ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Ir al canal en Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Mostrar más1 720
Suscriptores
-124 horas
-47 días
-1430 días
Archivo de publicaciones
Can't get enough poetry in your life?! Come on down to Pallet (near "Yugo Church", Bole) on Thursday for a night of connection with our friends at Spittoon!
https://facebook.com/events/s/spittoon-poetry-reading-night/591908678309967/?ti=as
አባ ዳኘው-አጤ ምኒልክና ባዕታ ማርያም
Jan 21, 2020
| Written by
ታመነ መንግስቴ
|
ታሪክ/ history
"አለ ወልድ አልነሳኝ
ስለቴን በከንቱ
የተገፋን ሰሚ
ባዕታ አለች እናቱ።"
ይች ስንኝ በወጣቱ የሙዚቃ ባለሙያ ዳን አድማሱ ዳምጠው "አራት ኪሎ" የተሰኘች አነጋጋሪ እና ቅኒያም ነጠላ ዜማ ውስጥ ያለች ናት።
ታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም እዚያው አራት ኪሎ ከግቢ ገብርኤል ከፍ ብላ ለእምየ ምኒልክ መታሰቢያ ትሆን ዘንድ በልጃቸውና በዘመኗ ኢትዮጵያን ንግስተ ነገስት ሆና ባስተዳደረቻት ዘውዲቱ ምኒልክ የተሠራች ናት።
የታላቁ ንጉስ ዓጤ ምኒልክ እና ባለቤታቸው የኢትዮጵያ ብርሃን -እቴጌ ጣይቱ ብጡል መቃብርም በዚችው ገዳም ነው።
ለዚህም ይመስላል ለዛሬው ትውልድ እንደ ማንቂያ ደወል የሚሆኑ፣እንደ ወይን ጠጅ የሚጣፍጡ የአባ ዳኘው-አጤ ምኒልክና ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ መልዕክቶች በአፀደ ገዳሟ በጉልህ ተፅፈው መነበባቸው።
እነሆ እንደ መነሻ፦አባ ዳኘው ጣሊያንን አፈር አስግጠው ካባረሩት በሗላ ስለ ህዝባቸው መዘመን አብዝተው ይጨነቁ ጀመር።ጠላታቸውን ያሸነፉት በበዛ የፈጣሪያቸው ድጋፍና በህዝባቸው ቀናኢነት እንጅ በተጠና የጦር ስልት፣በተለካ ጥበብ አለመሆኑን አሰቡ።እናም ዘመናዊ ትምህርትን ማስፋፋት የማይታለፍ ተግባራቸው መሆኑን አመኑ።እንዲህም አሉ።
"በጣም ወደ ሗላ የቀረን ህዝቦች ነንና፤ገና የምንሰራው ብዙ ስራ ስላለ ወጣቶቻችንን ማስተማር አለብን።"
ይሁንና አባ ዳኘውን እንዲህ ያሳሰባቸው የትምህርት ጉዳይ ከድፍን ምዕተ ዓመት(100ዓመት) በሗላም እንደነበረ አለ። ይሄን ያስተዋለው ዳን አድማሱ "በአራት ኪሎ" ዘፈኑ፦
"የአውራ ዶሮ ቁንጮ ስሙ ነው ኮኮን
ስንቱ ቆቡን ጫነ ያልተማረውን።"
እያለ የትምህርታችንን ውድቀት ያሽሟጥጠዋል።
እምየ ምኒልክ ተዓምር በሰሩባት አገር ያላቸው የህይወት ገመድ መመንመኑን እየተረዱ ነው።ሞት ብዙ ጊዜ ድል ያደረጉትን ንጉስ ሊወስዳቸው እየመጣ ይመስላል።እሳቸውም በዓለም የሚፀፀቱበት የለምና በፀጋ ተቀብለውታል ፤ግን በተጋደሉላት አገራቸው ኢትዮጵያ ከእሳቸው ህልፈት በሗላ የሚመጣው የስልጣን ሽኩቻ ለዳግም አድዋ ዳርጓት ኢትዮጵያን እንዳያሳጣ ይሰጋሉ።ስለሆነም መኳንንቱን ሰብስበው እንዲህ ሲሉ የመሰናበቻ መልዕክታቸውን አደረሡ፦
"እኔ እስካሁን በፍቅር እንዳኖርሗችሁ እናንተም በፍቅር ተስማምታችሁ እንድትኖሩ እለምናችሗለሁ።"
የምኒልክ ልጅ ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱም ምንም እንኳን ታሪካቸው በብልጣብልጡ እንደራሴያቸውና የሗላው ንጉሰ ነገስት ተፈሪ መኮነን የተጋረደ ቢመስልም በአገራቸው ጉዳይ የዋዛ ሴት አይደሉም።
በታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ያለው ነፍስ አለምላሚ መልዕክታቸው ይሄን ይመስላል፦
"መሪዎች በቤተ-መንግስት ቢቀመጡ፣ህዝቡም በየግል ቤቱ ቢቀመጥ መጠለያ ይባላል፤እንጅ የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ ናት!"
ሁሉንም መልዕክቶች አራት ኪሎ ከቤተ-መንግስቱ በስተ ምስራቅ ካለችው የታዕካ ነገስት ባዕታ ለማርያም ገዳም ቅጥር ግቢ አገኘሗቸው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ይቆየን!
Copyright ©2020 All rights reserved | This site is owned by NConsults
ብርዕ – በደም ዕንባ / ሙሉጌታ ተስፋዬ
በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ጥራና
ባፅሜ ቀሰም ብርዕ
በህይወት ማቅለሚያው
ጠርቤ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
የራሴ ጉልቻ … አንገቴ አለ ዘምበል
የደም ወዜ ጠለል … እንባዬ አለ ከምበል
በሞት ሞት ጣረሞት … <በልቤ ልብ በል!>
ሥጋት አንድውጋት
ነፍሴን ሲሰንጋት
በቅኔ እንቆቅልሽ … ቁልቁል ተቆልፌ
በእምነት … እምም እመ-እዝነት
በህልም ዓለም ሽምጥ ግልቢያ ተሰልፌ
ለሥጋ ታርቄ
ለገላ መርቄ
እርቃኔን ወጥቼ – ግቤኔን አስጥቼ
የጎኔን ጨረስኩት – ሆዴን ስሸነግል
ለነገ ራሴ ስንቅ – ልቃንጣዬ አገልግል።
ካምና ከታች አምናው
የጉልበት የጤናው
ቢታይ ሁለንተናው – <ሁሉ> ሁለመናው
የልቤ ልብ በል – ለልቤ ሲጠናው
ብቻ ላይኔ ብቻ – ላይኔ ለብረቱ – ላይኔ ብቻ ቀናው!
ለታይታ ለዝናው …
በሰው ፊት በሸንጎ ለወግ ማ’ርግ ዝናው!!
አዎ! በኔው ‘ኔ ጥራና
በኔው ‘ኔ ብራና
በብርዔ ስለቁጥ
የኑሮን ሽቁጥቁጥ
ደም እንባ – ደም እንባ – እንበለ እንባ ደም
ሕይወት እንጉርጉሮ – በአትም አይታደም።
(ለሚንቁኝ – ለማያውቁኝ)
29/7/84
ባለቅኔ ሙልጌታ ተስፋዬገ(አያ ሙሉ የወሎ አበጋር ወድ አለቃ ጅብ አይበላሽ)
🦋🦋👇🦋🦋
https://telegram.me/sufafel
✅🦋👆🦋✅
✍🦋 ሙሌዋ ✍ 🦋
🦋
እኛ ቤት ሴት አለ
በአባዎች አለም እነ እማ ባቆሙት
መኩሪያዋ እልፍ ነው የሶስት ወንዶች እናት
የሶስት ወንዶች እናት
በወንዱም በሴቱም አለም እየገባች
ጾታዋን ተሻግራ ሁሉን እያሳየች
ወንድ ልጆችዋ ውስጥ ሴትነትን አየች
እኔ ትንሹ ነኝ የመጨረሻው ልጅ
ቃጭሌን አንቃጭላ ዱብ ያደረገችኝ
ይህ ቃጭል ሲንቃጨል
አባቴ ደስ አለው ወንድ ልጅ ሲደገም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልብ እንጂ ሴት አልተወለደም
ሴትነት ውስጤ አለ
ተፈጥሮ ከእናቴ ተማክረው የዘሩት
ቤተሰብ ከመንደር ተባብረውም ቢያጥሩት
በሰብዓዊ ለዛ የማሰቢያ ጥጌ
አጼ ሆኜ ሳለሁ ያረገኝ እቴጌ
ሴትነት ውስጤ አለ
የአንደበቴ አራሚ የኔነቴ አንዱ መልክ
የጉልበቴ ሚዛን የሰውነቴም ልክ
እወቀው አባቴ እወቀው ወንድሜ አንተም ውስጥ እኔም ውስጥ ሴትነት አለልክ
ይህን እጹብ ጸጋ ወንድሞቼ ስተው
እማዎች ባጸኑት መኖሪያ አለማቸው
አባ ሆነው ቀሩ ልክ እንደአባታቸው (የት አባታቸው)
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ!’ . . .
እኔ ግን ‘ወንድ ነኝ’ ብዬም የማልፎክር
በሴታዊ ገጼም ከቶም የማላፍር
ሴትነት ወንድነት ቅኝቴ ውስጥ የለም
ሰው መሆን ዜማዬ ለሁለቱም ቀሰም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ሴታሴት ልቤ እንጂ ሴት አልተወለደም
እነ እማ ባጸኑት በዚህ የእኛ ቤት አለም
ወንዳወንድ ቀልቧ እንጂ ወንድ እናት አልሆነም
የተገደበ እንባ ኤሌትሪክ አልሰጠም
በአባቴ አዛኝነት ቤታችን አልሞተም
በኔ ቡና ማፍላት ጎረቤት አልሳቀም
ምክንያቱም . . .
የሶስት ወንዶች እናት ወንዶች ውስጥ ሴት እንጂ ሴት አልወለደችም
እነ እማ ባቆሙት በአባዎች አለም
እኛ ቤት ሴት አለ እኛ ቤት ሴት የለም
ሰይፈ ተማም 2011
በልብ የቀበሩት
አይኖቿ ሲሰርቁኝ፤ እኔም ሰርቄያቸዉ፣
ምኞቴን አርግዤ፤ ትግል ገጠምኳቸዉ፣
የሚሸነፍ ጠፍቶ፤ ተዉ ሺሸኝ…! አልሸሽም…!
እንዳዉ ስንባባል፣
የጊዜ መቁጠሪያ፤ ለካ ጥሎን ሄዷል፡፡
በሱለይ አደም
ጦቢያ ግጥምን በጃዝ
📅 102ኛውን ፕሮግራም ዛሬ ረቡዕ ጥር 6/2012 በ11፡30
📍 ራስ ሆቴል
🙏 @Ribki
መግቢያ 100 ብር ብቻ
@eventsethiopia
Day 1 of our 31 Days of Poetry! Check out Rob Haile's beautiful piece, "Living Tribute"! https://youtu.be/rE06WYe4uPM
አደረች አራዳ አደረች አራዳ
የኔ ብርቱካኔ የኔ ፅጌረዳ
(የጌታነህ ልጅ ©)
አደረች አራዳ አደረች አራዳ
የኔ ብርቱካኔ የኔ ፅጌረዳ
አንቺ የኔ አበባ የብርቱካን ፍሬ
ማደሩን እደሪ
ብትከርሚም ክፍት ነው አይዘጋም በሬ
እኔ ጌታ አይደለሁ
ዘይትሽ አልቋል ብዬ ፊቴን አላዞርም ፊትሽን እያየሁ
እጠብቅሻለሁ
ባደርሽበት ነግቶ ማለዳን እያየሁ
አበባዬ ፅጌ
እሾህ የወረረሽ ከቀለምሽ ግርጌ
እንዴት ዓይኔን ልክደን
ያደርሽበት ወዳጅ እሱ እኔን አይደለ
በቀለምሽ ድምቀት...
አይገባው ይሆናል እንደተታለለ
አሳዘነኛ
አንድ እኔ አለሁ አይደል?
በቀለምሽ ድምቀት...
አውቄ 'ምታለል!?
የብርቱካን ልጣጭ ውስጡን ግጬ በላሁ
አዳርሽ አስግቶኝ ደጅ ደጁን እያየሁ
አዳርሽ እንዴት ነው አንቺ ፅጌረዳ
ደስ ብሎሽ አነጋሽ? ንገሪኝ ልረዳ
እ?
ተይ ተይ
ተይ አትመልሺልኝ አትበይኝ ስ**
ነገ እንድጠብቅሽ ደጅ ደጁን እያየሁ
ይቅር አትንገሪኝ ይቅር ብዬሻለሁ
እስክትመለሺ
ድንግዝግዙ ጠዋት ሌቱ ከሰዓት ነው!
----_----_----_----_----_----_----_----
ታህሳስ 19: 2012
ሰላም ሰላም ቤተሰብ!
ግጥማዊ ቅዳሜ በሚቀጥለው ወር ሀገር አቀፍ ይሆነ የግጥም ውድድር ለማካሄድ አቅዷል። ስለሆነም በክልል ከተሞች የምትገኙ የግጥም ቤተሰቦች ከተሞቻችሁን ወክላ/ሎ የምትወዳደር/የሚወዳደር አንድ ገጣሚ መርጣችሁ ብትልኩልን ደስ ይለናል..... ጥበብ እየተጣራች ነው ፣ አቤት በሉ!!!
እስካሁን ድረስ የሚከተሉት ከተሞች ተወካዮቻቸውን ልከውልናል!
- ባህር ዳር
- ሀዋሳ
- ጂማ
- ድሬዳዋ
- ጎንደር
- አዳማ
ሌሎቻችሁ ደሞ እስከ ሰኞ ታህሳስ/20/2012 ድረስ በፌስቡክ ወይም በቴሌግራም ገፆቻችን ሹክ በሉን።
Are you ready for a throw down?! It's time for the third installment of Poetic Saturdays' Poetry Slam in the evening of Saturday, December 21st! Winner takes prize and the traveling notebook...
Want to sign up?! Message us!
Come experience the truth of some of your favorite poets at Addis Tavern (formerly La Lyonnaise) behind Sheger Building, Bole. https://www.facebook.com/events/2640363339376592/
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
