es
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Ir al canal en Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

El canal ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 983 suscriptores, ocupando la posición 17 269 en la categoría Educación y el puesto 2 838 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 983 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 04 marzo, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -107, y en las Ăşltimas 24 horas de 0, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 0%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 05 marzo, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a EducaciĂłn.

11 983
Suscriptores
Sin datos24 horas
-337 dĂ­as
-10730 dĂ­as
Archivo de publicaciones
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ እና እራሳቸውን ለይተው የቆዩ ቢሆንም፤ ከ10 ቀን በኃላ ህመማቸው ለውጥ ስላላሳየ ወደ ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ። V
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ እና እራሳቸውን ለይተው የቆዩ ቢሆንም፤ ከ10 ቀን በኃላ ህመማቸው ለውጥ ስላላሳየ ወደ ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ። Via BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🦠 የውጪ ዜና - #CoronaVirus #world Total cases - 1,259,778 Total death - 68,418 Total Recovered - 259,882 #USA Total cases - 330,242 Today New Case -18,885 Total death - 9,443+ Total Recovered - 16,590 #ITALY Total cases - 128,948 Total Recovered - 21,815 Today New Case - 4316 Total death - 15,887 ዛሬ በ24ሰአት ውስጥ 525 ሰው ሞተዋል። #SPAIN Total cases - 130,759 Total Recovered - 38,080 Today New Case - 4591 Total death - 12,418 ዛሬ በ24ሰአት ውስጥ 471ሰው ሞተዋል። #BRITISH(UK) Total cases - 47,806 Total Recovered - 135 Today New Case - 5,903 Total death - 4,934 ዛሬ በ24ሰአት ውስጥ 621ሰው ሞተዋል። #ፈረንሳይ አልተገለፀም። #ጠዋት ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🦠የጎረቤት ሀገራት ዜና 🖍በሱዳን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 12 ደረሱ! ሱዳን በዛሬው እለት ሁለት ተጨማሪ የኮሮና ቫይረስ ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችም 12 ደር
🦠የጎረቤት ሀገራት ዜና 🖍በሱዳን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 12 ደረሱ! ሱዳን በዛሬው እለት ሁለት ተጨማሪ የኮሮና ቫይረስ ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችም 12 ደርሰዋል። በሱዳን ሁለት ሰው ከቫይረሱ ያገገመ ሲሆን ከዚህ ቀደም የሁለት ሰዎች ሞት ሪፖርት መደረጉ አይዘነጋም። 🖍የሩዋንዳ ጤና ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት ሁለት አዲስ ኬዞችን ሪፖርት አድርጓል። በሀገሪቱ ያሉ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ታማሚዎች ቁጥርም 104 ደርሰዋል። 🖍በኬንያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 142 ደረሱ! የኬንያ ጤና ሚንስቴር መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ አስራ ስድስት (16) ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በኮቪድ-19 ሕይወታቸው ላለፈው ሁለት ኢትዮጵያውያን ሀዘናቸውን ገለጹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በኮቪድ-19 ሕይወጣቸው ላለፈው ሁለት ኢትዮጵያውያን የተሰማቸውን ሀዘን
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በኮቪድ-19 ሕይወታቸው ላለፈው ሁለት ኢትዮጵያውያን ሀዘናቸውን ገለጹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በኮቪድ-19 ሕይወጣቸው ላለፈው ሁለት ኢትዮጵያውያን የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ለሁለቱም በኮሮና ቫይረስ ሕይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያውያ ቤተሰቦች እና ወዳጆች ከልብ መጽናናትን፥ ለነፍሳቸው ዘላለማዊ እረፍትን እንዲያገኙ ተመኝተዋል። “ዜናውን የሰማችሁ ሁሉ እንድትረጋጉ እና የወጡትን መመሪያዎች በጥብቅ እንድትከተሉ አሳስባለሁም” ነው ያሉት። “የሚገጥመንን ሁኔታ በጋራ ለማስተናገድ በምንዘጋጅበት በዚህ ጊዜ፣ በእምነት ጸንተን ቫይረሱ በማኅበረሰባችን መካከል እንዳይሠራጭ በትጋት ልንሠራ ያስፈልጋልም” ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ “አካላዊ ርቀታችሁን ጠብቁ፣ እጆቻችሁን በሚገባ ታጠቡ፣በምትችሉት መንገድ ሁሉ ለሌሎች ድጋፍ አድርጉ” ሲሉም አሳስበዋል። #FBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#Ethiopia : ሁለተኛው ሟች የ56 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ ሲሆኑ መጋቢት 24/2012 ዓ/ም የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋግጦ በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነበር። ግለሰቡ ከገቡበት ዕለት ጀምሮ በፅኑ ህክምና ላይ አስፈላጊው ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ሲሆን በዛሬው ዕለት ከቀኑ 12:00 ሰዓት ህይወታቸው አልፏል። በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር 2 ደርሷል። ጤና ሚኒስተር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#BREAKING #Ethiopia : በኢትዮጵያ አንድ ተጨማሪ ሰው በኮሮና ቫይረስ ህይወቱ አልፏል:: በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የሟቾች ቁጥር ሁለት ሆኗል::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ባስተላለፉት መልዕክት በሌሎች አገራት እንደተደረገው የሕዝቡን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ለመዝጋት የሚያስችል አቅም መንግሥታቸው እንደሌለው ገልጸዋል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል “ሙሉ ለሙሉ እንቅስቃሴዎችን ለመዝጋት መንግሥት አቅም የለውም” ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ፤ የሚነገሩ የጥንቃቄ ተግባራትን በመፈፀም የተጎጂዎችን ቁጥር ለመቀነስ መንግሥታቸው እንደሚሰራ አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ሁሉንም ዜጎች ቤታችሁ ተቀመጡ ማለት የማይቻልበትን ምክንያት ሲያስረዱ፤ ቤት የሌላቸው እንዳሉ፤ ያላቸውም ቢሆኑ የዕለት ጉርሳቸውን የሚያገኙት ከእጅ ወደአፍ በሆነ ሁኔታ መሆኑን በማስታወስ መንግሥት ለእነዚህ ወገኖች ምግብ ማቅረብ ካልቻለ የበለጠ ቀውስ እንደሚፈጠር አብራርተዋል። ነገር ግን በመጪው ሳምንት የሚኖረውን የወረርሽኙን አዝማሚያ በማጤን መንግሥት ተጨማሪ እርምጃዎችን ሊወስድ የሚችልበት ዕድል እንዳለ አመልክተዋል። ጨምረውም “ይህንን ወረርሽኝ ከተረዳዳን፣ ከተደማመጥን ዓለም ከዚህ ቀደም ከገጠማት ወረርሽኝ በበለጠ ፍጥነት ለመቆጣጠር እንችላለን” ብለዋል። መንግሥት ባለው አቅም ሞትን ለመቀነስ በርካታ የማስተማሪያ ስልት ቀይሶ እየሰራ ጠቅሰው፤ ነገር ግን የጥንቃቄ መልዕክቶች አሁንም ተግባራዊ ሲደረጉ እንደማይታይና መዘናጋት እንደሚስተዋል ተናግረዋል። የኮሮናቫይረስን በሚመለከት ከአፍሪካ መሪዎችና ከዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸው የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወረርሽኙ አሁን ባለው ሁኔታ በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥ ከቀጠለ ያለው የአገሪቱ የመከላከል አቅም በእጅጉ እንደሚፈተንና አደጋውም ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ስጋት መኖሩንና ገልፀዋል። ሕዝቡ ራሱን የሚነገሩትን የጥንቃቄ መልዕክቶች በአግባቡ እየተገበረ ባለመሆኑ “ስጋታችን ከፍተኛ ሆኗል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ምናልባት ችግሩ ከጸና በማለት ለኢትጵያዊያን ቤተሰቦች ጥያቄ አቅርበዋል። ይህም አንድ ቤተሰብ ለሌላ አንድ ቤተሰብ በቀን አንድ ምግብ ለማቅረብ እንዲዘጋጅ ጠይቀው፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህንንም “ማዕድ ማጋራት” ሲሉ ጠርተውታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ የሆኑት ታከለ ኡማ አዲስ አበባ ሙሉ ለሙሉ የመዝጋት እቅድ እንደሌለ መናገራቸው ይታወሳል። ጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት የበሽታውን መዛመት ለመግታት ሲሉ ከሁለት እስከ ሦስት ሳምንታት የሚቆዩ እንቅስቃሴን ሙሉ ለሙሉ የመዝጋት እርምጃ ወስደዋል። [BBC] ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የጣልያን የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦ ባለፉት 24 ሰዓት በጣልያ የ525 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ቁጥሩ ባለፉት 5 ቀናት ሪፖርት ከተደረጉት #ዝቅተኛ ነው። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 15,887 ደርሷል። በተጨማሪ በ24 ሰዓት 4,316 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 128,948 ከፍ ብሏል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#Coronavirus በግብፅ ሀገር የሚገኙት የቀድሞ የሊቢያ ጠቅላይ ሚንስትር ማህሙድ ጅብሪል በኮሮና ቫይረስ የተነሳ ህይወታቸው አለፈ። ማህሙድ ጅብሪል በግብፅ ለ10 ቀን ያህል በህክምና ሲረዱ እንደነበርም ተነግሯል::

AnimatedSticker.tgs0.15 KB

ኮሮናን ለመከላከል ሲባል የሰዎችን እንቅስቃሴ መረጃ ይፋ እንደሚያደርግ ጎግል አስታውቋል! መረጃው በ131 ሀገራት ያሉ ተጠቃሚዎቹን የእንቅስቃሴ መረጃ በልዩ ድረ-ገፅ ላይ ይፋ የሚደረግ ሲሆን ሰዎች
ኮሮናን ለመከላከል ሲባል የሰዎችን እንቅስቃሴ መረጃ ይፋ እንደሚያደርግ ጎግል አስታውቋል! መረጃው በ131 ሀገራት ያሉ ተጠቃሚዎቹን የእንቅስቃሴ መረጃ በልዩ ድረ-ገፅ ላይ ይፋ የሚደረግ ሲሆን ሰዎች መቼና የት ተገኝተው እንደነበረ ያሳያል፡፡ መረጃዎቹ በዓለም ዙርያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ የሞባይል ተጠቃሚዎች ባሉት የጎግል ማፕ አገልግሎት አማካኝነት የሚሰበሰብ ነው፡፡ የቻይና፣ ሲንጋፖር እና እስራኤልን የኤሌክትሮኒክስ ክትትል እንዲደረግ አዘዋል፡፡ በአውሮፓና አሜሪካን የሚገኙ የቴክኖሎጂ ተቋማትና ግለሰበዊ ነፃነትን የሚጋፋ መረጃ ስብሰባን አጥብቃ የምትቃወመው ጀርመንን ጨምሮ ይህንኑ አማራጭ ለመጠቀም እያሰቡ ይገኛሉ፡፡ የግለሰብ ማንነትን እንዳይታወቅ በሚረዳ ስልት መልኩ ተግባራዊ ይሆናል ቢባልም ከትችት ግን አላመለጠም፡፡ የተለያዩ የመብት ተሟጋቾች ይህ ዘዴ ኮሮናን ምክንያት በማድረግ አምባገነን መንግስታት የገለልተኞችን ድምፅ ለማፈን እና መንግስታዊ ስለላን ለማጠናከር እየተጠቀሙበት መሆኑን ቅሬታ እያሰሙ ናቸው፡፡ ምንጭ፡- Bloomberg, Tech Xplore, Tech IN ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#DrLiaTadesse #VOA ጤና ሚኒስቴር እጅግ ወደ ከፋ መዛመት ሊያመራ ይችላል ላለው እና በጥቂት ሳምንታት ውስጥም የሀገሪቱን የጤና አገልግሎት ስርዓት ሊያሰናክል ይችላል የሚል ስጋት ያሳደረ ከሁሉ የከፋ ሁኔታ ቢፈጠር ለሚሆን አዝማሚያ የሚያዘጋጅ ሙከራ በማድረግ ላይ ነው ይላል ይህ የቪኦኤ ዘገባ። የአሜሪካ ድምፅ አገኙሁት የሚለውና የጤና ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት ያዘጋጀው የትንበያ መረጃ 28 ሚሊዮን የሚደርስ ዜጋ ለቫይረሱ ሊጋለጥ ይችላል ይሆናል የሚል ግምት አስቀምጧል። በመንግስታዊው አሃዝ መሰረትም ቁጥሩ 9,700 የሚደርስ ሰው በመጪዎቹ 4 ሳምንታት ውሥጥ በፅኑ ለታመሙ ህሙማን የሚሰጥ ህክምና አገልግሎት ሊያስፈልገው ይችላል የሚል እቅድ ነው የያየዘው። ማህበራዊ መራራቅ የሚለው አስፈላጊ ጥንቃቄ በተግባር ላይ ውሎም 30,000 ያህል ሰው የሚጋለጥበት ሁኔታ እንደሚፈጠር መረጃው ያመለክታል። ሬድዮ ጣቢያው አግኘሁት የሚለውን መረጃ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አረጋግጠውልኛልም ብሏል። ሰነዱ እስካሁን ባለው ሁኔታ ሙሉ በሙሉ የትንበያ ነው! ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በአለም ላይ በኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ እስከአሁን የተጠቁ ሰዎች ብዛት ከ1 ሚሊየን 30 ሺህ ሲያልፍ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ብዛት ደግሞ ከ54 ሺህ በልጧል:: ከ220 ሺህ በላይ
በአለም ላይ በኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ እስከአሁን የተጠቁ ሰዎች ብዛት ከ1 ሚሊየን 30 ሺህ ሲያልፍ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ብዛት ደግሞ ከ54 ሺህ በልጧል:: ከ220 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ አገግመዋል:: አንዳንድ የአፍሪካ ሀገሮች እና በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ብዛት ****** ኤርትራ 22 ኢትዮጵያ 35 ኬንያ 110 ሩዋንዳ 84 ናይጄሪያ 190 ሴኔጋል 207 ጋና 204 ካሜሮን 306 ሞሮኮ 735 ግብፅ 865 ደቡብ አፍሪካ 1,462 ከነዚህ ሀገራት መሀል ኬንያ 4 ሞቶችን ናይጄሪያ 2 ሴኔጋል 1 ጋና 5 ካሜሮን 7 ሞሮኮ 47 ግብፅ 58 ደቡብ አፍሪካ ደግሞ 5 ሞቶችን አስመዝግበዋል:: ምንጭ worldometer

#Ethiopia : ኮሮና ቫይረስ ጥቁር ነጭ አማራ ትግሬ ኦሮሞ ጉራጌ....አይልም ሲገል ውድ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያኖች በናተ ብርታት ኢትዮጵያዊያን እና ህዝቦቿን ለመርዳት የሚዋጣው ገንዘብ $547,228 ደርሷል $750,000 እስኪደርስ እንበርታ! ይህብ መጥፎ ግዜ አንድ ላይ በመሆን እናልፈዋለን ለኢትዮጵያ ሀገራችን እና ህዝቦቿ እንደርስላታለን:: ወጥር ዲያስፖራ https://www.gofundme.com/f/EthiopiansAgainstCoronaVirus

#NewsAlert‼️ #Ethiopia : በኮሮናቫይረስ የተያዙ #ስድስት ተጨማሪ ሰዎች ተገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 74 ሰዎች ውስጥ 6 ሰዎች በኮሮናቫይረ
#NewsAlert‼️ #Ethiopia : በኮሮናቫይረስ የተያዙ #ስድስት ተጨማሪ ሰዎች ተገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 74 ሰዎች ውስጥ 6 ሰዎች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።  ይህም በኢትዮጵያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 35 እንዳደረሰው የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት፤ በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጡት ውስጥ አምስቱ ከአዲስ አበባ ሲሆን አንድ ከድሬዳዋ ነው። በቫይረሱ የተያዙት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። በአዲስ አበባ ከተያዙት ውስጥ ሁለቱ የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆን የመጀመሪያው የ35 ዓመት ወንድ መጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም ከዱባይ የመጣ፣ ሁለተኛው የ30 ዓመት ወንድ በተመሳሳይ ከዱባይ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም የመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሁለቱም አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የገቡ ናቸው። ሶስተኛው የ28 ዓመት ወንድ፤ አራተኛውም የ56 ዓመት ወንድ፣ አምስተኛው የ30 ዓመት ወንድ የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ናቸው። እነዚህ ሰዎች ያላቸው ግንኙነት እየተጣራ መሆኑን ሚኒስትሯ ገልጸዋል። ስድስተኛዋ ሰው የ33 ዓመት ሴት ስትሆን በድሬዳዋ ከዚህ በፊት በኮሮናቫይረስ መያዙ ከተገለጸው ሰው ጋር ግንኙነት የነበራት መሆኑ ታውቋል።

#NewsAlert‼️ #Ethiopia : በኮሮናቫይረስ የተያዙ ስድስት ተጨማሪ ሰዎች ተገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 74 ሰዎች ውስጥ 6 ሰዎች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።  ይህም በኢትዮጵያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 35 እንዳደረሰው የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት፤ በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጡት ውስጥ አምስቱ ከአዲስ አበባ ሲሆን አንድ ከድሬዳዋ ነው። በቫይረሱ የተያዙት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። በአዲስ አበባ ከተያዙት ውስጥ ሁለቱ የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆን የመጀመሪያው የ35 ዓመት ወንድ መጋቢት 10 ቀን 2012 ዓ.ም ከዱባይ የመጣ፣ ሁለተኛው የ30 ዓመት ወንድ በተመሳሳይ ከዱባይ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም የመጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሁለቱም አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የገቡ ናቸው። ሶስተኛው የ28 ዓመት ወንድ፤ አራተኛውም የ56 ዓመት ወንድ፣ አምስተኛው የ30 ዓመት ወንድ የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ናቸው። እነዚህ ሰዎች ያላቸው ግንኙነት እየተጣራ መሆኑን ሚኒስትሯ ገልጸዋል። ስድስተኛዋ ሰው የ33 ዓመት ሴት ስትሆን በድሬዳዋ ከዚህ በፊት በኮሮናቫይረስ መያዙ ከተገለጸው ሰው ጋር ግንኙነት የነበራት መሆኑ ታውቋል።

📌አጫጭር መረጃዎች፦ ❖ ዛሬ #በአሰላ ከተማ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በዋና ዋና መንገዶች ላይ የፀረ-ተህዋስያን ኬሚካል ርጭት መደረጉን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል፡፡ ❖ #USA ጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ይፋ ባደረገው መረጃ በ24 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 1 ሺህ 169 አሜሪካዊያን በኮሮናቫይረስ ሞተዋል። ይህም ወረርሽኙ በቻይና ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ በአገር ደረጃ በአንድ ቀን ብቻ የተመዘገበ ከፍተኛው የሞት ቁጥር ሆኗል። ❖ #የዓለም_ባንክ ቡድን የዳይሬክተሮች ቦርድ ትላንት ባሳለፈው ውሳኔ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ኢትዮጵያ የሚያስከትለውን የጤና እና የምጣኔ ሀብት ቀውስ ለመቋቋም የሚያስችላትን የ82.6 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንዲሰጣት ማፅደቁን ኢቲቪ ዘግቧል። ❖ በኮሮና ቫረስ ከተያዙት ኢትዮጵያዊያን ውስጥ የጉዞ ታሪኳ ሲገለፅ ጅቡቲ ብራዚል ህንድና ኮንጎ ኢትዮጵያ የተባለችው የ 33 አመት ኢትዮጵያዊ #ሆስተስ ነች:: ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦ - የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአገሪቱ የጣሉትን በቤት የመቀመጥ ውሳኔ በአንድ ወር አራዝመዋል - እስካሁን ቫይረሱ ሀገሯ ሳይገባ የቆየችው ማላዊ በዛሬው ዕለት ሶስት ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች። - የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባኤ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። - በምዕራብ አፍሪካ የነበሩ 3 የፈረንሳይ ወታደሮች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ተሰምቷል። ወታደሮቹ ወደፈረንሳይ እንዲመለሱም ተደርጓል። - በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ የ760 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ በቫይረሱ ተጠቅተው የሞቱ ሰዎች ቁጥር 13,915 ደርሰዋል። በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም 115,242 ደርሰዋል። - በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 5,626 ደርሰዋል። 235,860 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል። - በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በልጧል። ከ51,000 በላይ ሰዎችም ሞተዋል። 210,308 ሰዎች አገግመዋል። -ሳዑዲ አረቢያ የ24 ሰዓት የሰዓት እላፊ በቅዱስ ከተሞቿ ላይ ጥላለች። በመካ እና በመዲና የተጣለው የሰዓት እላፊ የኮሮናቫይረስን ስርጭት ለመከላከል ነው ተብሏል። #SkyNews #BBC #Euronews #Aljazeera ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በመላው ዓለም በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ አንድ ሚሊዮን መቃረቡን የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ አሁናዊ አሃዞች ያመላክታሉ። እስከ ዛሬ ንጋት ድረስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 937,170
በመላው ዓለም በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ አንድ ሚሊዮን መቃረቡን የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ አሁናዊ አሃዞች ያመላክታሉ። እስከ ዛሬ ንጋት ድረስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 937,170 ሲሆን ከእነዚህም መካከል 212,000 የሚሆኑት በአሜሪካ የሚገኙ ናቸው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሟቾች ቁጥር 50 ሺህ ሊደፍን የቀረው ጥቂት ነው። ዛሬ ንጋት ላይ በመላው ዓለም በወረርሽኙ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 47,235 ነው። 😭በአገራት ዝርዝር ደግሞ ከፍተኛውን የሞት ቁጥር ካስመዘገቡ አገራት መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል። ❖ ጣሊያን 13,155 ❖ ስፔን 9,387 ❖ አሜሪካ 5,116 ❖ ፈረንሳይ 4,043 ❖ ቻይና 3,316 ❖ ኢራን 3,036 ❖ ዩናይትድ ኪንግደም 2,357 እንጠንቀቅ !! ምንጭ፦ BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks