Ethiopian Broadcasting corporation ®
Ir al canal en Telegram
Ethiopian broadcasting corporation is a 24 working public media. https://telega.io/c/EBC_TV ማንኛውም አይነት አስተያየት እና ጥቆማ ካላችሁ በዚህ ላኩልን እንቀበላለን!! https://t.me/+G7d4hSzJEhViMzQ0
Mostrar más9 127
Suscriptores
-324 horas
-247 días
-13530 días
Archivo de publicaciones
+4
የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ነው፦ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
***************
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፤ ኢትዮጵያን ከባዕድ ወረራና ከባንዳዎች ሴራ የሚከላከል፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቀና የማይበገር አየር ኃይል መገንባቱን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ሆኗል ያሉት ዋና አዛዡ፤ በቴክኖሎጂ የላቀ፣ በሥነ-ልቦና የጠነከረ፣ ለሀገር ክብር መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆነ እና ጠላትን አምርሮ የሚጠላ ጀግና ሠራዊት መገንባቱን ተናግረዋል።
ሌተናል ጄኔራል ይልማ አክለውም፣ የአየር ኃይሉ የውጊያ ዝግጁነት ቀዳሚ ዓላማ ውጊያን ከሩቅ ማስቀረት ቢሆንም፤ ጠላት የሰላም አማራጭን ችላ ብሎ ወደ ውጊያ ከገባ ግን አየር ኃይላችን የጠላትን ህልውና እስከወዲያኛው የሚያከስም አስተማማኝ መቺ ኃይል መሆኑን በተግባር ያረጋግጣል…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0sySvwwWjnCa7wxiuFRKPJoPGxp5MHGuj7YLaViCS2Jq2fpk4tvmUseUV38LXVhkKl
+2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በይፋ አስጀመሩ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን ብለዋል።
ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ ሲሉም ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ አቅርበዋል።
#Ethiopia #EBC #PMAbiyAhmed
+3
ቱኒዚያ አሰልጣኝ ሳብሪ ላሙቺን አሰናበተች
*********
የቱኒዚያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑ በዓለም ዋንጫው መክፈቻ በስዊድን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት መሸነፉን ተከትሎ፣ የ54 ዓመቱን ዋና አሰልጣኝ ሳብሪ ላሙቺን ማሰናበቱን ‘ዘ ሰን’ ዘግቧል።
ውሳኔው የተላለፈው የፌዴሬሽኑ አመራሮች ከሽንፈቱ በኋላ ባደረጉት አስቸኳይ ስብሰባ ሲሆን፣ ደጋፊዎች ድርጊቱን በዓለም ዋንጫ መድረክ ላይ የተወሰደ እጅግ አስከፊ ውሳኔ ሲሉ እየተቹት ይገኛል።
አሰልጣኝ ሳብሪ ላሙቺ የካርቴጅ ንስሮቹን በዋና አሰልጣኝነት የመሩት ለአምስት ጨዋታዎች ብቻ ሲሆን፣ በዓለም ዋንጫው መድረክ ግን በአንድ ጨዋታ ብቻ መርተው መሰናበታቸው በውድድሩ ታሪክ ክስተት ሆኗል።
ቱኒዚያ ከዓለም ዋንጫው በፊት በቤልጂየም እና በስዊድን በሰፊ ግቦች መሸነፏ ይታወሳል። ይህ ደግሞ በደጋፊዎችና በቦርዱ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።
ላሙቺ ቡድኑን ከተረከቡ በኋላ በሄይቲ ላይ ካስመዘገቡት ብቸኛ ድል ውጭ ከካናዳ፣ ኦስትሪያ፣ ቤልጂየም እና ስዊድን ጋር ባደረጓቸው ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻሉም።
የካርቴጅ ንስሮቹ የፊታችን ቅዳሜ ከጃፓን ጋር ወሳኝ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ በመሆኑ፣ የቀድሞ ኮከቡን ዋህቢ ኻዝሪን ወይም የቀድሞውን አሰልጣኝ ሞንድሄር ኬባየርን በጊዜያዊነት ለመሾም ማሰባቸውን ዘ ሰን እና ስፖርት ሞል ዘግበዋል።
በአዲስ የሺዋስ
#FIFAWorldCup #tunisia #Ebc #Sport
+1
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘገበ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ነበር።
ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
+4
የ6ኛ ክፍል ከተማ እና ክልል አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና በነገው ዕለት መሰጠት ይጀምራል
***************
የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ከተማ አቀፍ እና ክልል አቀፍ ፈተና በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በሌሎችም የሀገራችን ክልሎች በይፋ መሰጠት ይጀምራል።
ከነገ ሰኔ 8 እስከ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት በሚሰጠው በዚህ ማጠናቀቂያ ፈተና ላይ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ የሚሸጋገሩበትን ብቃት ለመመዘን በየክልሎቹ የትምህርት ቢሮዎች አዘጋጅነት አስፈላጊው የቅድመ-ዝግጅት ሥራ ተጠናቆ ነገ መርሐ ግብሩ በይፋ እንደሚጀመር…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02vfQ3Ff6YNutwgQmts4y9dXae1sGoNnXRxRbNPo2t6ft2emb94Y9TN9KnMN3QpaFhl
+5
ሲዳማ ቡና ወደ ሊጉ ሻምፒዮናነት ይበልጥ የተቃርበበትን ድል አስመዘገበ
********
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 35ኛ ሳምንት ጨዋታ፤ ሲዳማ ቡና ተጠባቂውን ጨዋታ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር አድርጎ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለዋንጫው ያለውን ዕድል ይበልጥ አስፍቷል።
ለሲዳማ ቡና ያሬድ ባዬ እና ብርሃኑ በቀለ ግቦቹን ሲያስቆጥሩ፣ ለኢትዮጵያ ቡና ዘላለም አባተ ከሽንፈት ያልታደገቻቸውን ከመረብ አሳርፏል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 64 በማድረስ የሊጉን መሪነት ይበልጥ ከማጠናከሩም በላይ ወደ ሻምፒዮንነቱ እጅግ ሲቃረብ፤ ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በ46 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
በሌላ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
ለፈረሰኞቹ የማሸነፊያ ግቦቹን ፍጹም ጥላሁን፣ ሀብታሙ ጉልላት እና የአብሥራ ተስፋዬ ከመረብ አሳርፈዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ49 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ በመሸነፉ የዋንጫ ፉክክር ዕድሉ የጠበበው መቻል በ53 ነጥብ በ2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
#EthiopianFootballEthiopianBroadcastingCorporation #EthiopianPremierLeague
+4
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ውል ላይ ደረሰ
*************
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
በሌላ በኩል ኢራን አሜሪካ በዲፕሎማሲያዊ ሂደቱ ላይ በተደጋጋሚ…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid034fyfhojofYT9669eX5PGpFQUU5xKSCBjDKSnEsqVeunhuNshdCA2YHf1qNhetPScl
የተስፋው ትውልድ አሻራ፡ ከሀገራዊ ራዕይ እስከ ዓለም አቀፍ ልዕልና
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0XdsLQTLnn68wbHUiEPqxLGYqnatNNPNhTpiYELtUTTHAbX81aimEsVHYkU5QQcFgl
+7
ገዳ ሜልባ ለአዲሱ ገዳ ሙደና ስልጣን አስረከበ
*************
በታሪካዊውና ጥንታዊው የገዳ ሥርዓት እሴት መሠረት፣ የቱለማ ገዳ የስልጣን ሽግግር ሥነ-ሥርዓቱን በዛሬው ዕለት አከናውኗል።
በዚህም መሠረት ላለፉት ስምንት ዓመታት በሜልባ ገዳ ዘመን (በአባ ገዳ ጎበና ሆላ) ሲመራ የነበረው የቱለማ ገዳ፣ ስልጣኑን ለአዲሱ ገዳ አስረክቧል።
የዘመነ ሜልባን ማጠናቀቅ ተከትሎ፣ የገዳ…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02tUpiamMkQ3EQh1CqTiwu35o7oC9wkLXAuJYJ5vvEVSh9kp3Ev127Vjc2jX7y15uTl
+3
የተፈጥሮ ጥሪና የእያንዳንዳችን ዐሻራ
************
አረንጓዴ ሕይወት ከሰው ልጅ መኖርና ደህንነት ጋር የማይነጣጠል ጥልቅ ትስስር አለው። ተፈጥሮ ንጹህ አየርን፣ ዝናብንና ለምለም መሬትን በመለገስ የሰውን ልጅ ህልውና ስትደግፍ፣ ሰው ደግሞ እሷን በመንከባከብና በመጠበቅ ውለታዋን ይመልሳል።
ይህ በእንክብካቤ ላይ የተመሠረተ የጋራ መስተጋብር የሕይወት ቀጣይነት መሠረት ሲሆን፣ ኢትዮጵያም ይህንን እውነታ በተግባር በማሳየት ረገድ ተጠቃሽ ታሪካዊ ስኬትን ማስመዝገብ ችላለች።
ሀገራችን በጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ባለፈው ዓመት ብቻ 7.5 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል የቻለች ሲሆን፣ በተለይም በአንድ ጀምበር 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን አፈር በማልበስ የተከናወነው አኩሪ ተግባር የሕዝባችንን የአንድነት ኃይልና ለተፈጥሮ ያለውን የጋራ ጽናት…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02E7n1KcPVo6ofrsBRuC24LGGuSU8vRH45iNxaTNTpq5Tcs1Q65xQTvyHX4WYDiDXnl
+1
ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ አገኘች
**************
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረተበት 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብሯል። በዚሁ መድረክ ላይ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች በርካታ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ላደረገችው ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተቋሙ ከፍተኛ የዕድገት እርከን የሆነው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሰጥቷታል።
በዕለቱም ለክብርት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ ለኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ ለኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ለምክትል ኮማንደር ሰንበሬ ተፈሪ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል። በተጨማሪም በአሰልጣኝነት ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፤ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ አባላትም ዕውቅና ተሰጥቷል።
በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት እውቅ ጀግኖችን በማፍራት በኩል የላቀ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ተቋሙ ይህንኑ አበረታች ሥራውን ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። በበኩላቸው ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ ተቋሙ ታራሚዎችን አምራችና ሕግ አክባሪ ዜጋ አድርጎ የማውጣት ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸው፤ ይህንንም ለማሳካት የስፖርት እና የኪነ-ጥበብ ክፍሎቹ ታራሚውን በማዝናናት፣ በማስተማርና የአካል ብቃት በማጎልበት በኩል ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አስታውቀዋል።
+2
ኳታር 1 - 1 ስዊዘርላንድ፦ የሙሉ ሰዓት ውጤት
******
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ምድብ ሁለት ኳታር ከ ስዊዘርላንድ ያደረጉት ጨዋታ፤ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
ብሪል ኤምቦሎ 17ኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ለስዊዘርላንድ ሲያስቆጥር፤ ቡዓሊም ኮክሂ ኳታርን አቻ ያደረገች ግብ 95ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል።
#WorldCup2026 #qatar #switzerland #EBC #sports
አረንጓዴ አሻራ የ7 ዓመታት ጉዞ
***********
✅ ጠቅላላ የተተከሉ ችግኞች ➡️ ከ48 ቢሊዮን በላይ
✅ የችግኞች የመጽደቅ ምጣኔ ➡️ 84% (ከ40 ቢሊዮን በላይ የጸደቁ)
✅ የሀገራችን የደን ሽፋን ➡️ ከነበረበት 3% ተነሥቶ ወደ 23.6% ደርሷል
✅ ያገገመ የተራቆተ መሬት ➡️ ከ10 ሚሊዮን ሔክታር በላይ
✅ የተፈጠረ ጠቅላላ የሥራ ዕድል ➡️ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች
#Ethiopia #EBC #greenlegacy #success
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋና ጉጉት የሚጠብቀው ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል -
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
"ኢትዮጵያ እየመከረች ነው"
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሐምሌ8 #ኢትዮጵያ
+2
"የኢትዮጵያ ሕዝብ የምክክር ጉባኤ" ሐምሌ 8 በይፋ ይጀመራል፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
***********
በኢትዮጵያ በሂደት ላይ በሚገኘው ሀገራዊ ምክክር ሀገራችን ወደ አዲስ የፖለቲካ የታሪክ ምዕራፍ የምትሻገርበት ወሳኝ ድልድይ እየተገነባ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በሀገራችን ስር የሰደዱና ለዘመናት የቆዩ የቅራኔ ምንጮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመፍታት ታሪካዊ ኃላፊነት ተረክቦ እየተንቀሳቀሰ ነው።
ዋነኛ ግቡም በፖለቲካው ሳቢያ የሚስተዋሉ መሠረታዊ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት ነው። ይህም ብሔራዊ መግባባትን ለማምጣት፣ ማኅበራዊ መተማመንን ለማደስ እና የሀገርን አንድነት በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ነው።
ኮሚሽኑ “ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!” በሚል መሪ ቃል እያከናወነ ያለው ተግባር…https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0HLrTEJEJ1UuXeqxuU7MrkeFjVKetQHyD6yxp4TMx9W6tFAZCudZ8rXxi1i1z2kVLl
+2
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ እወስዳለው ያሉትን ጥቃት እንደተዉት አስታወቁ
**************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል እንዳሳየ እና ከስምምነት ሊደረስ እንደሚችል በመግለፅ በኢራን ላይ ሊሰነዝሩት ያሰቡትን ጥቃት ማቋረጣቸውን አስታውቀዋል።
ትራምፕ ትናንት ሐሙስ ኻርግ ደሴት ላይ ኢራንን “ክፉኛ እንመታለን” ብለው ቢዝቱም፤ ሊያደርሱት የነበረውን ጥቃት ለመሰረዝ መወሰናቸውን ነው የተናገሩት።
ከኢራን ጋር የሚፈረመው የመግባቢያ ሰነድ “የመጨረሻ ደረጃ” ላይ መድረሱን ጠቅሰው በዚህ ሳምንት ስምምነቱ ሊገባደድ እንደሚችል አስረድተዋል። ስምምነቱ የሚፈረመው አውሮፓ ውስጥ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስምምነቱ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያግድ እንዲሁም በአፋጣኝ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት የሚያስገድድ እንደሚሆን ትራምፕ አስረግጠው ተናግረዋል።
ትራምፕ ይህንን ቢሉም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለመቃረባቸውን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በድርድሩ “ከልክ ያለፈ ጥያቄ” እያቀረበች እንደሆነም ጠቅሰዋል።
ኳታር ሁለቱን አገራት ለማሸማገል ጥረት እያደረገች እንደሆነ ተጠቁሟል።
ትራምፕ ኢራን ላይ ጥቃት እንደማይፈጸም መግለጻቸውን ተከትሎ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ማሳየቱን የዘገበው ቢቢሲ ነው ።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢራን #አሜሪካ #ትራምፕ #ሆርሙዝ
ኮሚሽኑ "የኢትዮጵያ ሕዝብ የምክክር ጉባኤ" የሚጀመርበትን ቀን ዛሬ ይፋ ያደርጋል
************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የምክክር ጉባኤ የሚጀመርበትን ቀን ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ይህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት የሚጀመርበትን ዝርዝር መርሃ-ግብር ከምሽቱ 1፡30 ጀምሮ በሁሉም የመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል።
ኮሚሽኑ "ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!" በሚል መሪ ቃል እያከናወነ ያለው ይህ ተግባር፣ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ይታወቃል።
#NationalDialogueEthiopia #Ethiopia #PeaceAndDialogue #EthiopianBroadcastingCorporation
+1
ሁሉም የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች በምልክት ቋንቋ ይተረጎማሉ
****
ይህን እንቅስቃሴ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ፊፋ በመላው ዓለም ለሚገኙ ደጋፊዎች ይበልጥ አካታች የሆነ የውድድር ተሞክሮ ለመፍጠር የታቀደ ትልቅ እርምጃ ሲል ገልጾታል።
የአካል ጉዳት ያለባቸው ደጋፊዎች በስታዲየም ውስጥም ሆነ በሩቅ መመልከቻ አማራጮች አማካኝነት በውድድሩ ሙሉ በሙሉ መደሰት እንዲችሉ ማድረግን ዓላማው አድርጓል።
ማኅበሩ በመግለጫው “ፊፋ አካል ጉዳተኞችን እና ቤተሰቦቻቸውን እንዲሁም ጓደኞቻቸውን ጨምሮ ሁሉም ደጋፊዎች በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ላይ ግሩም ተሞክሮ እንዲኖራቸው ለማድረግ ቁርጠኛ ነው” ብሏል።
ሙሉውን የጨዋታ እንቅስቃሴ በመተርጎም መስማት ለተሳናቸው እና የመስማት ችግር ላለባቸው ደጋፊዎች መሳጭ ተሞክሮ ይሰጣል።
በፊፋ የተመደቡ አስተርጓሚዎች የየደቂቃውን እንቅስቃሴ ማስተላለፍ ብቻ ሳይሆን እንደ ዳኛ ፊሽካዎች፣ የደጋፊዎች የድጋፍ ድምፅ እና በስታዲየሙ ድባብ ውስጥ ያሉ ድምፆችን ያጋራሉ፤ ይህም ደጋፊዎች እያንዳንዱን የጨዋታውን ቅጽበት እንዲከታተሉ ያደርጋቸዋል ነው የተባለው።
የእግር ኳስ ደጋፊዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በካናዳ የሚደረጉ ሁሉም የምድብ ጨዋታዎች የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ትርጉም የሚኖራቸው ሲሆን፣ በሜክሲኮ የሚደረጉ ጨዋታዎች ደግሞ የሜክሲኮ የምልክት ቋንቋ (LSM) ይኖራቸዋል።
ለዚህም እንዲረዳ የሞባይል መተግበሪያ መዘጋጀቱን ነው ፊፋ ያስታወቀው።
በእስከዳር ይኩኖአምላክ
#FIFAWorldCup #Ebc #sport
+2
ኤቨርተን ለበርንሌይ 35 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲከፍል ተወሰነ
ኤቨርተን የፋይናንስ ደንብ (PSR) በመጣሱ ምክንያት ለበርንሌይ 35 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲከፍል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ልዩ ኮሚሽን ወስኗል።
ይህ ውሳኔ አንድ የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ከሌላው በታሪክ የጠየቀውና የተፈቀደለት ትልቁ የካሳ ክፍያ ሆኖ ተመዝግቧል።
መነሻ ምክንያቱ የሚያያዘው ከ2021/22 የውድድር ዘመን ጋር ነው። በወቅቱ ኤቨርተን የትርፍና ዘላቂነት ደንብ (PSR) በመጣሱ በ2023/24 የውድድር ዘመን የአስር ነጥብ ቅጣት ተጥሎበት እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን በርንሌይ "ኤቨርተን ደንቡን በጣሰበት የ2021/22 የውድድር ዘመን የነጥብ ቅጣቱ ተፈጻሚ ቢሆን ኖሮ እኛ ከሊጉ አንወርድም ነበር፤ በመውረዳችን ምክንያት ከፍተኛ የፋይናንስ ኪሳራ ደርሶብናል" በማለት የካሳ ክስ መስርቷል።
በወቅቱ ኤቨርተን 16ኛ ደረጃን ይዞ ሲተርፍ፣ በርንሌይ 18ኛ ደረጃ ሆኖ መውረዱ ይታወሳል።
ኤቨርተን ውሳኔውን "ህጋዊ ያልሆነ፣ መሰረት የሌለው እና ፍጹም የተሳሳተ" ነው ሲል የገለጸው ሲሆን፣ ወዲያውኑ ይግባኝ ማለቱን አስታውቋል። ይህ ውሳኔ ከጸና ለሊጉ ትልቅ መነጋገርያ ይሆናል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ሊድስ ዩናይትድ ቀደም ብሎ ከኤቨርተን ጋር ከፍርድ ቤት ውጭ ስምምነት ማድረጉ ሲነገር፣ እንደ ቼልሲ እና በ115 ክሶች የተጠረጠረው ማንችስተር ሲቲ ያሉ ክለቦች ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ፣ ሌሎች ክለቦችም በተመሳሳይ መልኩ በሚሊዮን የሚቆጠር የካሳ ይገባኛል ክስ እንዲመሰርቱባቸው ትልቅ በር ሊከፍት ይችላል ሲል ስጋቱን ያስቀመጠው ቢቢሲ ነው።
በአዲስ የሺዋስ
#EthiopianBroadcastingCorporation
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
