Tesfa Ayat1 Site2 House Owners Association (40/60 Condominium, Lemikura Sub city, Woreda 03)
Ir al canal en Telegram
ይህ ቻናል በ40/60 አያት 1 ሳይት 2 ክልል የሚገኙ 9 ብሎኮች (ብሎክ 5-8 እና 14-18) ላይ የሚገኙ የቤት ባለቤቶች በአዋጅ ቁ. 370/1995 መሰረት ተደራጅተዉ ላቋቋሙት "ተስፋ አያት 1 ሳይት 2 የጋራ ህንፃ ቤት ባለቤቶች ማህበር" ወቅታዊ መረጃዎችና ማስታወቂያዎች የሚለቀቁበት ነዉ፡፡ አድራሻዉ፡ አዲስ አበባ፣ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 03 አስተዳደር ክልል፣ አያት 49 አካባቢ
Mostrar másEl país no está especificadoLa categoría no está especificada
277
Suscriptores
Sin datos24 horas
+17 días
+130 días
Archivo de publicaciones
ለአያት 1 ሳይት 2 ብሎክ 5-8 እና ብሎክ 14-18 ነዋሪዎችና የቤት ባለቤቶች በሙሉ:
እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!!
ከእንስሳት እርድ ጋር ተያይዞ ለጋራ አካባቢ ንጽህናና ብክለት ጥንቃቄዎች ትኩረት ሰጥተን እንድንፈፅምና ተገቢዉን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት እንድንከተል ከአደራ ጋር መልእክታችንን እናስተላልፋለን::
የእንስሳት እርድ የምትፈጽሙ ፈርሱን እና ሌሎች የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችን በተዘጋጁ ሁለት ጉድጓዶች (ብሎክ 06 ጀርባና ብሎክ 18 ጀርባ) በጥንቃቄ በመድፋት ማስወገድ የምትችሉ ሲሆን፤
አጥንት፣ ሞራ፣ ቀንድ፣ ጭንቅላትና ቆዳ በማዳበሪያ በማድረግ ደረቅ ቆሻሻ ለሚሰበስቡ ማህበራት እንዲታስረክቡ እናሳስባለን።
በምንም ዓይነት መልኩ የእንስሳት እርድ ተረፈ ምርትን በክፍት ማንሆሎች ዉስጥና ባልተፈቀደ ቦታ እንዳይጣል እና ለጋራ አካባቢያችን ንጽሕና ሲባል ሁላችንም ተባብረን እንድንከላከልና ኃላፊነታችንን እንድንወጣ እያልን፤
አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የጤናና የበረከት ዘመን እንዲሆንልን፤ በማህበራችን ሥራዎችም ትብብራችንን አጠናክረን አሁንም በስኬታማ የልማት ተግባራት የምንቀጥልበት ዘመን እንዲሆንልን እንመኛለን፡፡
መልካም አዲስ ዓመት!!
ተስፋ አያት 1 ሳይት 2 የጋራ ህንፃ ቤት ባለቤቶች ማህበር
+2
በመጨረሻም ያልጠበኩት ነገር፡
በማህበሩ ዉስጥ ባለኝ ኃላፊነት በተሰሩ መልካም ሥራዎች ለማመስገንና እዉቅና ለመስጠት ጋቢ አልበስዉኛል፡፡ ለዚህም በጣም አመሰግናለሁ፤ ፈጣሪ ፀጋዉን ያልብሳችሁ እላለሁ፡፡
በብዙ የቤት ባለቤቶችና ነዋሪዎች ቀና ትብብር እና ከኮሚቴ አባላት ጋር በመሆኑ የተሰሩ ሥራዎች በመሆናቸዉ ምስጋናዉና እዉቅናዉ የሁላችንም ነዉ፡፡ በሙያዊና ቴክንካዊ ድጋፍ፣ በሀሳብና በሞራል ከኔ ጋር እጅግ የደከሙና ለተሻለ የኃላፊነት ሥራዎች ያበረቱኝ ግለሰቦች ስላሉ እጅግ አመሰግናለሁ፡፡ አሁንም በእጃችን ቀጣይ የልማት ፕሮጀክቶች/እቅዶች ስላሉ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ የማህበሩ የሁሉም ቤት ባለቤቶች ዓመታዊ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባም ስለሚኖረን ቀኑን በቅርብ ጊዜ ዉስጥ የምናሳዉቃችሁ ይሆናል፡፡
የጋራ ህንፃ ለዘመናዊ አኗኗርና ለአብሮነታችን መጠናከር ብዙ የጋራ እድሎች አሉት!!
በምንችለዉ አቅም እየተባበርን በየጊዜዉ የተሻለ ለዉጥ ለማምጣት በጋራ እንበርታ!!
+2
በመጨረሻም ያልጠበኩት ነገር፡
በማህበሩ ዉስጥ ባለኝ ኃላፊነት በተሰሩ መልካም ሥራዎች ለማመስገንና እዉቅና ለመስጠት ጋቢ አልበስዉኛል፡፡ ለዚህም በጣም አመሰግናለሁ፤ ፈጣሪ ፀጋዉን ያልብሳችሁ እላለሁ፡፡
በብዙ የቤት ባለቤቶችና ነዋሪዎች ቀና ትብብር እና ከኮሚቴ አባላት ጋር በመሆኑ የተሰሩ ሥራዎች በመሆናቸዉ ምስጋናዉና እዉቅናዉ የሁላችንም ነዉ፡፡ በሙያዊና ቴክንካዊ ድጋፍ፣ በሀሳብና በሞራል ከኔ ጋር እጅግ የደከሙና ለተሻለ የኃላፊነት ሥራዎች ያበረቱኝ ግለሰቦች ስላሉ እጅግ አመሰግናለሁ፡፡ አሁንም በእጃችን ቀጣይ የልማት ፕሮጀክቶች/እቅዶች ስላሉ ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ የማህበሩ የሁሉም ቤት ባለቤቶች ዓመታዊ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባም ስለሚኖረን ቀኑን በቅርብ ጊዜ ዉስጥ የምናሳዉቃችሁ ይሆናል፡፡
የጋራ ህንፃ ለዘመናዊ አኗኗርና ለአብሮነታችን መጠናከር ብዙ የጋራ እድሎች አሉት!!
በምንችለዉ አቅም እየተባበርን በየጊዜዉ የተሻለ ለዉጥ ለማምጣት በጋራ እንበርታ!!
+2
የትላንትናዉ ዕለት (01/13/2018) የብሎክ 06 ነዋሪዎች ዓመታዊ ስብሰባ፣ የቆሻሻ ማስወገጃ ሥራ ምርቃትና ልምድ
በማህበራችን "ተስፋ አያት 1 ሳይት 2 የጋራ ህንፃ ቤት ባለቤቶች ማህበር" ስር ከሚታወቁ ዘጠኝ ብሎኮች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ በብሎክ 06 የነዋሪዎች ኮሚቴ አስተባባሪነት ከብሎኩ ነዋሪዎች መዋጮና የዉስጥ ገቢ በመጠቀም ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ (ጋርቤጅ ሹተር) ተሰርቶ ተጠናቆ ለአገልግሎት በማብቃት እኔም በእንግድነት ተገኝቼ ተመርቋል፡፡
ጋርቤጅ ሹተሩ በከተማችን ባሉ አፓርታማ ህንፃዎች ላይ ከሚሰሩት ባልተናነሰ ደረጃ የተሰራ ሲሆን በየፍሎሩ የቆሻሻ ማስገቢያ መስኮቶች እና ታች ቤዝመንት ላይ የማጠራቀሚያ ገንዳ ተሰርቶለታል፡፡
10ኛ ፎቅ ላይ የሚኖር ሰዉ በየጊዜዉ ሰራተኛ እየጠራ ቆሻሻ የማስወሰድ ልፋት ቀርቶለት ቆሻሻዎችን በዓይነት በመለየትና በመቋጠር በቀላሉ በመስኮት ብቻ ወደ ታች መወርወር ነዉ፡፡
በማህበራችን ስር ካሉት ዘጠኝ ብሎኮች ይህ የመጀመሪያ ሥራ ሲሆን ለሌሎች ብሎኮችም እንደ ሞዴል የሚታይና የሚማሩበት ተግባር ነዉ፡፡
የብሎክ 06 ነዋሪዎችና የብሎኩ ኮሚቴ ላደረጋችሁት የአርአያነት ተግባር በማህበራችን ስም እያመሰገንና እያደነቅን ጋርቤጅ ሹተሩ ተሰርቶ ለአገልግሎት መብቃቱ ብቻዉን ግብ ባለመሆኑ በዘመናዊ የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት (በዓይነት በመለየት የማስወገድ ሥርዓት) እና በሌሎች የብሎኩ ቀሪ ሥራዎች ትብብራችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እንላለን፡፡
በሌላ በኩል የብሎኩ ኮሚቴ ከሚያደርጉት ዓመታዊ ስብሰባ በተጨማሪ በወር አንድ ጊዜ ተገናኝተዉ ማህበራዊ ትስስራቸዉን ለማጠናከር እንደሚጠያየቁ እና በአንዳንድ የጋራ ጉዳዮች እንደሚወያዩ የቀረበ ልምድ ሲኖር ይህ ለሌሎች ብሎኮችም እንደ ትምህርት የሚወሰድ ነዉ፡፡
ዉድ የአያት ቁጥር 1 40/60 ሳይት 2 ነዋሪዎች በሙሉ የበኣል ስራዎችንም ከወዲዉ በጋራ እንድን ሰራ ለማሳሰብም ጭምር ነዉ የሚን ወደዉ
ይነበብ ለብሎክ ነዋሪዎችም ይደረስ ተባበሩን
በዚህ ብቻ አትጠብቁን በግቢያችን የታሰበው የመዝናኛ ቦታ ማለትም ለሽማግሌ መቀመጫ ለወጣቶች መወያያ መጫዎቻ ለህፃናት መደሰቻ ቦታ ሊጀመር ነው ። ሁላችሁም ተደስቱ ። አሳቡን ኮመንት አድርጉ የሚሻሻል ካለ በአካል መጥታችሁ እንወያይ አመሰግናለሁ
በዛሬው ዕለት በብሎክ 08 የሊፍት ዕቃ ላይ ዘረፍ ሲፈፅሙ የተያዙ ግለሰቦች
ዛሬ የያዝናቸው ሌቦች ብሎክ 8 የሊፍት እቃ
የትላንት (21/12/2018) ጠዋት ክስተት ሁኔታ እና ቀጣይ ትምህርት፣ መልእክትና ምክር ለሁላችንም፡
ትላንት (21/12/2018) ጠዋት አንድ መኪና ከብሎክ 07 ጀርባ ፓርኪንግ ተሰረቀ ተብሎ በተፈጠረ መደናገጥ ለቀጣይ ትምህርት እንዲሆነን፡
ተሰረቀ የተባለዉ መኪና ወዲያዉ በአቅራቢያ ዋና መንገድ ላይ የተገኘ ሲሆን ጉዳዩ ሲጣራ ባለቤቱ ምሽት ላይ ይዞ ወጥቶ ዋና መንገድ ላይ ባቆመበት ረስቶ ወደ ቤቱ እንደገባና ጠዋት ሲመጣ ፓርኪንግ ቦታ ያሳደረዉ መስሎት ስርቆት እንደተፈፀመ ተደርጎ መደናገጦች፣ አላስፈገላጊ ፀብና ክርክሮች ተፈጥሯል፡፡ መኪናዉ ወዲያዉ መገኘቱ ተረጋግተን ወደየሥራችን የሄደን ሲሆን ለቀጣይ ትምህርት እንዲሆነን ማታ ተገናኝተን አምሽተን ተወያይተናል፡፡
ለቀጣይ ትምህርት፣ መልእክትና ምክር ለሁላችንም፡
1. የመኪና ባለቤቶች/አሽከርካሪዎች በተመደበላችሁ የፓርኪንግ ቦታዉ ላይ ለአዳር ስታቆሙ ያቆማችሁበት ሰዓት ጭምር እርግጠኛ በመሆን ለእለቱ ተረኛ ጥበቃ ማሳየትና የእለቱን ተረኛ ጥበቃ ስም መያዝ
2. ጠዋት ከቆመበት ሞተር ከማስነሳት በፊት የመኪናዎን ደህንነት በደንብ መፈተሽ፣ ማታ ባደረበት ሁኔታ መገኘቱን ማረጋገጥ
3. ስርቆት ወይም የተለየ ሁኔታ ሲያጋጥም ለጥበቃ ኃላፊ አቶ አዳነ (0919549390)፣ ለማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ዳኜ (0911803853) ወይም ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ገነት (0973461244) እና ለፖሊስ ማመልከት/ማዝመዝገብ፣ ማመልከቻና የሚያዝ ጊዜያዊ ቃለ ጉባኤ መፈራረም
4. ጉዳዩ በህግ አካል ተይዞና ተጣርቶ ተገቢዉ መፍትሔ ላይ ሳይደረስ ምንም ዓይነት የፍረጃና አላስፈላጊ ስሜት ከማንፀባረቅ መቆጠብ፣
5. ለመፍትሔዉ አስፈላጊዉን መረጃዎች/ማስረጃዎች በማቅረብ ከመተባበር በስተቀር በአንድ ድርጊት ክስተት የማህበሩንና የጥበቃ ኤጄንሲዉን ስም ከማጥፋትና ማንቋሸሽ ተግባራት መቆጠብ (የድርጅትንም የግለሰብንም የሥራ ሞራልና ሥነ ምግባር መጠበቅ)
6. በክስተቱ ላይ ከጉዳዩ ባለቤት ዉጪ የሆኑ ነዋሪዎች፣ የኮሚቴ ተወካዮች ቶሎ ቸኩለን ያልተጣሩ መረጃዎችን ወደ ማይመለከታቸዉ ሰዎች ከማስተላለፍ ይልቅ በእርጋታ በማየት/በመጠበቅ ለመፍትሔዉ መተባበር
7. በባለፉት አምስት ዓመታት በብዙ ፈተናዎች ዉስጥ እያለፍን ከዓመት ወደ ዓመት የተሻሉ ሥራዎችን እየሰራን እየገነባን ያለነዉን የጋራ ማህበራችንን በአንድ ክስተት/ድርጊት ለመመዘን መቸኮልና ስም ለማጥፋት መሞከር ተገቢ አለመሆኑ ለወደ ፊቱ መታረም አለበት፡፡
8. በቀን 15/12/2018 ዓ.ም የአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች ማህበራት ኮሚቴዎች በተገኙበት በከተማ ደረጃ በተከናወነዉ የሰላምና የፀጥታ የግንዛቤ ማስጨበጫና ስብሰባ ላይ በተለያየ አካባቢ በተራቀቀ ስልት የመኪና ስርቆቶች እያጋጠሙ መሆናቸዉን የተገለፀልን በመሆኑ የማህበራችንና የጥበቃ ኤጄንሲዉ ሥራዎች እንደተጠበቀ ሆኖ የመኪና ባለቤቶች/አሽከርካሪዎችም አስፈላጊዉን ጥንቃቄ እንድታደርጉ እንመክራለን፡፡ በተለይ መኪና ስታሳድሩ ከላይ የተጠቀሱት እንደተጠበቀ ሆኖ በተቻለ መጠን የመሪ መቆለፊያ ብትጠቀሙ እንላለን፡፡
9. በዚሁ አጋጣሚ የፓርኪንግ አገልግሎት ወርሃዊ ክፍያ ያልከፈላችሁ ካላችሁ ወይም ጊዜ እያሳለፉ ያስቸገሩም ስላሉ ወር በገባ ከቀን 1-5 ዉስጥ እንድትከፍሉ (ኢ.ን.ባ ሒ/ቁ 1000401319178) በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
መልካሙንና በጎዉን ለሌሎች፣ ስህተቶችንና ድክመቶችን ለራሳችን በዉስጣችን በመነጋገር ለተሻለ የጋራ ሰላምና ደህንነት እና ምቹ የጋራ አካባቢን ለመገንባት እንተባበር!!
ከሰላምታ ጋር
ተስፋ አያት 1 ሳይት 2 የጋራ ህንጻ ቤት ባለቤቶች ማኀበር
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
+6
የቀን 17/12/2018 ፅዳት ዘመቻ አረሞችን የመመንጠርና የፍሳሽ አካባቢዎችን የማጽዳት ሥራም ያካተተ ነበር፡፡
