es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 359 suscriptores, ocupando la posición 6 129 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 349 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 359 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 522, y en las últimas 24 horas de 23, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 27.03%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 880 visualizaciones. En el primer día suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 359
Suscriptores
+2324 horas
+1087 días
+52230 días
Archivo de publicaciones
"በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር።" ሉቃ 1፡10 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! መልካም ዕለተ ሰንበት! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህር
"በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይጸልዩ ነበር።" ሉቃ 1፡10 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! መልካም ዕለተ ሰንበት! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ!" መዝ 44(45)፡16 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtu
"በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ!" መዝ 44(45)፡16 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሰኔ 21 በዚህች ቀን እምቤታችን ልጇ ወዳጇ በእርሷ ስም በሠራው ቤተ መቅደስ በመገኘት ሐዋርያትን ቀድሶ ያቆረበበት ነው። እንኳን አደረሳችሁ! "ልዑል ማደርያውን ቀደሰ" መዝ 45(46)፡5 የሰንበት
ሰኔ 21 በዚህች ቀን እምቤታችን ልጇ ወዳጇ በእርሷ ስም በሠራው ቤተ መቅደስ በመገኘት ሐዋርያትን ቀድሶ ያቆረበበት ነው። እንኳን አደረሳችሁ! "ልዑል ማደርያውን ቀደሰ" መዝ 45(46)፡5 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መጻሕፍት ስርጭት በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የታተሙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ያሉ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤቶች እያሰራጨ ይገኛል። መ
ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መጻሕፍት ስርጭት በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የታተሙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ያሉ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤቶች እያሰራጨ ይገኛል። መጻሕፍቱን ለመውሰድ፦ 👉 ከሀገረ ስብከት አልያም ከአጥቢያ ደብዳቤ መላክ ያስፈልጋል። 👉 ስርዓተ ትምህርቱን እየተገበሩ ያሉና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እየሰጠ ያለውን የመመዘኛ ፈተናዎች እየወሰዱ የሚገኙ መሆን አለባቸው። የመጻሕፍቱ ዋጋ፦ 1ኛ ክፍል 450 ብር (10$) 2ኛ ክፍል 450 ብር (10$) 3ኛ ክፍል 550 ብር (15$) 4ኛ ክፍል 550 ብር (15$) ምን ያህል መውሰድ ይቻላል? 👉 ከእያንዳንዱ ክፍል መነሻው 6 መጽሐፍ  ሆኖ ከዛ በላይ። ማሳሰብያ 👉 ከእያንዳንዱ ክፍል 6 በአጠቃላይ ከ24 መጻሕፍት በታች መውሰድ አይቻልም ቦታ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መጻሕፍት ስርጭት በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የታተሙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ያሉ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤቶች እያሰራጨ ይገኛል። መ
ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መጻሕፍት ስርጭት በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የታተሙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ያሉ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤቶች እያሰራጨ ይገኛል። መጻሕፍቱን ለመውሰድ፦ 👉 ከሀገረ ስብከት አልያም ከአጥቢያ ደብዳቤ መላክ ያስፈልጋል። 👉 ስርዓተ ትምህርቱን እየተገበሩ ያሉና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እየሰጠ ያለውን የመመዘኛ ፈተናዎች እየወሰዱ የሚገኙ መሆን አለባቸው። የመጻሕፍቱ ዋጋ፦ 1ኛ ክፍል 450 ብር 2ኛ ክፍል 450 ብር 3ኛ ክፍል 550 ብር 4ኛ ክፍል 550 ብር ምን ያህል መውሰድ ይቻላል? 👉 ከእያንዳንዱ ክፍል መነሻው 6 መጽሐፍ  ሆኖ ከዛ በላይ። ማሳሰብያ 👉 ከእያንዳንዱ ክፍል 6 በአጠቃላይ ከ24 መጻሕፍት በታች መውሰድ አይቻልም ቦታ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የዱግዳ ወረዳ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶች ቀንን በማስመልከት የ3 ቀን መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ አከናወነ። በዓሉ በወረዳው ሥር ከሚገኙ ከተለያዩ አጥቢያ የመጡ
+4
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የዱግዳ ወረዳ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶች ቀንን በማስመልከት  የ3 ቀን መርሐ ግብር በደማቅ ሁኔታ አከናወነ። በዓሉ በወረዳው ሥር ከሚገኙ ከተለያዩ አጥቢያ የመጡ የሰንበት ት/ቤት አባላት ልብሰ ስብሐታቸውን ለብሰው በመገኘት በመቂ ደ/አ/ቅ/ጊዮርጊስና ደ/ፀ/ቅ/ማርያም አብያተ ክርስቲያናት አክብረዋል።  ጉባኤው ከሰኔ 14-16/2016 ዓ፡ም የተከናወነ ሲሆን ጉባኤው የተዘጋጀው ከዱግዳ ወረዳ ቤተ ክህነት ጋር በመተባበር ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በመተከል ሀገረ ስብከት የግልግል በለስ ከተማ ሰንብት ትምህርት ቤቶች አንድነት የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ቀንን በድምቀት አከበረ። በዕለቱ መ/ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ የደ/ም ቅ/ጉብርኤል አስተዳዳሪ
+1
በመተከል ሀገረ ስብከት የግልግል በለስ ከተማ ሰንብት ትምህርት ቤቶች አንድነት የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ቀንን በድምቀት አከበረ። በዕለቱ መ/ሰላም ቆሞስ አባ ዮሐንስ የደ/ም ቅ/ጉብርኤል አስተዳዳሪ፣ ቀሲስ ንብረት እጅጉ የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤት ክፍል ሐላፊ፣ የሰላም አርጊው ቅ/ድ/ማርያም መምህራን እና ካህናት የተገኙ ሲሆን የተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብራት ተካሒደዋል። በተመሳሳይ 13ኛውን የሰ/ት/ቤቶች ቀን በደሴ ቅዱስ ገብርኤል ካቴደራል በልዩ ልዩ መርሐ ግብራት ተከብሮ ውሏል በዕለቱም በወረዳው የሰ/ት/ቤቶች ክፍል ሐላፊ እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀው መርሐግብር በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ተጠናቋል። ሰኔ 15/2016 በአውደ ርዕይ የተጀመረው መርሀግብሩ ሰኔ 16
+9
በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሰ/ት/ቤቶች ቀንን በማስመልከት  የተዘጋጀው መርሐግብር በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ተጠናቋል። ሰኔ 15/2016 በአውደ ርዕይ የተጀመረው መርሀግብሩ ሰኔ 16/2015 ልዩ የጋራ ጉባኤ በማድረግ ተጠናቋል። መርሐግብሩ በሳ/ደ/ኃ/ቅ/ገብርኤል ካቴድራል የተደረገ ሲሆን በበዓሉም ላይ ከሁሉም ሰ/ት/ቤቶች አባላት ተገኝተዋል። በአንድነቱ ጽ/ቤት የመክፈቻ ንግግር እና ስለ በዓሉ አከባበር ገለጻ የተደረገ ሲሆን  የዕለቱን ትምህርተ ወንጌል በመጋቢ ምሥጢር መምህር ያሬድ ተሰጥቷል። በመጨረሻም በዘንድሮው አከባበር ላይ የላቀ አስተዋጽዖ ላበረከቱ ፍሬ አምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ፣ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት፣ ሐመረ ኖኅ ሰ/ት/ቤት፣ ፍኖተ ጥበብ ሰ/ት/ቤት እና ደ/አ/አ/ተክለሃይማኖት ሰ/ት/ቤት የምስጋና የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል። ዘገባውን ከድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሚዲያ አግኝተናል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የዩኬና አየርላንድ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምርትቤት አንደነት በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ቀንን በለንደን ደብረገነተ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አሰኪያጅ ቀሲስ ከፍያ
+5
የዩኬና አየርላንድ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምርትቤት አንደነት በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ቀንን በለንደን ደብረገነተ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አሰኪያጅ ቀሲስ ከፍያለው ፣ ካህናት እንዲሁም የማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ በተገኙበት ለ6ጊዜ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ምተከብሯል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! በዓል! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tik
+1
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! በዓል! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቅዱስ ፓትርያርኩ በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር የተፈጠረውን መለያየት ፤ በማቀራረብ ፣ በእርቀ ሰላም እንዲፈቱ በሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጉባኤ ተጠየቁ ። ሰኔ 17/10/2016 (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ዓመታዊ ጉባኤው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ዕለት የሚከበር በመሆኑ በዕለቱ ከበርካታ አህጉረ ስብከት የተሰበሰቡ የጉባዔው ታዳሚዎች ቅዱስ ፓትርያርኩ እረቀ ሰላሙን ለመፈጸም ቃል እንዲገቡላቸው ከመቀመጫቸው በመነሣት በታላቅ አክብሮት ጠይቀዋል ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ የሴት ቤቶች ማ/መማሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፫ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ የቃለ ጉባኤ ማጠቃለያ እና የጋራ አቋም መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተከርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ፲፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 15 እና 16 / 2016 ዓ.ም ከየአህጉረ ስብከቱ የተወከሉ የሀገረ አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አጠቃላይ ጉባኤ አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሄዷል። በመሆኑም በጉባኤው ከቀረቡ ዓመታዊ ሪፖርቶች፣ ተዘጋጅተው ከቀረቡ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከአህጉረ ስብከቶች ከቀረቡ አስተያየቶች እና ከጉባኤው ተሳታፊዎች ከተነሱ የውውይት ሐሳቦች የውይይት ግብዓቶች በመነሳት ባለ 10 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡ 1. በ፲፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ የቀረበውን ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተቀብለን አጽድቀናል፤ ለትግበራው በጋራ እንሠራለን፤ 2. ቅዱስ ሲኖዶስ በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በሁሉም አህጉረ ስብከቶች በሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ተግባራዊ እንዲሆን እና ለማስጀመርያ መጻሕፍት ኅትመት በጀት በመበጀትና እንዲታተሙ በማድረግ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም እና የመምሪያችን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ አመራር ሰጭነትና ክትትል የመጻሕፍት ዝግጅቱ ውጤት ላይ ደርሶ ከኛ እስከ 4ኛ ከፍል 23 የትምህርት አይነት የያዘ በ4 ጥራዝ 23 መጻሕፍት ታትመው ዛሬ በቅዱስ ፓትርያርኩ እንዲመረቁ መደረጉ በሰንበት ት/ቤቶች የአገልግሎት ታሪከ አንዱ ትልቅ ምዕራፍ በመሆኑ በልጅነት መንፈስ አድናቆታችንን እንገልጻለን፤ 3. የታተሙት እና በዝግጅት ላይ ያሉ መጻሕፍት በሁሉም አህጉረ ስብከቶች በሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ተደራሽ እንዲሆኑ በጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ሁሉም መዋቅራት በጀት በጅተው መጻሕፍቱን ለሰንበት ት/ቤቶች መምህራን ተደራሽ እንዲያደርጉ እና ምዕመናን በማስተባበር ተደራሽነቱ እንዲሰፋ እንጠይቃለን፤ 4. በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መመሪያ ማዕቀፍ መሠረት በሚደረገው የትግበራ ሥራ ከሚስተዋሉ የአፈጻጸም ከፈተቶች መካከል የሀገረ ስብከትና ሀገር አቀፍ ምዘና በ4ኛ፣ 6ኛ፣ 10ኛ እና 12ኛ የነበረው ወደ 4ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ እንዲሆን እንዲሁም ሌሎች የተሰጡ አስተያየቶች በመመሪያው እንዲስተካከሉ ወስነናል፤ 5. ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበርና ለአጠቃላይ የሰንበት ት/ቤት እንቅስቃሴ ተገቢው በጀት ከአጥቢያ ጀምሮ በየደረጃው ባሉ የቤተከርስቲያኒቱ መዋቅር እንዲፈቀድ በአጽንኦት እንጠይቃለን፤ 6. ከመንበረ ፓትርያርከ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት ያካተተው ስልታዊ ዕቅድ ዝግጅት በጥልቀት ገምግመናል፡፡ ይህም አገልግሎታችንን ወጥና የተናበበ እንዲሆን መሠረታዊ ስለሆነ በጉባኤው የተሰጡ ማስተካከያዎችን በማካተት ወደ ሥራ እንዲገባ ወስነናል፤ 7. ከመንበረ ፓትርያርከ ጠቅላይ ቤተ ከህነት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት ዝርዝር የአደረጃጀት መዋቅር በ12ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጸድቆ ለትግበራ የቀረበው ሰነድ ለትግበራ በተሰጠው ግንዛቤ ገለጻ መሠረት ሁሉም የሰንበት ት/ቤት ተዋረዳዊ መዋቅራት በአደረጃጀት ሰነዱ መሠረት በተመሳሳይ ጊዜ የአመራር ምርጫ በማከናወን እንዲያስፈጽሙ ወስነናል፤ 8. በ2016 ርከበ ካህናት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጸድቆ ወደ ትግበራ እንዲገባ የተወሰነው መሪ እቅድና መዋቅራዊ አደረጃጀት ውሳኔን ጠቅላላ ጉባኤው በአድናቆት ተቀብሎታል፡፡ ለትግበራውም የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ቃል እየገባን በሕገ ቤተከርስቲያን በተደነገገው የካህናት የምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የአስፈጻሚነት ድርሻ በየደረጃው ባለው የቤተከርስቲያኒቱ መዋቅር ተግባራዊ እንዲደረግ እንጠይቃለን፤ 9. በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚስተዋሉ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ሁሉ በመሳተፍና እንደ ቤተክርስቲያን ተተኪ ልጅነታችን የበኩላችን ሐላፊነት በባለቤትነት መንፈስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ባለው መዋቅር ትኩረት ሰጥተን የምንመራ መሆናችንን እንገልጻለን። 10. በዚኸ ጉባኤ ላይ በተለያዩ ምከንያቶች ያልተገኙ የአህጉረ ስብከት ተወካዮች እንዳሉ ቢታወቅም በተለይ ግን በትግራይ ከልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከቶች ጋር በተፈጠረዉ እጅግ አሳዛኝ መለያየት የተነሣ የከልሉ አህጉረ ስብከት ተወካይ ወንድሞች እና እኅቶች ባለመገኘታቸዉ ጉባኤው ከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶታል!! ከዚህም በላይ ችግሩ ወደ ምዕመናን እየሰፋ መሔዱ ጉባኤውን በእጅጉ አሳስቦታል፡፡ ይኸ መለያየት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ሔዶ በእንዲቷ ቤተከርስቲያን ላይ ከፍተኛ አደጋና የማይጠገን ስብራት ከመድረሱ በፊት ልዩነቶችን አስወግዶ በሥርዓተ ቤተከርስቲያን አግባብ የክልል ትግራይ አህጉረ ስብከቶች ወደ መዋቅራቸው ጠቅላይ ቤተክህነት ይመለሱ ዘንድ፤ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎችም ፍሬ ያፈሩ ዘንድ እግዚአብሔርን ከመለመን ባሻገር የተቻለንን ኹሉ እንደምናደርግ ቃል በመግባት ችግሩን ለመፍታትና እርቀ ሰላሙን ለማምጣት ከፍተኛዉን ድርሻ ሊወጡ የሚችሉት ብፁዕ ውቅዱስ አባታችን እንደኾኑ እናምናለን፡፡ ይኽንኑ ለመፈጸም ቅዱስ ፓትርያርካችን ቃል ይገቡልን ዘንድ በታላቋ ቤተክርስቲያን ስም የቤተከርስቲያን ልደት ተብሎ በሚታወቀው በዛሬው በዓለ ጰራቅሊጦስ ስም ከመቀመጫችን በመነሣት በታላቅ አከብሮት እና ትህትና እንጠይቃለን!! ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ 13ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠላላ ጉባኤ (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube https://www.youtube.com/@eotc-gssu 👉 Facebook https://www.facebook.com/EOTC.GSSU 👉 Telegram https://t.me/eotcgssu21 👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@eotc_gssu 👉 Email office@eotc_gssu.org

13ኛው የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በድምቀት ተከብሮ ዋለ። ሰኔ 16/10/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት) 13ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤ
+2
13ኛው የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በድምቀት ተከብሮ ዋለ። ሰኔ 16/10/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት) 13ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የመምሪያ ሐላፊዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እንዲሁም ቁጥራቸው በርከት ያለ የሰንበት ት/ቤት ዓባላት በተገኙበት ተከብሮ ውሏል። በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ከ1ኛ ክፍል እስከ 4ኛ ክፍል የተዘጋጁት መጻሕፍትም በቅዱስነታቸው ተባርከው የተመረቁ ሲሆን በመጽሐፍ ዝግጅቱ ወቅት የተሳተፉና በሐሳብ በምክር ላገዙት አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube https://www.youtube.com/@eotc-gssu 👉 Facebook https://www.facebook.com/EOTC.GSSU 👉 Telegram https://t.me/eotcgssu21 👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@eotc_gssu 👉 Email office@eotc_gssu.org