es
Feedback
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ

የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ

Ir al canal en Telegram

ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ

El canal የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ (@abuhyder) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 990 suscriptores, ocupando la posición 5 361 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 100 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 990 suscriptores.

Según los últimos datos del 17 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -42, y en las últimas 24 horas de -5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.40%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer día suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 18 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 990
Suscriptores
-524 horas
+367 días
-4230 días
Archivo de publicaciones
ወደ ገጠር ለሚጓዙ ወንድምና እሕቶች

ወደ መርየም የተላከው መልአኩ ጂብሪል ነው ወይስ ሌላ?

አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላህ እነዚህን ወንድሞች ትምህርታቸውን በቲክቶክ ፎሎው በማድረግ ተከታተሏቸው። በአላህ ፈቃድ ተጠቃሚ ትኾናላችሁና

ኢህሳን ፋውንዴሽን በጎ አድራጎት ድርጅት በትላንትናው እለት በአዳማ ከተማ በተከታታይ ለ11ኛ ዓመት የመልካምነት ፕሮግራም አካሄደ። ኢህሳን ፉውንዴሽን ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ 1)በየ አመቱ በጣም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 1,500 አባወራዎችን ሙሉ የረመዳን ኢፍጣር እና ስሁር በመለገስ እነዚህ ቤተሰቦች ስለምግብ ሳይጨነቁ ከሌላው ህብረተሰብ እኩል ረመዳንን በኢባዳ እንዲያሳልፉ በማገዝ 2)በየ ወሩ በተከታታይ ሳይቋረጥ 35 አባ ወራ እጅግ አቅመ ደካማ እና ጠዋሪ ላጡ ወላጆች እና የቲም ልጆች ሙሉ ወርሃዊ አስቤዛ በማቅረብ የሚረዳ 3)በየ ሳምንቱ ጁሙዓ በተለያዩ መስጂዶች በመዘዋወር 300 ለሚሆኑ ለምስኪኖች የምገባ ፕሮግራም ያካሄዳል በተጨማሪም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍል በሚፈጠሩ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ላይ የአልባሳት :ምግብ እና ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ይለግሳል:: በተጨማሪም ሁሉም ወደ ማይቀረው አኼራ መሸኛ የሚሆን ዘመናዊ የጀናዛ ማጠቢያዎችን በመስራት የሚያስረክቡ ሲሆን እነዚህን እና ሌሎች ኸይር ስራዎችን ለመስራት እና በቀጣይነት ለፉውንዴሽኑ ቋሚ ገቢ የሚያስገኝ ህንፃ ለመጀመር የምያግዛቸውን የገቢ ማሰባሰቢያ አንድ አካል የሆነ ፕሮግራም በአዳማ ከተማ አከናውነዋል:: ይህ ፉውንዴሽን የቡዙዎቻችን ግዴታ የሆኑትን ወላጆች ,ልጆች እና እህቶችን እንባ የሚያብስ ተቋም ሲሆን ሁሉም የመንግስት አካል ,የተለያዩ ተቋማቶች,እና አላህ አቅሙን የሰጠው ሰው ሁሉ የሁላችንም ግዴታ መሆኑን አውቀን በምንችለው ሁሉ ልናግዛቸው ልናበረታታቸው ይገባል የሚል መልዕክቴን ማስተላለፍ እወዳለሁ::

አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ልጅ ረያን አብዱልከሪም አሊዪ AML የሚባል አጣዳፊ የደም ካንሰር ህክምና ታክሞ በማገገም ላይ እያለ ድጋሜ ያገረሸበት በመሆኑ የመቅኒ ቅያሬ ህክምና ለመዳን ብቸኛ አማራጭ መንገድ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በመሆኑም ይህ ህክምና ሀገር ውስጥ የሌለ በመሆኑ ወደ ውጪ ሀገር ሄዶ ህክምናውን እንዲከታተል በሜዲካል ቦርድ ተወስኗል :: በመሆኑ የምትችሉትን ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ ቤተሰቦቹ ጥሪ ያቀርባሉ:: ድጋፍ ለማድረግ የጎፈንድሚ ሊንክ https://gofund.me/5dc21ab6 አካውንት Abdulkerim Aliyi Haji Comertial bank of ethiopia 1000440849036 Awash Bank 01320157558300 Absinia 34482357 Oromia Coporative 1075100075079

ዐሹራእ ደረሰ በአቡ ሀይደር አሰላሙ ዐለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡ #ዐሹራእ ምንድነው? ዐሹራእ ማለት (የሙሐረም ወር) አስረኛው ቀን ማለት ነው፡፡ አሁን ያለንበት ወር ሙሐረም አንደኛው ወር ተብሎ ይጠራል፡፡ #ይህ ወር ክብር ያለው ወር ነው አቢ ሁረይራህ(ረዲየላሁ ዐንሁ) ከነቢያችን(ዐለይሂ ሶላቱ-ወስ-ሰላም) እንዳስተላለፈልን የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል፡- "ከረመዷን ቀጥሎ ከጾሞች ሁሉ በላጩ የአላህ ወር የሆነው ሙሐረም ነው" (ሙስሊም 2812)፡፡ ከሙሐረም ወር ውስጥ ደግሞ አስረኛው የዐሹራእ ቀን በላጭ ቀን ነው፡፡ #ለምን ይጾማል? ዐብደላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ አሉ፡- "የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና ሲገቡ አይሁዶችን በዐሹራእ ቀን ሲጾሙ አገኟቸው፡፡ ይህን ቀን የምትጾሙት ለምንድነው? ብለው ሲጠይቋቸው፡ እነሱም፡- ይህ ታላቅ ቀን ነው! አላህ ሙሳንና ተከታዮቹን ከፊርዐውንና ሰራዊቱ በማዳን እነሱን በባሕር ያሰጠመበት ቀን ስለሆነ ሙሳም ለአላህ ምስጋናን ለማድረስ ጾሞታል እኛም እንጾመዋለን ብለው መለሱ፡፡ የአላህ መልክተኛውም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ፡- ለሙሳ (ወዳጅነት) ከናንተ ይልቅ እኛ የቀረብንና የተገባን ሰዎች ነን እኮ! በማለት እሳቸውም ጾሙት ሶሓባዎቻቸውንም እንዲጾሙ አዘዙ" (ሙስሊም 2714)፡፡ ከዛ በፊት ግን በመካ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዐሹራእን ይጾሙ ነበር ነገር ግን ማንንም አላዘዙም፡፡ #ጥቅሙስ ምንድነው? አቢ ቀታዳህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተናገረው የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የዐረፋ ቀን ጾም አላህ ዘንድ ያለፈውንና የሚመጣውን (የሁለት) ዓመት (ትናንሽ) ኃጢአቶችን ያስምራል፣ የዐሹራእ ቀን ጾም ደግሞ ያለፈውን አንድ ዓመት (ትናንሽ) ኃጢአት ያስምራል" (ሙስሊም 1976)፡፡ ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ(ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ አለ፡- የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የዐሹራእን ቀን የጾሙና ሶሓቦቻቸውን ያዘዙ ጊዜ፡- "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህን ቀን እኮ አይሁዶችና ክርስቲያኖች ያከብሩታል ሲሏቸው፡ እሳቸውም፡- በቀጣዩ ዓመት አላህ ካደረሰን ዘጠነኛውን ቀን እንጾማለን አሉ፡፡" (ሙስሊም 2722)፡፡ በሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ "ከ(ዐሹራእ) ቀን ከፊቱ ወይም ከኋላው አንድን ቀን ጹሙ" ብለዋል (አሕመድ የዘገቡት)፡፡ ያ ዓመት ሳይደርስ የአላህ መልክተኛ ከዚህ ዓለም ተለዩ፡፡ የኢስላም ሊቃውንትም ከዚህ ሐዲሥ በመነሳት የሁዳዎችን ላለመመሳሰል ዘጠነኛውንም ቀን ጨምሮ መጾም ነቢያዊ ሱንና መሆኑን ገለጹ፡፡ #መጾሙ ዋጂብ ነው ወይስ ሱንና? የዐሹራእን ቀን መጾም ሑክሙ ሱንና ነው፡፡ በሒጅራ 2ኛው ዓመት የመጀመሪያው ወር ሙሐረም ላይ ስለነበር የተደነገገው የረመዷን ጾም እስኪደነገግ ድረስ ዋጂብ ነበር፡፡ ከ7 ወር በኋላ ግን በሒጅራ 2ኛው ዓመት 8ኛው ወር ሻዕባን ላይ የረመዷን ጾም ግዳጅነት ሲደነገግ፡ ዐሹራእ ግዳጅነቱ ተሰረዘ፡፡ ይህን በተመለከተ ቀጣዩ ሐዲሥ እንዲህ ይላል፡- እናታችን ዓኢሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡- "የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ረመዷን ሳይደነገግ በፊት ዐሹራእን ይጾሙ ነበር፡፡ ካዕባም የሚሸፈንበት ቀን ነበር፡፡ አላህ ረመዷንን በደነገገበት ጊዜ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- የፈለገ ሰው (ዐሹራእን) ይጹመው ለመጾም ያልፈለገ ደግሞ ይተወው" (ቡኻሪይ 1489)፡፡ #መቼ እንጀምር? የሙሐረም አስረኛው ቀን(ዐሹራእ) የፊታችን ቅዳሜ ነው የሚውለው፡፡ ስለዚህ አላህ ወፍቆት ይህን ዐሹራእን መጾም የፈለገ ከአራቱ መንገዶች አንዱን መርጦ ይጹም፡- ሀ. ቅዳሜን ብቻ፡- 10ኛውን ቀን መጾም ማለት ነው፡፡ ዋናው ዐሹራእ ተብሎ የሚጠራውም ይህ ቀንነው፡፡ ለ. ጁምዓና ቅዳሜን ፡- 9ኛውንና 10ኛውን ቀን መጾም ማለት ነው፡፡ ይህም በላጭ ነው፡፡ ሐ. ከ ጁምዓ-እሁድ ፡- 9ኛ፣10ኛና 11ኛውን ቀን ማለት ነው፡፡ ይህ ከሁሉም በላጩ ነው፡፡ መ. ቅዳሜና እሁድ፡- 10ኛውና 11ኛውን ቀን መጾም ማለት ነው፡፡ ይህም ሱንና ነው አላህ ይወፍቀን፡፡ #ስምንቱ የፆም ቀናት አላህ ፆምን ያገራለትና የወፈቀው ሰው ደግሞ ከፈለገ በተከታታይ ለስምንት ቀናት መፆም ይችላል፡፡ እንዴት ካሉም፡- ሀሙስ፡- ይህ 8 ኛው ቀን በራሱ የሱንና ፆም ቀን በመሆኑ ይፆማል ማለት ነው፡፡ ከጁምዓ-እሁድ ፡- እነዚህ ሶስት ቀናት የሙሐመረም 9ኛ 10ኛና 11ኛ ቀናት ስለሆኑ፡ ከዐሹራእ ፆም ጋር በተያያዘ መልኩ ይፆማሉ ማለት ነው፡ ሰኞ፡- ይህ 12ኛው ቀን በራሱ የሱንና ፆም ቀን በመሆኑ ይፆማል ማለት ነው፡፡ ማክሰኞ -ሀሙስ ፡- እነዚህ ሶስት ቀናት የሙሐረም 13ኛ 14ኛና 15ኛ ቀናት ናቸው፡፡ አያሙል-ቢድ በመባልም ይጠራሉ፡፡ የወሩን ሶስት ቀናት በነዚህ ቀናት መፆም በላጭ ነው፡፡ Click and Like ➤➤ http://fb.com/Ustaz.Abuhyder

እንኳን ለ 1,446ኛው የዒዱል ፊጥር በዓል አላህ በሰላም አደረሳችሁ! ጌታ አላ ህ ዒዱን የደስታ የምስጋናና የዚክር ያድርግልን ዒዱኩም ሙባረክ!! ተቀበለሏሁ ሚንና ወሚንኩም

ጠቃሚ የፊቂህ ትምህርቶች ክፍል 19 በዑስታዝ አቡሐይደር

ጠቃሚ የፊቂህ ትምህርቶች ክፍል 18 በዑስታዝ አቡሐይደር

ጠቃሚ የፊቂህ ትምህርቶች ክፍል 17 በዑስታዝ አቡሐይደር