486
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች
ቀደም ብለን በገለጺነዉ መሰረት ነገ ሰኞ፥ መስከረም 7፥2016 ዓ.ም ትምህርት የሚጀምር ሲሆን ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30 ጀምሮ መሆኑን በድጋሚ እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች
በቅድሚያ እንኳን ለ 2016 ዓ.ም የት/ት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ!
መልካም የትምህርትና የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁም ልባዊ ምኞታችን ነው፡፡
በመቀጠልም፦
1. የዓመቱ መደበኛ ትምህርት በሁሉም የተቋሙ ግቢዎች መስከረም 07/2016 ዓ.ም ይጀመራል፡፡
2. የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) ተማሪዎችን በተመለከተ፦
ሰኞ የሚገቡት ጀማሪዎች (Pre-KG) ተማሪዎች ብቻ ሲሆኑ የሁለተኛ ዓመት (LKG) እና የሦስተኛ ዓመት (UKG) ተማሪዎች የሚመጡት ማክሰኞ መስከረም 08/2016 ዓ.ም ይሆናል፡፡
3. ከሰኞ መስከረም 07/2016 እስከ ረቡዕ መስከረም 09/2016 ባሉት ቀናት በሁሉም ግቢዎች ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ሲሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚወስዱት ከ6፡30 ጀምሮ ይሆናል፡፡
4. ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲመጡ እንደተለመደው የደንብ ልብሳቸውን (Uniform) ለብሰው እንዲመጡ ይጠበቃል፡፡
5.ቀደም ሲል እንደገለጽነው ከመንግሥት የቀረቡልንን መጻሕፍት በማስተላለፍ ላይ የምንገኝ መሆናችንን እያሳወቅን ትምሕርት ከመጀመሩ በፊት እንድትወስዱ እናሳስባለን።
ለ ቪዥን ወላጆች
👉 ለ2016 የትምሕርት ዘመን ከ1ኛ -8ኛ ክፍል ለመማር ማስተማር የሚውሉ ለየክፍል ደረጃው የተዘጋጁ የመንግስት መጽሐፍት ት/ቤቱ ያቀረበ ስለሆነ ልጆቻችሁ በሚማሩበት ግቢ በመሔድ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት እንድትገዙ እናሳስባለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር!
ውድ ወላጆች
👉 የ2016 ዓ.ም ምዝገባ የመጨረሻ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም መሆኑን ባሳወቅነው መሠረት አብዛኛው ነባር ወላጅ ተመዝግቧል፡፡
ጥቂት ነባር ወላጆች በተለያየ ምክንያት ያለመመዝገባቸውን ስለተገነዘብን ምዝገባውን ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ዐርብ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም ያራዘምን መሆኑን እየገለጽን፣
ምዝገባውም
ጠዋት ከ2፡30 – 6፡30
ከሠዓት በኋላ ከ8፡00 – 10፡00
የሚካሄድ መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
ለወላጆች በሙሉ
የ2016ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፣ የመጨረሻው የምዝገባ ቀን ሐምሌ 15/2016ዓ.ም ሲሆን
👉 ከሰኞ - ዓርብ ከ2፡30 – 10፡00
👉 ቅዳሜ ከ2፡30 – 6፡00 መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባችሁን እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡
📩ማሳሰቢያ ሰለ ክረምት ትምህርት
📌ነገ ስኞ፣ ሐምሌ 10, 2015 ይጀመራል።
📌ከ ት/ቤት መውጫ ስዓት🕰 6:45 ይሆናል
📌ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሶ መምጣት ይጠበቅባቸዋል።
መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንላችሁ!
የት/ቤቱ አስተዳደር!
📩በ2016 ለ6ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች
ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ሰኞ ሐምሌ 10 2015 ዓ.ም.ስለሚጀመር ሁሉም የ6ኛና8ኛ ክፍል ተማሪዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው በእለቱ እንዲገኙ እናሳስባለን።
👉ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ይጠበቃል።
👉ትምህርቱ የሚሰጠው በግማሽ ቀን መርሀ ግብር (እስከ 6:45🕰)መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች
ቀደም ሲል ባሳወቅነው መሠረት የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 3 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ነባር ተማሪዎችን የምናስተናግድበት የመጨረሻው ቀን ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባ እንድታካሂዱ እያሣሠብን ከሐምሌ 15 በኃላ የሚመጣ ወላጅ የማይስተናገድ መሆኑን ከወዲሁ እናሣውቃለን።
የት/ቤት አስተዳደር!
ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች
ነገ ፣ማክሰኞ፣ሰኔ 27/2015ዓ.ም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ በሚማሩበት ግቢ ከ7፡00 ጀምሮ ስለሚሰጥ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
