es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 339 suscriptores, ocupando la posición 6 146 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 357 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 339 suscriptores.

Según los últimos datos del 23 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 507, y en las últimas 24 horas de 14, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.68%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.08% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 681 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 875 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 28.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 24 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 339
Suscriptores
+1424 horas
+1027 días
+50730 días
Archivo de publicaciones
"እርስ በርሱ የሚናበብ ትውልድን በተገቢው መንገድ በመቅረጽ ቤተ ክርስቲያንን ለመታደግ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስተግበር የሁላችንም ድርሻ ነው።" (ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
+6
"እርስ በርሱ የሚናበብ ትውልድን በተገቢው መንገድ በመቅረጽ ቤተ ክርስቲያንን ለመታደግ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስተግበር የሁላችንም ድርሻ ነው።" (ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ) (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መጋቢት 22/07/2017 ዓ.ም በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት አዘጋጅነት በሀገረ ስብከቱ ስር ላሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ የሚገኘውን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራና መዋቅራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ በማደራጃ መምሪያው ልዑክ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ። ሥልጠናውን በትኩረት ሲከታተሉ የነበሩት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ እስከ "ዛሬ የሥርዓተ ትምህርቱ መዘግየት ብዙ ያጎደለብን ሲሆን አሁንም ባለማስተግበር እንዳናዘገየው አደራ ፤ እንደ ምሥራቅ ሐረርጌ ከሥልጠናው እንደተረዳነው ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚመለከተው ስለሆነ ተባብረን ለማስተግበር እንጥራለን። እስከ ዛሬ እርስ በርሱ የማይናበብ ትውልድ ፈጥረን የምንቸገረው ሥርዓተ ትምህርት ባለመኖሩ ነው።" በማለት አባታዊ መልእክትና መመሪያ አስተላልፈዋል። በሥልጠናውም በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተሳታፊዎች ገልጸው ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ያላቸውን ቁርጠኝነት በአቋም መግለጫ አረጋግጠዋል። የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ክፍል ሐላፊ የሆኑት መልአከ ሰላም ከበደ ይፍሩ የሥልጠናው መርሐ ግብር እስከ ወረዳ በማውረድ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ (አዳማ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ በቀን
+4
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ (አዳማ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ በቀን 20/07/2017 ዓ.ም ውይይት እና ሥልጠና ተከናወነ። የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2014 ዓ.ም በ2 ሰ/ት/ቤቶች ብቻ የተጀመረውን የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት በከተማው በሚገኙ 26 ሰ/ት/ቤቶች እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን ፤ ባለፉት 3 ዓመታት ለሥርዓት ት/ቱ ባለ ድርሻ አካላት ብዙ ሥልጠናዎች ሰጥቷል። የትላንቱም ሥልጠና በዋናነት “የማስተማር ሥነ -ዘዴ” ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ ሥልጠናው የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የግንኙነት ክፍል ሐላፊ በመ/ር ያረጋል አስፋው ተሰጥቷል። በሥልጠናው የሰ/ት/ቤት አባላት ፣ሰባኪያነ ወንጌል እና የአብነት መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከሥልጠናው በተጨማሪ መምህራን በማስተማር ሒደቱ ላይ ያጋጠሟቸው ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረጓል። ለሥርዓተ ትምህርቱ ተጠናክሮ መተግበር የመንበረ ጵጵስና ወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ላደረገው ድጋፍና ክትትል የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከፍተኛ ምሥጋና አቅርቧል። መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት በቅርብ ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆ
+1
የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት በቅርብ ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል። ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል። በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ 👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ 👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት  ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።   ለሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም) "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት
ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም) "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬደዋ የአዲሱ መዋቅራዊ አደረጃጀት አፈፃፀም ዙሪያ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት ጋር ሰፊ ውይይት ተደረገ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት በ13ኛው
+3
በድሬደዋ የአዲሱ መዋቅራዊ አደረጃጀት አፈፃፀም ዙሪያ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት ጋር ሰፊ ውይይት ተደረገ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት በ13ኛው ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ጸድቆ ወደ ትግበራ እየገባ ባለው የሰ/ት/ቤቶች ዝርዝር መዋቅራዊ አደረጃጀት ዙሪያ መጋቤ ሃይማኖት መምህር ዘላለም ፍቃዱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ፣ የአንድነቱ አመራር እና የአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት በተገኙበት በትላንትናው ዕለት ሰፊ ውይይት ተደርገጓል። በውይይቱም  በመወቅራዊ አደረጃጀቱ ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ለጉባኤው የተሰጠ ሲሆን በአፈፃፀሙ ዙሪያ ከጉባኤው ለተነሱ ጥያቄዎችም በቂ ምላሽ እንደተሰጠም ተገልጧል። በመጨረሻም የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፋል ሐላፊ መጋቤ ሃይማኖት ዘላለም ፈቃዱ የአንድ ወር መዋቅሩን የማጥኛ ጊዜ በመስጠት እና ለተፈፃሚነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ በማሳሰብ ስብሰባውን በፀሎት ዘግተዋል። መረጃው የአንድነቱ መረጃና መዛግብት ክፍል ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በጎንደር ርዕስ ከተማ ውስጥ በሚገኙ በ24 ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 30 / 2017 ዓ.ም ተሰጥ
+5
በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በጎንደር ርዕስ ከተማ ውስጥ በሚገኙ በ24 ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 30 / 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ በተለይም በዕርሰ ከተማ በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዘንድሮ ሦስተኛ የትግበራ ዓመታችው  ሲሆን ከ2200 በላይ ተማሪዎች  የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና የካቲት 30/ 2017 ዓ.ም ከ፩ኛ -፬ኛ ክፍል ሥርዓተ ትምህርቱን የሚማሩ ተማሪዎች በ24 ሰንበት ት/ቤቶች ውስጥ ምዘናውን ወስደዋል። በሀገረ ስብከቱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በዕርስ ከተማው ከሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በተጨማሪ በ5 ወረዳዎችም ሥርዓተ ትምህርቱ እየተተገበረ ይገኛል፡፡ በአዘዞ ወረዳም መጋቢት 08/2017 ዓ/ም ከ1400 ያላነሱ ተማሪዎች ተፈትነዋል፡፡ መረጃው የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቅዱስ መስቀል "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ገላ 6:14 መጋቢት 10 የክብር ባለቤት ጌታ
ቅዱስ መስቀል "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ገላ 6:14 መጋቢት 10 የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት የከበረ መስቀል የተገለጠበት እና የተገኘበት ቀን  ዓመታዊ መታሰቢያ ነው። ከዕፀ መስቀሉ በረከት ያሳትፈን የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በባሌ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲሱ የሰ/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። እስካሁን
+7
በባሌ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲሱ  የሰ/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። እስካሁን በሦስት ወረዳወች በ10 አጥቢያ ሰ/ትቤቶች ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል 1271 ተማሪዎች የመንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ሲሆን ቅድመ መደበኛ ለ344 ህጻናት ምዘና ተሰጥቷል። ሌሎች በአጀማመር ወቅት በተለያየ ምክንያት ወደ ኋላ የቀሩ (ዘግይተው የጀመሩ አጥቢያወች) ከመጋቢት 13 እስከ 21 የሚሰጥ ይሆናል። እስካሁን በመንፈቅ ዓመቱ አፈጻጸም 402 ተማሪዎችን በማስፈተን የጎባ ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ፍሬ ሰላማ ሰ/ት/ቤት  ትልቁን ድርሻ ተወጥቷል። መረጃው የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ/ናዝሬት የና/ደ/መ/መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት ከገዳሙና ከካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባባር ለገዳሙና ካቴድራሉ ማኅበረ ካህናት የሰ/ት/
+4
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ/ናዝሬት  የና/ደ/መ/መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት ከገዳሙና ከካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባባር ለገዳሙና ካቴድራሉ ማኅበረ ካህናት የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መርሐግብር አካሔድዋል፡፡ ሥልጠናው የተሰጠው ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድንት አገልጋይ በየሆኑት ቀሲስ አለማየሁ ደበበ ሲሆን ከሥልጠናው በተጨማሪ ከማኅበራት ካህናት በተሰኑ ጥያቄዎች ላይ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ጳውሎስ መርሐግብሩን በጸሎት በማስጀመር የሥልጠናውን ዓላማውን በመግለጸ መርሐግብሩን ያስጀመሩ ሲሆን ማኅበረ ካህናቱም በሥርዓተ ትምህርቱ ተግበራ ላይ ከማስተማረ ጀምሮ በንሰሐ ልጆቻቸው በኩል ሰፊ የቅስቃሳና ሥርዓተ ትምህርቱን የማስተዋወቅ ሥራ እንዲሰሩ  መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም መሰል ሥልጠናዎች ጠቀሜታቸው የጎላ በመሆኑ እንዲሚቀጥሉም አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ
+3
በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ ከተማ በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓት ትምህርት ዘንድሮ ሁለተኛ የትግበራ ዓመቱ ሲሆን የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በከተማው ከሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በተጨማሪ በተወሰኑ ወረዳዎችም መጀመሩን የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አስታውቋል። መረጃው የጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የ
መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስታወቀ፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ክፍል ሐላፊዎች፣ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ አስተባባሪዎችና የአንድነቱ ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመጀመሪያ ወሰነ ትምህርት አተገባበር ላይ ያተኮረ ግምገማ በዛሬው ዕለት አካሄዷል፡፡ የከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነቱ የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መ/ር ቡሩክ ተስፋዬ “ዛሬ ላይ በሕፃናትና ወጣቶች ላይ የሚሠራ ሥራ የነገን ቤተክርስቲያን ቀጣይነት ያረጋግጣል” የሚል መሪ መልእክት መነሻ አድርገው ንግግር ያደረጉ ሲሆን አድባራት ከቁሳዊ ልማት ባሻገር ለሰው ኃይል ልማት ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መ/ር ቡሩክ አክለውም በከተማ አስተዳደሩ አድባራት ከተመዘገቡት 13 ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል በአሥሩ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው የሰበካ ጉባኤያት ትኩረት አናሳ መሆን፣ የግንዛቤ ክፍተትና የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ወጥ አለመሆን ከገጠሟቸው ችግሮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተገኘ መረጃና በአካል በተደረገ ክትትል የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቢኖሩም በመረጃ ክፍተት ምክንያት በትግበራው ላይ ውስንነት ያለባቸው እንዲያሻሽሉ አጫጭር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮችና የኹሉም አድባራት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አስፈጻሚ አባላት በተገኙበት መርሐ ግብሩ ተካሂዷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና
+7
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና አሰጠ፡፡ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወረዳው ስር ባሉ 26 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ላይ በሀገረ አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በወጣ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በ23/06/2017 ከ1ኛ -5ኛ ክፍል እና በ30/06/2017 ዓ.ም ከ6ኛ - 9ኛ ክፍል ያሉ አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበሩ ባሉ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምዘና አሰጥቷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok