es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 359 suscriptores, ocupando la posición 6 129 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 349 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 359 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 522, y en las últimas 24 horas de 23, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 27.03%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 880 visualizaciones. En el primer día suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 359
Suscriptores
+2324 horas
+1087 días
+52230 días
Archivo de publicaciones
"አንተ ጴጥሮስ ነህ ፤ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም።" ማቴ 16፡18 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ
+1
"አንተ ጴጥሮስ ነህ ፤ በዚህችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም።" ማቴ 16፡18 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ ፣ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ እና የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት ለመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ የአድባራት እና ገዳማት የአብነት መምህራንና ሰባኪያነ ወንጌል የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ላይ ያተኮረ ስልጠና እና ውይይት ተካሔደ ፡፡ ለመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት (አዳማ ከተማ) ስር ለሚገኙ ለገዳማትና አድባራት ሰባኪያነ ወንጌል ፣ የዜማ፣ የቅዳሴ፣ የአቋቋም ፣የድጓ ፣የቅኔ ... መምህራን በሰ/ት/ቤቶች እየተተገበረ የሚገኘውን ሥርዓተ ትምህርት አስፈላጊነት ተገንዝበው በሰ/ት/ቤት እንዲያስተምሩ የሚያስችል ስልጠና በ26/10/2016 ዓ.ም የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በጉባኤው መሪነት ፣የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ እና የሀ/ስብከቱ የመምሪያ ኃላፊዎች በተገቡበት ተሰጥቷል፡፡ በዕለቱ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ አባታዊ መመሪያና ቡራኬ በመስጠት የቅድስት ቤተክርስቲያንን ተልዕኮዋን ለማስፈጸም ለተገኙየጉባኤው ተሳታፊዎች የ‹‹ ቤ/ክንን የሚመጥንና ወደ ፊት ሊያሻግራት የሚችል ሐሳብ በማመንጨት የሚሰጠውን ስልጠና በንቃትና በበጎ ጎን በመረዳት ለተግባራዊነቱ የበኩላችሁን እንድትወጡ በማለት አባታዊ መመሪያ በማስተላለፍ ጉባኤውን ከፍተዋል፡፡ ስልጠናው የሥርዓተ ትምህርቱን አስፈላጊነትና ጥቅም ፣የሥርዓተ ትምህርቱን አከፋፈልና የተካተቱ የትምህርት ዓይነቶች፣በሥርዓተ ትምህርቱ ዝግጅት የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ሱታፌ፣በሥርዓተ ትምህርቱ በጠቅላይ ቤተ ክህነትና በሀ/ስብከቱ የተሰጠውን መመሪያ እና በሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ የአብነት መምህራንና የሰባኪያንን ድርሻ የሚሉ ርዕሰ ጎዳዮችን በዝርዝር የዳሰሰ ሲሆን ፤ ስልጠናውን የሰጡት የሀገርአቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት መምህር የሆኑት መ/ር በላይነህ መኮንን የተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት የታሪክ ፣ የዶግማ ፣የሥነ ምግባር እና የሥርዓተ ቤተክርስቲያን ትምህርቶች በተጨማሪ በቀድሞው የአብነት ትምህርት ቤት ብቻ የሚሰጡ የግዕዝ፣ የዜማ፣የቅዳሴ ወዘተ ትምህርቶችን በስፋት ያካተተ መሆኑን ገልጸው፤ ሥርዓተ ትምህርቱ ሊቃውንተ-ቤተ ክርስቲያንን / ሰባኪነ ወንጌልን በሰ/ት/ቤት ገብተው እንዲያስተምሩ በማሰብ የተዘጋጀ በመሆኑ ለትግበራው ሁሉም አካላት በትብብር እንዲሠራ አስገንዝበዋል፡፡ የጉባኤው ተሳታፊዎች ሀሳቦችንና አስተያየቶችን በማንሳት ውይይት ከተካሔደ በኋላ ፤የጉባኤው ተሳታፊዎች ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባኤው ተጠናቋል፡፡ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መለአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ ሥርዓተ ትምህርቱን ሁሉም ሰበኪያነ ወንጌልና የአብነት መምህራን ሰ/ት/ቤት ጋር በመቀራረብ እንዲያስተምሩ መልዕክት አስታልፈው ፤ብጹዕ አባታችን አባታዊ መመሪያ ሰጥተው የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል፡፡ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ ፤ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ እና ሌሎች የማደራጃ ክፍል ኃላፊዎች የሰ/ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት እንዲተገበር ለሰጡት ትኩረትና ፤ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሀ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከፍተኛ ምሥና ያቀርባል፡፡ ************************ የአቋም መግልጫ *********************************************************************** በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የጉባኤው መሪነት ፣የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ እና የመምሪያ ኃላፊዎች ፣ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ የአድባራት እና ገዳማት የአብነት መምህራንና ሰባኪያነ ወንጌል ፣የሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርትና ትምህርት ክፍል ተጠሪዎች በተገኙበት ሰኔ 26/2016 ዓ.ም የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ስልጠና ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላ ቤተክህነት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመጡ ልዑክ በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ፡፡ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን የካህናትና የሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በስልጠናው ላይ አባታዊ መመሪያና ቡራኬ በመስጠት የቅድስት ቤተክርስቲያንን ተልዕኮዋን ለማስፈጸም እዚህ እንደመገኘታችሁ ቤ/ክንን የሚመጥንና ወደ ፊት ሊያሻግራት የሚችል ሐሳብ በማመንጨት የሚሰጠውን ስልጠና በንቃትና በበጎ ጎን በመረዳት ለተግባራዊነቱ የበኩላችሁን እንድትወጡ በማለት አባታዊ መመሪያን በማስተላለፍ ጉባኤውን ከፍተዋል፡፡ በመቀጠልም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ ለጉባኤው ብፁዕነታቸው ያስተላለፉትን አባታዊ መመሪያ በመከተል ጉባኤው በነቃ ተሳትፎ በመከተታተልና ለተግባራዊነቱ የበኩላችሁን ጉልህ ሚና እንድትወጡ በማለት የአደራ መልእክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን የዕለቱ ስልጠና የተሳካ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመመኘት ወደ እለቱ ስልጣና ተግባቷል፡፡ ስልጠናው የሚከተሉትን ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል ፡፡ 1.እየተተገበረ ያለው ሥርዓተ ትምህርት ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ ዕውቅና ያለው በመሆኑ እኛም የቅድስት ቤ/ክ አደራ ስላለብን በልበ ሙሉነት በመቀበል ባለንበት ገዳማትና አድባራት ከሰ/ት/ቤቱ ጎን በመሆን የሚጠበቅብንን ድርሻ የምንወጣ መሆኑን ቃል እንገባለን፡፡ 2.ሥርዓተ ትምህርቱ ተደራሽነቱ እንዲሰፋ በማስልጠንና በሰ/ት/ቤት መማሪያ ክፍሎች በመገኘት አዲሱን ትውልድ በፍቅርና በእውቀት ለማነጽ የሚደረጉትን እንቅስቃሴዎች ሁሉ በቁርጠኝነት የምንወጣ መሆኑን ቃል እንገባለን፡፡ 3.መምህራን ቤተክርስቲያን ባስቀመጡልን አደራ መሠረት የሚመጡትን ፈተናዎች ሁሉ ታግሰን ተተኪ መምህራንን ለማፍራት ቃል እንገባለን፡፡ 4.አለመግባባቶችን በትምህርት በመፍታት መለያየትን ሳይሆን አንድነትን የሚወድ በሃይማኖት የጸና ትውልድ ለማፍራት እንደምንሠራ ቃል እንገባለን፡፡ 5.ክርስቶስ ያስተማረንን የወንጌል ትምህርት ቋንቋን ባማከለ በከተማና በገጠሪቱ ቤተክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ ሃይማኖት ዶግማና ቀኖና ጠብቀን ለማስጠበቅ የድርሻችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡ ሰኔ 26/2016 አዳማ ኢትዮጵያ መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው፡፡

"በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን ይሉአት ነበር።" ዮሐ 4፡42 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት
"በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን ይሉአት ነበር።" ዮሐ 4፡42 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በጉራጌ ሀገረ ስብከት የወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት በስርዓተ ትምህርቱ ያስተማራቸውን ከ1-11 ክፍል የሁለተኛውን መንፈቅ አመት ማጠቃለያ
+9
በጉራጌ ሀገረ ስብከት የወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት በስርዓተ ትምህርቱ ያስተማራቸውን ከ1-11 ክፍል የሁለተኛውን መንፈቅ አመት ማጠቃለያ ፈተና ሰጠ። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች የተናበበ ወጥ ዝርዝር መዋቅራዊ አደረጃጀት ሰነድ ተግባራዊ እንዲሆን 13ኛ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በወሰነው መሠረት ለሁሉም መዋቅር ተላከ:- ቅዱስ ሲኖዶስ ለሰ/ት/ቤቶች ማ/መመሪያ ዓለም አቀፍ ስ/ት/ቤቶች አንድነት በተሰጠው መተዳደርያ ደንብ መሠረት ከአጥቢያ ስንበት ትምህርት ቤቶች ጀምሮ እስከ መንበረ ፓትርያርክ ያለው የስንበት ት/ቤቶች አገልግሎት ወጥ፣ የተናበበ፣ በዕቅድ የሚመራ እና በተደራጀ ሥርዓተ ትምህርት የሚያስተምሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ወደ ተደራጀ መዋቅራዊ አደረጃጀት እንዲመጡ የሚመራ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በመመሥራት ሥራ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዚህ ዓመት 13ኛው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 15ና 16/2016 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን ከተወሰኑ ውሳኔዎች መካከል የሰንበት ት/ቤቶች ዝርዝር መዋቅራዊ አደረጃጀት በሁሉም መዋቅር ተግባራዊ እንዲሆን እና የሁሉም መዋቅራት አመራር ምርጫ በአንድ ጊዜ እንዲፈጸም ነው፡፡ በዚህም መሠረት ከመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ድረስ እንዲተገበር የተዘጋጃው ዝርዝር መዋቅራዊ አደረጃጀት ተደራሽ እንዲሆን በስስ ቅጅ በድረ ገጹ https://eotc-gssu.org/a/ ስለ አንድነቱ በሚለው ገጽ የተቀመጠ ሲሆን በየደረጃው የሚገኘው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት መዋቅራት እስከ አጥቢያ ከሚመለከተው መዋቅር ጋር በመናበብ የማሰልጠን እና የማስገንዘብ ሥራዎችን በመሥራት ሁሉም መዋቅር በተዘጋጀው አፈጻጸም መሠረት ሥራ አመራር አባላትን በማስመረጥ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ሀገረ ስብከቶች ለሁሉም አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች በደብዳቤ እንዲገለጽላቸው ተያይዞ የተላከ ሲሆን ቀጥታ ለማውረድ የሚከተለውን ሊንክ ቀጥታ ይጠቀሙ ፩_ ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ የሰንበት-ት-ቤቶች-ተቋማዊ-አደረጃጀት (PDF) https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-ተቋማዊ-አደረጃጀት/ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ዘመነ ክረምት ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ድረስ "በምድር ላይ ዝናብን ይሰጣል፥ በእርሻም ላይ ውኃ ይልካል።" ኢዮ 5፡10 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
ዘመነ ክረምት ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ድረስ "በምድር ላይ ዝናብን ይሰጣል፥ በእርሻም ላይ ውኃ ይልካል።" ኢዮ 5፡10 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከኮልፌ እና ከአራዳና ጉለሌ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመሆን ከመጋቢት 19/ 2016 ዓ.ም እስከ ግንቦት 19/2016  ዓ.ም በቅዳሜና እሑድ ለ2 ወራት ሲሰጥ የነበረው የምድባት  የተተኪ መምህራን ሥልጠና የምርቃት መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የትምህርት ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሃይማኖት ይታገሱ ደሴ ፣ የአዲስ አበባ የትምህርት ክፍል እና የሁለቱ ክፍለ ከተሞች አስተባባሪዎች በተገኙበት ዕውቅና የመስጠት መርሐ ግብር  በማድረግ ተጠናቀቀ። በዚህ የዕውቅና መርሐ ግብር ላይ በቀሲስ አለማየሁ የአ/አ/ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የትምህርት ክፍል ተጠሪ የጸሎት እና የተአምረ ማርያም ምንባብ እንዲሁም የመክፈቻ ንግግር ተደርጓል። በመልእክታቸውም የሥልጠናውን አስፈላጊነት እንዲሁም የአንድነትን መንፈስ በሰንበት ት/ቤቶች ማሳደግ እንዲሚኖርብን ያሳሰቡ ሲሆን በማጠቃለያ ንግግራቸውም ሠልጣኝ መምህራኑ በቀጣይ በሚኖራቸው የአንድነት ኃላፊነትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ቤተክርስቲያንን በሚፈለገው መጠንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ እንዲያገለግሉ የማሳሰቢያ መልእክት አስተላልፈዋል። በመቀጠልም በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የትምህርት ክፍል ሐላፊ መጋቤ ሃይማኖት ይታገሱ ደሴ ለዕለቱ መርሐ ግብር ተስማሚ ትምህርተ ወንጌል አስተምረዋል። በመቀጠልም በአ/አ/ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ም/ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን በላይ ገ/ሕይወት በቀጣይ በአንድነቱ ሊሠሩ የታሰቡትን ሥራዎች በማስተዋወቅና ለሠልጣኝ መምህራን መልካም የአገልግሎት ጊዜ ተመኝተዋል። በመጨረሻም ሠልጣኞችን ለላኩ 18 ሰንበት ት/ቤቶች የምስክር ወረቀት እንዲሁም ለ62 ተመራቂ ሠልጣኞችም ዕውቅና በመስጠት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። መረጃውን ያደረሰን የአ/አ/ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በሁሉም አህጉረ ስብከት የመጀመርያ ዙር ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል የሰንበት ት/ቤቶች መጻሕፍ ሥርጭት ተደራሽ እንዲሆን መመሪያ ተሰጠ! በ41ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በቀረበው ወጥ የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ አፈጻጸም ሥርዓት መሠረት የሁሉም አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች እና የየዘርፉ ኃላፊዎች  በተገኙበት የውሳኔ ሐሳብ ቀርቦ ቅዱስ ሲኖዶስ በምልዓተ ጉባኤው የተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት  ለትውልድ እንዲደርስ በሁሉም አህጉረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ተግባራዊ እንዲደረግ ተወስኗል፡፡ ለተግባራዊነቱም በየደረጃው ያለው ሁሉም መዋቅር በዕቅድ ይዞ እንዲተገብረው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት መመሪያ መተላለፉ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ለትግበራዊ አስፈላጊ ከሆነው አንዱ የመጻሕፍት ዝግጅት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ የሰንበት ት/ ቤቶች ማ/መማሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፫ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየመምሪያው ሓላፊዎች፣ የአኅጉረ ስብከቱ የተወከሉ የሀገረ አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አጠቃላይ ጉባኤ አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡  በዚሁ አግባብ በመጀመርያ ምዕራፍ በየደረጃው ባለው የቤተ ክህነት መዋቅር በመነጋገር እንድታስፈጽሙ መመሪያ የተላለፍ ሲሆን መጻሕፍቱን ለመግዛት፦ ❶ 1ኛ ክፍል 5 የት/ት ዓይነት በአንድ ጥራዝ መጽሐፍ 450 ብር (10$)፣ ❷ 2ኛ ክፍል 6 የት/ት ዓይነት በአንድ ጥራዝ መጽሐፍ 450 ብር (10$)፣ ❸ 3ኛ ክፍል 6 የት/ት ዓይነት በአንድ ጥራዝ መጽሐፍ 550 ብር (10$)፣ ❹ 4ኛ ክፍል 6 የት/ት ዓይነት በአንድ ጥራዝ መጽሐፍ 550 ብር (10$)፣ ሲሆን በሀገረ ስብከት ደረጃ ለየአጥቢያው ላይብረሪ የሚሆኑ መጻሕፍት ገዝቶ በማሰራጨት፣ አጥቢያ ሰበካ ጉባኤያት ሰበካ ጉባኤያት ለመ/ራን የሚሆኑ መጻሕፍት፣ ሰ/ት/ቤቶች ለአገልጋዮች እና ወላጆችን በማስተባበር ለተማሪዎች ገዝቶ በማሰራጨት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በተላለፈው መመሪያ መሠረት እንዲፈጸም ይጠበቃል፡፡ ለበለጠ መረጃ፡  ዲ/ን ሚኪያስ +251 91 396 9785፣  እና መ/ርያሬድ +251 92 074 1461 እንዲሁም የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ቢሮ ስልክ ቁጥር 0111567279 በኢሜይል office@eotc_gssu.org ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

"ለአንተ የምስጋና መሥዋዕትን እሠዋለሁ፤" መዝ 115(116)፡17 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Y
"ለአንተ የምስጋና መሥዋዕትን እሠዋለሁ፤" መዝ 115(116)፡17 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በ13ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከተናገሩት የተወሰደ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲያካሂድ የነበረው "የሰንበት ት/ቤቶች ቀን" ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ። "የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በጅማ" በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ፲፫ ኛ ጊዜ የ
+7
የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲያካሂድ የነበረው "የሰንበት ት/ቤቶች ቀን" ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ። "የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በጅማ" በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ፲፫ ኛ ጊዜ የተከበረውን የሰንበት ት/ቤቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በጅማ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የሰንበት ት/ቤቶች ቀን ልዩ ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ። ጉባኤው በጅማ ከተማ የሚገኙ የ፲፭ ቱም ሰንበት ት/ቤቶች አባላት በሙሉ የተሳተፉበት ሲሆን ከሰኔ 21 - 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በጅማ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ካቴድራል የተካሄደ ነው። በጉባኤው ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ፣ የየም፣ የሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ፣ ክቡር መልዐከ ሠላም ተስፋ ሚካኤል አሰፋ የጅማ እና የየም አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ ክቡር ላዕከ ወንጌል መምህር ባዬ ከድር የጅማ እና የም አህጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ኃላፊ ፣ የሀገረ ስብከቱ የመምሪያ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በብጹዕነታቸው መመሪያም ይህ የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በጅማ መንፈሳዊ ጉባኤ በየዓመቱ እንዲህ ባለ ድምቀት እንዲከበር ተወስኗል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር በሚገኙ አጥቢያዎች የ፬ [4] ኛ , የ፮ [6] ኛ እና የ፲ [
+7
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር በሚገኙ አጥቢያዎች የ፬ [4] ኛ , የ፮ [6] ኛ እና የ፲ [10] ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የሞዴል (ናሙና) ምዘና ሰኔ 23/2016 ዓ.ም ተሰጠ !!! #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++