይስተናገድ መሆኑን ከወዲሁ እናሣውቃለን።
የት/ቤት አስተዳደር!
ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች
ነገ ፣ማክሰኞ፣ሰኔ 27/2015ዓ.ም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ በሚማሩበት ግቢ ከ7፡00 ጀምሮ ስለሚሰጥ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
