ch
Feedback
Vision Academy Grade 6

Vision Academy Grade 6

关闭频道
486
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች ቀደም ብለን በገለጺነዉ መሰረት ነገ ሰኞ፥ መስከረም 7፥2016 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች ቀደም ብለን በገለጺነዉ መሰረት ነገ ሰኞ፥ መስከረም 7፥2016 ዓ.ም  ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30  ጀምሮ መሆኑን በድጋሚ እናሳውቃለን። ት/ቤቱ

ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች በቅድሚያ እንኳን ለ 2016 ዓ.ም የት/ት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ! መልካም የትምህርትና የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁም ልባዊ ምኞታችን ነው፡፡ በመቀጠልም፦ 1.  የዓመቱ መደበኛ ትምህርት በሁሉም የተቋሙ ግቢዎች መስከረም 07/2016 ዓ.ም ይጀመራል፡፡ 2.  የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) ተማሪዎችን በተመለከተ፦ ሰኞ የሚገቡት ጀማሪዎች (Pre-KG) ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ የሁለተኛ ዓመት (LKG) እና የሦስተኛ ዓመት (UKG) ተማሪዎች የሚመጡት ማክሰኞ መስከረም 08/2016 ዓ.ም ይሆናል፡፡ 3.  ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30  ጀምሮ ይሆናል፡፡ 4.  ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲመጡ እንደተለመደው የደንብ ልብሳቸውን (Uniform) ለብሰው እንዲመጡ ይጠበቃል፡፡ 5.ቀደም ሲል  እንደገለጽነው ከመንግሥት የቀረቡልንን መጻሕፍት በማስተላለፍ ላይ የምንገኝ መሆናችንን እያሳወቅን ትምሕርት ከመጀመሩ በፊት እንድትወስዱ እናሳስባለን።

ቪዥን ወላጆች 👉 ለ2016 የትምሕርት ዘመን ከ1ኛ -8ኛ ክፍል ለመማር ማስተማር የሚውሉ ለየክፍል ደረጃው የተዘጋጁ የመንግስት መጽሐፍት ት/ቤቱ ያቀረበ ስለሆነ ልጆቻችሁ በሚማሩበት ግቢ በመሔድ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት እንድትገዙ እናሳስባለን። የት/ቤቱ አስተዳደር!

📩ውድ ወላጆች📩 በፈተና ቀናት (ዛሬ እና ነገ) ተማሪዎች ከት/ቤት የሚወጡት 6:00 🕰መሆኑን እንገልጻለን። ት/ቤቱ

ውድ ወላጆች 👉 የ2016 ዓ.ም ምዝገባ የመጨረሻ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም መሆኑን ባሳወቅነው መሠረት አብዛኛው ነባር ወላጅ ተመዝግቧል፡፡ ጥቂት ነባር ወላጆች በተለያየ ምክንያት ያለመመዝገባቸውን ስለተገነዘብን ምዝገባውን ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ዐርብ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም ያራዘምን መሆኑን እየገለጽን፣ ምዝገባውም ጠዋት ከ2፡30 – 6፡30 ከሠዓት በኋላ ከ800 – 10፡00 የሚካሄድ መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር!

ለወላጆች በሙሉ የ2016ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፣ የመጨረሻው የምዝገባ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም ሲሆን 👉 ከሰኞ - ዓርብ ከ2፡30 – 10፡00 👉 ቅዳሜ ከ2፡30 – 6፡00 መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባችሁን እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

📩ማሳሰቢያ ሰለ ክረምት ትምህርት 📌ነገ ስኞ፣ ሐምሌ 10, 2015 ይጀመራል። 📌ከ ት/ቤት መውጫ ስዓት🕰 6:45 ይሆናል 📌ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሶ መምጣት ይጠበቅባቸዋል። መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንላችሁ! የት/ቤቱ አስተዳደር!

📩በ2016 ለ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት  ሰኞ ሐምሌ 10 2015  ዓ.ም.ስለሚጀመር ሁሉም የ6ኛና8ኛ ክፍል ተማሪዎች  አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው በእለቱ እንዲገኙ እናሳስባለን። 👉ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ይጠበቃል። 👉ትምህርቱ የሚሰጠው በግማሽ ቀን መርሀ ግብር (እስከ 6:45🕰)መሆኑን እንገልፃለን። ት/ቤቱ

ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች ቀደም ሲል ባሳወቅነው መሠረት የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 3 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ነባር ተማሪዎችን የምናስተናግድበት የመጨረሻው ቀን ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባ እንድታካሂዱ እያሣሠብን ከሐምሌ 15 በኃላ የሚመጣ ወላጅ የማይስተናገድ መሆኑን ከወዲሁ እናሣውቃለን። የት/ቤት አስተዳደር!

ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች ነገ ፣ማክሰኞሰኔ 27/2015ዓ.ም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ በሚማሩበት ግቢ ከ700 ጀምሮ ስለሚሰጥ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር!