es
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Ir al canal en Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

El canal ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 983 suscriptores, ocupando la posición 17 269 en la categoría Educación y el puesto 2 838 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 983 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 04 marzo, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -107, y en las Ăşltimas 24 horas de 0, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 0%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 05 marzo, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a EducaciĂłn.

11 983
Suscriptores
Sin datos24 horas
-337 dĂ­as
-10730 dĂ­as
Archivo de publicaciones
#አንድ ተጨማሪ ሰው አገገመ! በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ ተጨማሪ ሰው ማገገሙን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። በለይቶ ማቆያ ማዕከል ውስጥ #25 የኮሮናቫይረስ ታማሚዎች መኖራቸውን የጤና
#አንድ ተጨማሪ ሰው አገገመ! በኮሮና ቫይረስ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ ተጨማሪ ሰው ማገገሙን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። በለይቶ ማቆያ ማዕከል ውስጥ #25 የኮሮናቫይረስ ታማሚዎች መኖራቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ከህመሙ ማገገማቸው ከተገለጸው ሁለት ህሙማን በተጨማሪ ሌላ ሶስተኛ ሰው ማገገሙን ተናግረዋል። አንድ ታማሚ ብጽኑ ህሙማን ውስጥ የሚገኝ መሆኑን አመልክተዋል። ምንጭ፦ ኢዜአ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

‍ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ስራዎን ለመስራት ተቸግረዋል እነዚህን የቴክኖሎጁ አማራጮች ይሞክሩ!! ------------------------ ወቅታዊው የዓለማችን አደጋ COVID-19 የስርጭት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎችን ከእንቅስቃሴ ውጭ እያደረገ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ብዙዎች በሽውታውን ለመከላከል እና የስርጭት መጠኑን ለመግታት ከመንግስት በወረዱ መመሪያዎች አማካኘነት ስራዎችን ከቤት በመሆን በመከወን ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌሎችም እያንዳንዷን ግንኙነታቸውን በርቀት እየተገበሩ ይገኛል፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት እነዚህን እንቅስቃሴዎች በቀላሉ ለመፈፀም እና ደህንነታችንንም በሚገባ ለመጠበቅ የቴክኖሎጂ እገዛ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ እነዚህ ከስር የምትመለከቷቸው መተግበሪያዎች እና ድረ ገፆች በአብዛኛው የአለም ክፍል መሰል እንቅስቃሴዎችን ከቤት ሆኖ ለመከወን እና ስራዎችን ለማቅለል የሚያገለግሉ ሲሆን፤ በእኛ ሃገር ሁኔታም በሚቻለው አቅም ቢተገበሩ የሚጠቅሙ ናቸው፡፡ ❖መረጃዎችን በአካል መገናኘት ሳያስፈልግ መላላክ የሚቻልባቸው ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች 1. Dropbox 2. Pipebytes 3. MailBigFile 4. filedropper 5. Google drive ❖ስብሰባዎችን እና ውይይቶችን በርቀት ለማከናወን የሚያግዙ ዌብ ቤዝድ መተግበሪያዎች 1. Crowdcast 2. GoToMeeting 3. Cisco Webex Teams 4. Intermedia AnyMeeting 5. https://zoom.us/download ፡ ❖ይህ በተለይም መረጃዎችን ፊት ለፊት በገጽታ ለማዉራት የሚያስችል ታወቂ ሶፍትዌር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎችንም ተግባራት ለማከናወን ይረዳል፤ መረጃን (File) ለመላላክ፣ ጽሁፍ ለመጻጻፍ እና ከ ሁለት በላይ የሆኑ ሰዎችን በተመሳሳይ ሰዓት በተለያየ ጊዜ አስቻይ በሆነ መንገድ ለማገናኘት፣ የተለያዩ ቦታ ሆኖ ህክምና ለመስጠት፣ ሪፖርት ለማድረግ፣ ኮንፈረንስ ለማካሄድ እና ሌሎችም የርቀት ትምህርቶቸን በኢተርኔት ለማግኘት እና ለመማማር የሚያግዙ ድረገፆች 1. Adobe Connect 2. Blackboard Collaborate 3. WizIQ 4. LearnCube 5. BigBlueButton ፡ ይህ በተለይም ብዙዎች የሚመርጡት የመስመር ላይ መማሪያ ስርዓት ሲሆን፤ ሩቅ ላሉ ተማሪዎች ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት እንዲያገኙ በማስቻል የተለያዩ የትምህርት አይነቶችን በቪዲዮ እና ኦውዲዮ ማጋራት የሚያስችል ነው፡፡ ❖ከዛ ባለፈ በሃገራችን የካሽ ብር መያዝ ሳያስፈልግ ሂሳብ መክፈል የሚችሉባቸውን እነዚህን መንገዶች በሚቻለው ቦታ በመጠቀም ከበሽታው ራሳችንን መከላከል እንችላለን 1. M-birr 2. Amole 3. Helocash 4. Awash mobile # ጥንቃቄያችን ለህይወት ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🛑 በጣም ጠቃሚ መረጃ በቻይና ሰዎች የሰጧቸው ዋና ዋና ጠቃሚ ምክሮች:-📌 . #1. ሁለት አይነት ጫማ ይኑርዎት። አንዱ ከቤት ውጪ የሚጠቀሙበት ሲሆን ሌላኛው ቤት ውስጥ የሚጠቀሙበት ይሆናል። ከቤት ውጪ የሚጠቀሙበትን በፍጹም ወደ ቤት ውስጥ አያስገቡ። ቤት ውስጥ የሚጠቀሙበትን በፍጹም ወደ ውጪ አያውጡ። #2. አንድ የተለየ ጠረጴዛ ይኑርዎት። ከውጪ የሚገዟቸውን እቃዎች ለማኖር የሚያገለግል አንድ የተለየ ጠረጴዛ ይኑርዎት። ከውጪ የሚገዟቸውን እቃዎች በሙሉ ለምሳሌ እንደ መድሐኒት: መጠጦች: አትክልቶች እና ሌሎችንም ሳይነኩ ለ24 ሰዓት በጠረጴዛው እንዲቆዩ ያድርጉ። #3. በተቻለ መጠን የገንዘብ ኖቶችንም ሆነ ሳንቲሞችን አይስጡ: አይቀበሉ። የገንዘብ ኖቶችንም ሆነ ሳንቲሞችን ወደ ወደ ቤት የሚያመጡ ከሆነ ለዚህ ጉዳይ ለይተው ባስቀመጡት ጠረጴዛ ላይ ለ24 ሰዓት አቆይተው ይጠቀሙ። #4. ሁሉንም አይነት አትክልቶች ማለትም ቀይ ሽንኩርት: ነጭ ሽንኩርት: ድንች እና ሌሎችንም በፈላ ውሃ ሙልጭ አድርገው ይጠቡ። በፈላ ውሃ ሊታጠቡ የማይችሉ አትክልቶችን አይግዙ። #5. ከቤት ከወጡ በተቻለ መጠን የእጅ ስልክዎን ይዘው አይሂዱ። ይዘው ከወጡ ደግሞ ወደ ቤት ሲመልሱ በአልኮል ያጽዱ። #6. ከቤት ከወጡ በተቻለ መጠን የቤት ቁልፎችን ይዘው አይውጡ። ይዘው ከወጡ ደግሞ ወደ ቤት ሲመልሱ በአልኮል ያጽዱ። #7. ከቤት ወጥተው ሲመልሱ እጅዎንና ፊትዎን በሳሙና ይታጠቡ። ቤት እንደተመለሱ የለበሱትን ልብስ አውልቀው እንዲታጠብ ያድርጉ። #8. ሴት እህቶቻችን ከቤት ስትወጡ ጸጉራችሁ በአግባቡ መጠቅለሉን አረጋግጡ:: ጸጉራችሁን በእጃችሁ አትነካኩ:: ፊታችሁን ጸጉር በነካ እጃችሁ አትንኩ። #9. አትክልት ለመግዛት ሲሄዱ የእጅ ጓንት ያድርጉ። ወይም አትክልቶችን ሲያነሱ የፕላስቲክ ከረጢቶችን በሁለቱም እጅዎት ማጥለቅዎትን እርግጠኛ ይሁኑ። ወደ ቤት ሲመልሱ የእጅ ጓንትዎን ማጠብዎን አይዘንጉ። በፕላስቲክ ከረጢቶች ተጠቅመው ከሆነ ወደ ቤት ሲመልሱ ወይም ወዲያውን ከተጠቀሙ በኋላ ያስወግዱ። #10. ሁልጊዜ ከቤት ከመውጣትዎ በፊት ራስዎን እና የሚያመጧቸውን ነገሮች ደህንነት እንዴት መጠበቅ እንደሚችሉ ያቅዱና በቂ ዝግጅት ያድርጉ። #11. በጣም የግድ ካልሆነ በስተቀር ምግብ ወይም መድሐኒት ለመግዛት ባይሰለፉ ይመረጣል። መሰለፉ ደግሞ የግድ ከሆነ እስከ ሁለት ሜትር ርቀትዎን ይጠብቁ። #12. ከውሾች እና ድመቶች ጋር ያለዎትን ንክኪ ያስወግዱ። #13. በተቻለ መጠን አረጋውያን ወደ ውጪ ባይወጡ ይመክራል። ቤት ውስጥ ያሉ ወይም በአካባቢው ያሉ ሰዎች ለአረጋውያን የሚፈልጉትን ነገር ገዝተው ቢያመጡላቸው ይመክራል። #14. ሁልጊዜ ከቤትዎ ከመውጣትዎ በፊት ከላይ የተጠቀሱትን መልዕክቶች በመመልከት አቅደው ተግባራዊ ያድርጉ። ኮሮና ለመከላከል ከላይ የተባሉትን መተግበር! ምንጭ ፡ ድረ ገጽ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🛑 ‹‹በየቤታችሁ ጸልዩ📌›› - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን #ETHIOPIA | ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ 📌 በዓለም ላይ ተስፋፍቶ የቆየውና በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ኢትዮጵያ የገባው የኮረና ቫይረስ በሽታ ዕለት ዕለት እየተስፋፋ ጥቂት የማይባሉ ወገኖቻችን በወረርሽኙ መያዛቸው ታውቋል፡፡ በመሆኑም ይህ ወረርሽኝ እንዳይስፋፋና በቀጣይም ሌሎች ወገኖቻችን እንዳይያዙ መከላከሉ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ በመሆኑ ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ስብሰባ በማድረግ የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 1. በአሁኑ ጊዜ እየደረሰ ያለው የወረርሽኝ በሽታን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው ባለሙያዎች እየተሰጠ ያለውን የጤና አጠባበቅ ምክርና ትምህረት እንዲሁም በፍትህ መንፈሳዊ እንደተደነገገው ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት በማድረግ ወረርሽኑን ማስቆም እንዲቻል በመላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጣም በተወሰኑ ካህናት መንፈሳዊ አገልግሎቱ እንዲሰጥ ሌሎች ካህናትና ምእመናን ለጊዜው በየቤታቸው በጸሎት እንዲወሰኑ፣ በአገልግሎት ላይ ለሚገኙ አገልጋይ ካህናትም በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ እንዲወሰኑ ሆኖ አስፈላጊው ሠርከ ህብስት የምግብ አቅርቦት እንዲዘጋጅላቸው እንዲደረግ፣ እግዚአብሔር አምላካችን የሕዝቡን ሁሉ ምሕላና ጸሎት፣ የካህናቱን አስተበቊኦት በርኀራኄው ሰምቶ፣ በቅዱሳኑ ቃልኪዳን፣ በወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም አማላጅነት ቁጣውን በምሕረቱ መዓቱን በትግዕስቱ አሳልፎ ፍጹም ደህንነትን እንደሚሰጠን እያመንን ፡- 2. በአሁኑ ጊዜ የወረርሽኙን ፍጥነት ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት እንዳለ ሆኖ በቀጣይ በበሽታው እየተያዙ ለሚመጡ ወገኖቻችን ማቆያ ቦታ ማዘጋጀቱ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር ከአዲስ አበባ ጀምሮ በመላው አህጉረ ስብከት የሚገኙ፡- ሀ. መንፈሳዊ ኮሌጆች ለ. የካህናት ማሠልጠኛዎች ሐ. ዘመናውያን ት/ቤቶች አስፈላጊው ዝግጅት እንዲደረግላቸውና መሟላት የሚገባቸው ሁሉ ተሟልቶ ለሕሙማን ማቆያ እንዲውሉ ለማድረግ ወረርሽኙ እስከሚያበቃ ድረስ አገልግሎት መስጫ እንዲሆኑ የሚመለከተው አካል ተረክቦ እንዲያስተናግድባቸው ተወስኗል፡፡ 3. በአሁኑ ጊዜ በወረርሽኙ ምክንያት መንግሥት ሕሙማንና የተቸገሩ አካላትን ለመርዳት እያደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ከመንበረ ፓትርያርክ ለጊዜው ብር 3,000,000.00 (ሦስት ሚሊየን ብር) በመንግሥት ደረጃ ለተቋቋመው እርዳታ አሰባሳቢ በቤተ ክርስቲያናችን ስም እንዲሰጥ፣ 4. በቤተ ክርስቲያናችን ሥር ለሚገኙ የሕጻናትና ማሳደጊያ ቦታዎች የሚገኙ ሕጻናትን እና ችግረኞችን በምግብና በንጽሕና መጠበቂያ መደጐም የሚያስፈልግበት ጊዜ በመሆኑ አስፈላጊው ርዳታ የማሰባሰብ ሥራ እንዲሠራና እንዲረዱ በቤተ ክርስቲያናችን ሥር በተቋቋመው ተስፋ ግብረ ኃይል በኩል የማስተባበሩ ሥራ እንዲሠራ፣ 5. ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አሁን የያዝነውን የጾምና የጸሎት ጊዜ ምክንያት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ቅዳሴውን በመምራትና በመባረክ መቆየታቸውን ቋሚ ሲኖዶስ ተገንዝቧል፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ያለው ወረርሽኝ በእጅጉ እየተስፋፋ በመሆኑና የተለየ አባታዊ ጸሎትና ሱባኤ የሚያስፈልግ ሆኖ በመገኘቱ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ከዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለዓለም ሰላምና ለሕዝቦች ደህንነት ሲባል ለጊዜው ለብቻቸው በልዩ የጾምና የጸሎት የሱባኤ ጊዜ እንዲቆዩ ቋሚ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለማችንንና አገራችን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን ለሕዝባችንም ምሕረትንና ፈውስን ይስጥልን ! አሜን ! (ፎቶ: በዲ/ን ሙሉዓለም ዐሥራት) EOTC TV ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 29 ደረሰ! በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች መገኘታቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል። ባለፋት 24 ሰዓታት 68 የላብራ
በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 29 ደረሰ! በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች መገኘታቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል። ባለፋት 24 ሰዓታት 68 የላብራቶሪ ናሙና ምርመራ ተደርጎ ተጨማሪ 3 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተነገረ። አጠቃላይ ቁጥሩም 29 ደርሷል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

አስቸኳይ ሀገራዊ ጥሪ ሼር ይደረግ❗ በዓለም ላይ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ሀገራችን ውስጥ መከሰቱም ይታዎቃል፡፡ በመንግሥትና በበጎ ፍቃደኛ ሰዎች ወረርሽኙን ለመቆጣጠጠር ከፍተኛ
አስቸኳይ ሀገራዊ ጥሪ ሼር ይደረግ❗ በዓለም ላይ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ሀገራችን ውስጥ መከሰቱም ይታዎቃል፡፡ በመንግሥትና በበጎ ፍቃደኛ ሰዎች ወረርሽኙን ለመቆጣጠጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ሲሆን ወደፊት የወረርሽኙ ሁኔታ እየከፋ ከመጣ በርካታ የበጎ ፍቃድ ባለሙያዎችን ማሰማራት ስለሚጠይቅ፤ 1. በጤና ሙያ ተመርቃችሁ ወደ ሥራ ያልተሰማራችሁ 2. መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት የምትሰሩ የጤና ባለሙያዎች 3. በጡረታና በተለያዩ ምክንያቶች ከሥራ የተገለላችሁ የጤና ባለሙዎች (ለመደበኛ አገልግሎት) 4. የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን 5. የጤና ተማሪዎች (በመንግስትና በግል) ከመጋቢት 24 ቀን 2012 ጀምሮ ከዚህ በታች በተገለፀው የጤና ሚኒስቴር ድረ-ገፅ( http://www.moh.gov.et/ejcc/am/node/201 ) እንድትመዘገቡ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

2 ላብሪቶሪዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ጀመሩ! በአርማዎር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዮት እና በብሄራዊ የእንስሳት ጤና ምርመራና ጥናት ማዕከል የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተጀምሯል። ሁለቱ ተቋማት 4 አር
2 ላብሪቶሪዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ጀመሩ! በአርማዎር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዮት እና በብሄራዊ የእንስሳት ጤና ምርመራና ጥናት ማዕከል የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተጀምሯል። ሁለቱ ተቋማት 4 አርቲ ፒሲአር ማሽኖች በመጠቀም በቀን ውስጥ እስከ 400 የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንደሚያደርጉ ነው የተነገረው። ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ትራምፕ አሜሪካዊያን ከፊታቸው ለተደቀነው አስከፊ ጊዜ እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ተናገሩ፡፡ ሁኔታው እጅግ አሳስቦኛል ያሉት ትራምፕ መጪዎቹ ቀናቶች በስቃይ የተሞሉ መሆናቸውን አሳስበዋል፡፡በቀጣዮቹ ሳምንታት ውስጥ 2 መቶ ሺህ አሜሪካዊያንን ህይወት ሊያሳጣ እንደሚችል ዎርስንኢንግ የተሰኘ ተቋም ግምቱን አስቀምጧል፡፡ይህ በጣም አሰቃቂ እና በጣም ከባድ ህመም ለመግታትና እያንዳንዱ አሜሪካዊ ወደፊት ለሚጠብቀው አስቸጋሪ ቀን ዝግጁ እንዲሆን እፈልጋለሁ ብለዋል ማለታቸውን ሲ ኤን ኤን ዘግቧል። Via BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

መጋቢት 22፣2012 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ(1) ተጨማሪ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስትር ተናገረ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ ባካሄደው ተጨማሪ የላብራቶሪ ምርመራ አንድ (1)
መጋቢት 22፣2012 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ(1) ተጨማሪ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስትር ተናገረ። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዛሬ ባካሄደው ተጨማሪ የላብራቶሪ ምርመራ አንድ (1) በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው በማረጋገጡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ሃያ ስድስት (26) ደርሷል ተብሏል ፡፡ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ የ42 ዓመት የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሲሆን የአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ከመጀመሩ አስቀድሞ መጋቢት 9፣2012 ከአውስትራሊያ አዲስ አበባ እንዲሁም መጋቢት 10፣2012 ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ ተጉዟል፡፡ ግለሰቡ የበሽታው ምልክት በማሳየቱ በላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጧል፡፡ በአሁን ሰዓት ግለሰቡ በድሬዳዋ የለይቶ ህክምና መስጫ ማዕከል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በለይቶ ህክምና መስጫ ማዕከል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ያሉ ሃያ ሁለት (22) ታማሚዎች ሲኖሩ ሁለት ታማሚዎች በጽኑ ህሙማን ህክምና ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል። #ShegerWerewoch #COVID19Ethiopia #Ethiopia

#ሼህ_ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ! የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታት የተለያዩ ተቋማት እና ግለሰቦች ድጋፋቸውን ለአዲስ አበባ
#ሼህ_ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ! የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመግታት የተለያዩ ተቋማት እና ግለሰቦች ድጋፋቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያደረጉ ነው። በዚህም ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለከተማ አስተዳደሩ አድርገዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦ • ዛሬ በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች - 3 • በአሁን ጊዜ በለይቶ ማቆያ ያሉ ታማሚዎች - 21 • ፅኑ ህሙማን - 2 • ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ያገገሙ - 2 •
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦ • ዛሬ በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች - 3 • በአሁን ጊዜ በለይቶ ማቆያ ያሉ ታማሚዎች - 21 • ፅኑ ህሙማን - 2 • ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ያገገሙ - 2 • በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ድምር - 25 📌ማስታወሻ፦ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጡ 2 ታማሚዎች ወደሀገራቸው ተመልሰዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#stayHome 🚶‍♀...................🚶‍♂ #socialDistance 👉 @kalbelay ....share.....

#Coronavirus : በስፔን በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት 849 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። #BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በዓለም የጤና ድርጅት አማካኝነት የተሰጡ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19)ን የሚመለከቱ የምክር ሀሳቦች ፦ ➡️ የኮቪድ-19 ቫይረስ ሞቃታማ እና እርጥበት የአየር ጠባይ ባለባቸው አካባቢዎችም ሊተላለፍ ይችላል ➡️ በረዶዋማ እና ቀዝቃዛማ የአየር ጠባይ አዲሱን የኮሮና ቫይረስ ሊያጠፋ አይችልም። ውጫዊው የአየር ሁኔታ ምንም ይሁን ምን መደበኛው የሰውነታችን የሙቀት መጠን ከ 36.5 °C እስከ 37 °C ያህል ሆኖ ይቆያል ፡፡ ➡️ ሙቅ በሆነ ውኃ ገንዳ ውስጥ መዘፍዘፍም ከኮሮና ቫይረስ አይከላከልም። ይልቁንስ የሚመከረው ቶሎ ቶሎ እጅን በሳሙና እና ውኃ በደንብ መታጠብን ነው። ➡️ አዲሱ የኮሮና ቫይረስ በወባ ትንኝ ወይም ቢንቢ አማካኝነት ከአንድ ሰው ወደ ሌላኛው አይተላለፍም። በሽታው የሚተላለፈው በበሽታው የተያዘ ሰው በሚስል ወይም በሚያስነጥስበት አልያም ከአፉ እና ከአፍንጫው በሚወጡ እንደ ምራቅ የመሳሰሉ ፈሳሾች ነው። ➡️ የሰውነት ሙቀት መለኪያ መሣሪያዎች አንድ ሰው መደበኛ የሰውነት ሙቀቱ ከፍ ብሎ እንደው ለመለካት አገልግሎት ላይ ሊውሉ ይችላሉ። ይሁንና መሣሪያው በበሽታ የተያዘውን ሰው ለይቶ ማወቅ አይችልም። ምክንያቱም በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የትኩሳት ምልዕክት እስኪያሳዩ ከ 2 እስከ 10 ቀናት ሊወስድ ይችላል። ➡️ አልኮል ወይም ክሎሪን መላ ሰውነትን በመቀባት ሰውነት ውስጥ ዘልቆ የገባ ቫይረስን ለመከላከል አይረዳም። እንደዚህ አይነት ነገሮችን ሲጠቀሙ ደግሞ ዓይን እና አፍ ውስጥ እንዳይገቡ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ይሁንና አልኮል እና ክሎሪን ብዙ ሰዎች የሚነኳቸውን ወለሎች ለማፅዳት አገልግሎት ላይ ሊውሉ ይችላሉ። ➡️ የጉንፋን ወይም ሌሎች የመከላከያ ክትባቶች ከዚህኛው ቫይረስ ሊከላከሉ አይችሉም። ይህ ቫይረስ አዲስ እና ከሌሎች የተለየ ስለሆነ የራሱ ክትባት ያስፈልገዋል። ➡️ ጨዋማ የአፍንጫ ስፕሬ በመጠቀም የኮሮና ቫይረስን መከላከል አይቻልም። ይሁንና አልፎ አልፎ ይህንን የተጠቀሙ እና ጉንፋን የያዛቸው ሰዎች በቶሎ ሲሻላቸው ተስተውሏል። ➡️ ነጭ ሽንኩርት አንዳንድ ፀረ-ተሕዋስያን ሊኖረው የሚችል ጤናማ ምግብ ነው። ሆኖም ነጭ ሽንኩርት መብላት ሰዎችን ከአዲሱ የኮሮና ቫይረስ እንደሚከላከል የተረጋገጠ መረጃ የለም። ➡️ በየትኛውም የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሰዎች በአዲሱ የኮሮና ቫይረስ ሊጠቁ ይችላሉ። አዛውንቶች እና ቀደም ሲል እንደ አስም ፣ የስኳር በሽታ ፣ የልብ ህመም ያላቸው ሰዎች በቫይረሱ የበለጠ ተጋላጭ ሲሆኑ ይስተዋላል ፡፡ ➡️ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ኮሮናን አይከላከልም። አንቲባዮቲክስ የሚወሰደው ባክቴሪያን ለመከላከል እንጂ ቫይረንስ ለመከላከል አይረዳም። ይሁንና በኮቪድ 19 የተያዙ ሰዎች ተያያዥ የባክቴሪያ በሽታዎች ገጥሟቸው ከሆነ አንቲባዮቲክስ እንዲወስዱ ሊደረግ ይችላል። Via #DW ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#DrLiaTadesse የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች 25 ደረሱ! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks
#DrLiaTadesse የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች 25 ደረሱ! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም እንዲጀምር መደረጉን የክልሉ መንግስት ገለፀ። በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ውስጥ በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ተቋርጦ የ
🖍በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም እንዲጀምር መደረጉን የክልሉ መንግስት ገለፀ። በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ውስጥ በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም እንዲጀምር መደረጉን የክልሉ መንግስት ገለፀ። የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ፥ በአካባቢዎቹ የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም ወደ ስራ እንዲመለስ የክልሉ መንግስት እና የፌደራል መንግስት በጋራ ሲሰሩት የነበረው ስራ መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ምንጭ ፋና ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የ70 ዓመቱ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔትናሁ የኮሮና ቫይረስ የላብራቶሪ ውጤታቸው ነጻ(ኔጋቲቭ) መሆናቸውን አሳይቷል። ውጤቱ ነጻ መሆናቸውን ቢያሳይም ከጤና ሚንስትር ተጨማሪ ማረጋገጫ እ
የ70 ዓመቱ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔትናሁ የኮሮና ቫይረስ የላብራቶሪ ውጤታቸው ነጻ(ኔጋቲቭ) መሆናቸውን አሳይቷል። ውጤቱ ነጻ መሆናቸውን ቢያሳይም ከጤና ሚንስትር ተጨማሪ ማረጋገጫ እና ፈቃድ እስኪነገራቸው ራሳቸውን ለይተው ይቆያሉ። Via Sheger FM ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ! ...ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከተወሰደ ናሙና ውስጥ አንዲት ታካሚ ላይ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባት በመጀመሪያ የላብራቶሪ ምርመራ በመታወቁ ለህብረተሰቡ መ
የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ! ...ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከተወሰደ ናሙና ውስጥ አንዲት ታካሚ ላይ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባት በመጀመሪያ የላብራቶሪ ምርመራ በመታወቁ ለህብረተሰቡ መጋቢት 18 ቀን 2012 ዓ.ም በተሰጠው መግለጫ ማሳወቃችን ይታወቃል። ይህች 16ኛ ታማሚ የ24 ዓመት ኢትዮጵያዊት ስትሆን የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላት እንዲሁም በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ጋር ንክኪ ያልነበራት በመሆኑ በድጋሚ ሶስት ጊዜ በተደረገላት የላቦራቶሪ ምርመራ ሶስቱም ውጤት #ነጌቲቭ በመሆኑ በቫይረሱ አለመያዟን ማረጋገጥ ተችሏል። ይሁንና ወጣቷ የቆየ ተጓዳኝ የጤና ችግር ያለባት በመሆኑ የህክምና ክትትል እየተደረገላት ይገኛል። #DrLiaTadesse ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#Coronavirus CNC፣ CCTV፣ CGTN እና Xinhua የተባሉ የቻይና ሚድያ ጣብያዎችን ዛሬ ስከታተል እንዳየሁት በርካታ ቻይናውያን የጤና ባለሙያዎች ቫይረሱን ለመዋጋት በአለም ዙርያ እየተሰማሩ ነው! እነዚህ ቻይና ውስጥ በሚገርም ሁኔታ ቫይረሱን የተዋጉ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ከአሜሪካ እስከ ፓኪስታን እየዘመቱ ነው። የእርዳታ ተቀባይ ሀገራት መሪዎች አየር ማረፊያ ድረስ በመሄድ ለቻይናዎቹ ባለሙያዎች ተገቢ አቀባበል እያረጉ ነው። የቻይናን እርዳታ በዚህ ሰአት የማይፈልግ የለም። መንግስትም እነዚህ የጤና ባለሙያዎች ወደ ሀገራችን እንዲመጡ ጥሪ ቢያቀርብ መልካም አይመስላችሁም? Via #eliasmeseret

መጋቢት 21፣ 2012 የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በለይቶ መቆያ መወሰናቸው ተሰማ፡፡ ኔታንያሁ በለይቶ መቆያ የተወሰኑት የቅርብ አማካሪያቸው በኮሮና ቫይረ
መጋቢት 21፣ 2012 የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በለይቶ መቆያ መወሰናቸው ተሰማ፡፡ ኔታንያሁ በለይቶ መቆያ የተወሰኑት የቅርብ አማካሪያቸው በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በምርመራ ከተረጋገጠ በኋላ እንደሆነ ታይምስ ኦፍ ኢዝራኤል ፅፏል፡፡ ከምናልባትም በላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁንም ቫይረሱ ሳያገኛቸው አልቀረም ተብሏል፡፡ የኔታንያሁ አማካሪ ባለቤትም በቫይረሱ መያዛቸው ታውቋል፡፡ ኔታንያሁ ለ14 ቀናት ራሳቸውን ለይተው እንደሚሰነብቱ ተነግሯል፡፡ በእስራኤል እስከ ትናንት በስቲያ ምሽት 4 ሺ 247 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው እንደተመዘገበ መረጃው አስታውሷል፡፡ 15 ሰዎች ደግሞ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሞተዋል ተብሏል፡፡ #ShegerWerewoch #COVID19 #ኮሮና_ቫይረስ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks