es
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Ir al canal en Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Mostrar más
El país no está especificadoLa categoría no está especificada
446
Suscriptores
+124 horas
+197 días
+6730 días
Archivo de publicaciones
#ሂደት ( #process ) በውስጡ ያለፈውን ነገር በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ሰርቶ ወደ አንድ ግብ ማድረሱና ቅርፅ ማስያዙ ስለማይቀር በሕይወታችን፣ በውሎአችን፣ በጊዜያችን ስለምናልፍበት ሂደ
#ሂደት ( #process ) በውስጡ ያለፈውን ነገር በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ሰርቶ ወደ አንድ ግብ ማድረሱና ቅርፅ ማስያዙ ስለማይቀር በሕይወታችን፣ በውሎአችን፣ በጊዜያችን ስለምናልፍበት ሂደት ልብ ብለን ልናስብ፣ ልንጠነቀቅ፣ እንዲሁም ለመንፈሳዊ ሰው እድገት የሚበጀውን ሂደት ልንመርጥ ይገባል። ምክንያቱም #ሂደት ለመገንባትም ሆነ ለመፍረስ አይቀሬ ማለፊያ ነው። መቼም የክርስቲያን መንፈሳዊ እድገት፣ ለውጥ፣ ተሐድሶ ዱብዳ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጋር የመቆየት፣ የጸሎት፣ በእግዚአብሔር ቃልና በመንፈስ ቅዱስ የመሰራት ውጤት ነውና በዚህ አንድን መንፈሳዊ ሰው በሚሰራ ሂደት ውስጥ ራሳችንን ማቆየት፣ ማሳለፍና መስራት ተገቢ ነው። የተሐድሶ ባለቤት አዳሹ እግዚአብሔር ቢሆንም ለመታደስ ደግሞ የእኛ ለእርሱ መገኘት ወሳኝ ነው!! ነገ ብለን ለምናስበው ኑሮአችን ዕቅድ ከያዝን ቀዳሚው ዕቅዳችን ከእግዚአብሔር ጋር ብዙ የመሰንበት፣ ፊቱን የመፈለግ ይሁን፤ ምክንያቱም ተሐድሶ፣ እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት በዛ ሂደት ውስጥ አለ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 February 11, 2024

#ልብን_በእግዚአብሔር_ማስመርመር! ስምዖን ጴጥሮስ ከኢየሱስ ጋር በነበረው ግንኙነት ጌታን ከመውደዱ፣ ለጌታ ከመቆርቆሩ፣ ያንተን ክፉ ለእኔ ያድርገው፣ እኔ አለውልህ ከማለቱ፣ ኢየሱስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ከመመስከሩና ከአንተ ወደ ማን እንሄዳለን አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ ከማለቱ በተጨማሪ፤ ከችኩልነቱና ከክህደቱ ባለፈ "ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ" የሚለውን የኢየሱስን ቃል የረሳው እስኪመስል ድረስ፤ ኢየሱስ ከሞተ፣ ከሞት ከተነሣ፣ ለእነርሱም ተገልጦ ራሱን ካሳያቸውና “ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እኔን እንደ ላከኝ፣ እኔም እናንተን እልካችኋለሁ” ካላቸው በኋላ እንደገና ዓሣ ወደ ማጥመድ መመለሱ፣ ለራሱ መሄዱ ሳያንስ ሌሎቹንም አስከትሎ የኢየሱስ ትኩረት ባልሆነው ዓሣ ፍለጋ ላይ መሰማራቱ ይስተዋላል። በጴጥሮስ መሪነት ጴጥሮስና አብረውት የነበሩት ዓሣ ፍለጋ ወጥተው ወደ ጀልባ ቢገቡም በዚያ ሌሊት ግን ምንም አላጠመዱም። ሲነጋም ምንም እንኳን ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስ መሆኑን ባያውቁትም ኢየሱስ ግን በባህሩ ዳርቻ ቆሞ ይመለከታቸው ነበር፤ የፈለጉትንም ዓሣ እንዳላገኙ ባስተዋለ ጊዜ ሊሸከሙት ከሚችሉት በላይ፣ አትረፍርፎ አሸከማቸው፤ ከፈለጉት በላይ ብዙ ዓሣ ተሸክመው ተመለሱ። በዚያ ስፍራ የኢየሱስ ዋና ትኩረት ዓሣ ፍለጋ ሌሎቹን አስከትሎ የወጣውን ጴጥሮስን በብዙ ዓሣ የመባረክ፣ ጊዜያዊ ረሃባቸውን ዓሣ በመስጠት ማስታገስ ሳይሆን ፍለጋ የወጡትን ዓሣ ሳይነፍጋቸው፤ በክህደት የተናወጠውን፣ ስፍራውን ለቆ የሄደውን የጴጥሮስን ልብ መመርመር፣ መፈተን፣ ሐሳቡን ማወቅ፣ እንደገና ወደ ስፍራው መመለስ፣ እንደገና ሸክምና ዐደራን መስጠትና " #ተከተለኝ ” ብሎ እንደገና ወደ ራሱ መሳብ ነበር። ኢየሱስ ጴጥሮስን "ትወደኛለህን?" ብሎ በተደጋጋሚ በመጠየቁ ጴጥሮስ ቢያዝንም “ጌታ ሆይ፤ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንደምወድህም ታውቃለህ” በማለት መልሱን ለኢየሱስ ሲተውለት፤ ኢየሱስም ለዐደራ አይበቃም ይሆን? ብሎ ሳይጠረጥረው ይልቁንም "ጠቦቶቼን መግብ" ፣ "በጎቼን ጠብቅ" ፣ "በጎቼን መግብ" በማለት ትልቅ ዐደራ በመስጠት ከሃዲ የነበረውን ጴጥሮስን እንደገና በኋላው ሲያስከትለው እናያለን። (ዮሐንስ 21፥1-22) ሳጠና እና ሳሰላስል ስለ ሁሉን አዋቂው አምላክ የሚናገረው የዳዊት መዝሙር (መዝሙር 139) ላይ ያለ አንድ ቃል ወደ ልቤ መጣ፦ "²³ እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ፤ ፈትነኝ፤ ሐሳቤንም ዕወቅ፤ ²⁴ የክፋት መንገድ በውስጤ ቢኖር እይ፤ በዘላለምም መንገድ ምራኝ።" ---መዝሙር 139 (አዲሱ መ.ት) ሁሉን አዋቂው እግዚአብሔር ስለ እኛ የማያውቀው አንዳች ነገር የለም፤ ከመንፈሱ ወዴትም መሄድ፣ ከፊቱም ወዴትም መሸሽ አንችልም፤ የልባችንን ሐሳብ ገና ከሩቁ ያስተውላል። ስለዚህ ልባችንን ዘወትር በፊቱ ማቅረብ፣ ማስመርመር ያስፈልገናል። ምክንያቱም የክፋት መንገድ በውጣችን ቢኖር፣ ልክ እንደ ጴጥሮስ ስተን የእርሱ ትኩረት ያልሆነን ነገር ፍለጋ፣ ልናጠምድ ያልተገባንን ነገር ለማጥመድ ብንወጣ የልባችን አምላክ የሆነው እርሱ እንደገና ወደ ሐሳቡ ይመልሰናል፣ " #ተከተለኝ" ብሎ ከፊት ቀድሞ በኋላው ያስከትለናል፤ እንደገና ሸክም ይሰጠናል፤ በዘላለምም መንገድ ይመራናል!! 📌(ዮሐንስ 21፥1-22) ✍️ መክሊት አየለ 📆 August 19, 2024

#ሙሉ_ምርመራ #ሙሉ_ምርመራ የማይገልጠውን በልባችን የተሰወረ ህመም እግዚአብሔር መመርመር፣ መግለጥ፣ ማከም፣ መፈወስና ማዳን ይችላል። የሰው (የእኛ) ልብ እጅግ ክፉ፣ ተንኮለኛና አሳች ከመሆኑ የተነ
#ሙሉ_ምርመራ #ሙሉ_ምርመራ የማይገልጠውን በልባችን የተሰወረ ህመም እግዚአብሔር መመርመር፣ መግለጥ፣ ማከም፣ መፈወስና ማዳን ይችላል። የሰው (የእኛ) ልብ እጅግ ክፉ፣ ተንኮለኛና አሳች ከመሆኑ የተነሳ ክፋቱ አይደለም ለሌሎች ሰዎች ለእኛ ለራሳችን እንኳን ሳይቀር ጠንቅ ነው። ሰው የሥጋ (አካላዊ) በሽታ ቢይዘው በሞያው የተካኑ በተባሉ ሀኪሞች #ሙሉ_ምርመራ ይደረግለታል፤ እንደየ ሕመሙ አይነት የተሰወረ በሽታው የመገኘትና መድኃኒት የማግኘት ዕድሉም ሰፊ ነው። #ልቡ ፣ የውስጥ ማንነቱ ቢታመም ግን መርማሪው፣ አካሚው ፈዋሹም #አንዱ_እግዚአብሔር_ብቻ_ነው። ስለዚህ በየጊዜው፦ #ልብን_በእግዚአብሔር_ማስመርመር፦ ምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለን ለማወቅ፣ ከእግዚአብሔር አሳብ ኮብልለን ከሆነ ወደ ስፍራችን፣ ወደ አሳቡ ለመመለስ፣ በእግዚአብሔር ታምኖ እና በእርሱ ላይ ተጣብቆ ለመቆየት እጅግ ፍቱን መድኃኒት ነው። ይህን ጽሁፍ ልብን በእግዚአብሔር ስለ ማስመርመር እያሰላሰልኹ፣ ከዚህ ቀደም የጻፍኹትን አንድ ጽሁፍ መለስ ብዬ እያየሁ ጻፍኹ። ዛሬም፦ የክፋት መንገድ በውጣችን ቢኖር፣ ልክ እንደ ጴጥሮስ ስተን የእርሱ ትኩረት ያልሆነን ነገር ፍለጋ፣ ልናጠምድ ያልተገባንን ነገር ለማጥመድ ብንወጣ የልባችን አምላክ የሆነው እርሱ እንደገና ወደ ሐሳቡ ይመልሰናል፣ " #ተከተለኝ" ብሎ ከፊት ቀድሞ በኋላው ያስከትለናል፤ እንደገና ሸክም ይሰጠናል፤ በዘላለምም መንገድ ይመራናል!! እላለሁ። ልባችንን በልባችን አምላክ ማስመርመር፣ መመለስ ይሁንልን!!

Amharic_Gospel_songs_kiristina_ክርስትና_by_Haramaya_University_fellowship.m4a5.46 MB

🔥 COMING SOON ON HOP MINISTRY 🔥 “The Martyr of Catacomb” — a powerful story of faith, courage, sacrifice, and eternal hope.
🔥 COMING SOON ON HOP MINISTRY 🔥 “The Martyr of Catacomb” — a powerful story of faith, courage, sacrifice, and eternal hope. Step into the world of the early believers who chose Christ above fear and stood firm in the midst of persecution. This inspiring story will strengthen your faith and encourage you to live the Word of God daily. 📖 Hear. Obey. Practice. 📍 Inspired by Luke 11:28 Join us and be part of this journey of transformation! 📘 Facebook: https://www.facebook.com/hopministry10 📢 Telegram: https://t.me/hopministry10 #HOPMinistry #HearObeyPractice #Faith #ChristianStory #ComingSoon #Luke1128

መጽሐፍ ቅዱስ እስትንፋሰ መለኮት ከመሆኑ የተነሳ የአንድን ሰው ሕይወት እንከን ሳያስቀር፣ እንደወደደ አድርጎ ሰርቶ ፍጹም፣ ብቁ፣ ለእግዚአብሔር የተገባ እና ለመልካም ስራ ሁሉ የተዘጋጀ አድርጎ ማቅረብ ይችላል!! በምንም ሊቀየርና ሊሰራ ያልቻለ ሕይወት የእግዚአብሔር መንፈስ አለባቸውና በቅዱሳት መጻሕፍት ይሰራል!! ሊሰራን፣ ሊያነጻን፣ ሊቀድሰን ከሚችለው ከእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ጋር መጣበቅ ይሁንልን!!! 2ኛ ጢሞቴዎስ 3 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለባቸው ናቸው፤ ለማስተማር፣ ለመገሠጽ፣ ለማቅናት በጽድቅም መንገድ ለመምከር ይጠቅማሉ፤ ¹⁷ ይኸውም የእግዚአብሔር ሰው ለመልካም ሥራ ሁሉ ብቁ ሆኖ እንዲገኝ ነው።

#ከእግርህ_ሥር_መሆን_@pastortesfayegabisoofficia3543128k.m4a2.87 MB

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. 🌿 Devotionals • Revival Histories • Biographies • Testimonies Based on Luke 11:28 📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10 📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶¹ ገዦች ያለ ምክንያት አሳደዱኝ፤ ልቤ ግን ከቃልህ የተነሣ እጅግ ፈራ። ¹⁶² ትልቅ ምርኮ እንዳገኘ ሰው፤ በቃልህ ደስ አለኝ። ¹⁶³ ሐሰትን እጠላለሁ፤ እጸየፋለሁ፤ ሕግህን ግን ወደድሁ። ¹⁶⁴ ጻድቅ ስለ ሆነው ሕግህ፤ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለሁ። ¹⁶⁵ ሕግህን የሚወዱ ብዙ ሰላም አላቸው፤ ዕንቅፋትም የለባቸውም። ¹⁶⁶ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ተስፋ አደርጋለሁ፤ ትእዛዝህንም እፈጽማለሁ። ¹⁶⁷ ነፍሴ ምስክርነትህን ትጠብቃለች፤ እጅግ እወደዋለሁና። ¹⁶⁸ መንገዴ ሁሉ በፊትህ ግልጽ ነውና፣ ሕግህንና ምስክርነትህን እጠብቃለሁ። … ¹⁶⁹ እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴ ከፊትህ ይድረስ፤ እንደ ቃልህም ማስተዋልን ስጠኝ። ¹⁷⁰ ልመናዬ ከፊትህ ይድረስ፤ እንደ ቃልህም ታደገኝ። ¹⁷¹ ሥርዐትህን አስተምረኸኛልና፣ ከንፈሮቼ ምስጋናን አፈለቁ። ¹⁷² ትእዛዛትህ ሁሉ የጽድቅ ትእዛዛት ናቸውና፣ አንደበቴ ስለ ቃልህ ይዘምር። ¹⁷³ ትእዛዝህን መርጫለሁና፣ እጅህ እኔን ለመርዳት ዝግጁ ይሁን። ¹⁷⁴ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ናፈቅሁ፤ ሕግህም ደስታዬ ነው። ¹⁷⁵ አመሰግንህ ዘንድ በሕይወት ልኑር፤ ሕግህም ይርዳኝ። ¹⁷⁶ እንደ ጠፋ በግ ተቅበዘበዝሁ፤ ትእዛዛትህን አልረሳሁምና፣ ባሪያህን ፈልገው።

4_5859299221059934155.mp36.54 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵³ ሕግህን አልረሳሁምና፣ ሥቃዬን ተመልከት፤ ታደገኝም። ¹⁵⁴ ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤ እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ። ¹⁵⁵ ሥርዐትህን ስለማይሹ፣ ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው። ¹⁵⁶ እግዚአብሔር ሆይ፤ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤ እንደ ሕግህ ሕያው አድርገኝ። ¹⁵⁷ የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ ብዙዎች ናቸው፤ እኔ ግን ከምስክርህ ዘወር አላልሁም። ¹⁵⁸ ቃልህን አይጠብቁምና፣ ከዳተኞችን አይቼ አርቃቸዋለሁ። ¹⁵⁹ መመሪያህን እንዴት እንደምወድ ተመልከት፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ። ¹⁶⁰ ቃልህ በሙሉ እውነት ነው፤ ጻድቅ የሆነው ሕግህም ዘላለማዊ ነው።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴⁵ እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ እጮኻለሁና መልስልኝ፤ ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ። ¹⁴⁶ ወደ አንተ እጣራለሁና አድነኝ፤ ምስክርነትህንም እጠብቃለሁ። ¹⁴⁷ ትረዳኝ ዘንድ ጎሕ ሳይቀድ ተነሥቼ እጮኻለሁ፤ ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ። ¹⁴⁸ ቃልህን አሰላስል ዘንድ፣ ዐይኔ ሌሊቱን ሙሉ ሳይከደን ያድራል። ¹⁴⁹ እንደ ቸርነትህ መጠን ድምፄን ስማ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ሕግህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ። ¹⁵⁰ ደባ የሚያውጠነጥኑ ወደ እኔ ቀርበዋል፤ ከሕግህ ግን የራቁ ናቸው። ¹⁵¹ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ቅርብ ነህ፤ ትእዛዛትህም ሁሉ እውነት ናቸው። ¹⁵² ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው፣ ከጥንት ምስክርነትህ ተረድቻለሁ።

የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዲሆን፦ እንደዚህ አይደረግም፣ እንደዚህ ደግሞ ይደረጋል የሚለው፣ የሚመክረው፣ የሚያስተምረው፣ የሚገስጸው፣ ልቡንም የሚያቀናው፣ የሕይወቱ መመሪያ የእግዚአብሔር ቃል ነው። “ #ጒልማሳ_መንገዱን_እንዴት_ያነጻል? #በቃልህ_መሠረት_በመኖር_ነው።” እንደሚል ቅዱስ ቃሉ ያለ መርህና መመሪያ ያልተወን እግዚአብሔር ይመስገን። ከፊታችን ጨለማ ተጋርዶ እግሮቻችን ሊሰናከሉ በቀረቡ ጊዜ ሕጉ ለእግራችን መብራት፣ ለመንገዳችንም ብርሃን ይሆነናል። ቃሉን ተመልክተን ሕይወት፣ አካሄድ፣ ለእግዚአብሔር መኖርን እንቀስማለን፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ ይረዳናል እንጂ አያሳስተንም። የማይዋሽ፣ እውነት የሆነ፣ ያለንበትን ሁኔታ ገልጦ የሚያሳይ የእግዚአብሔር ቃል ፊት ሰው በመስተዋት ራሱን አይቶ እንከኑን መሠወር እንደማይችል፤ የእኛ ሁለንተናም የተራቆተ ነው። ነገር ግን ሰድቦ ለሰዳቢ እንደሚሰጥ ሰው ሊያሸማቅቀን ሳይሆን፤ ሊያነጻንና ሊቀድሰን የተጋ፣ የሚሰራ ሕያው ቃል ነው። እግዚአብሔር ሆይ በቃልህ ውስጥ እንጥፋ፣ በቃልህ ውስጥ እንሰወር፤ ደግሞ በቃልህ ውስጥ እንገኝ፣ በቃልህ ውስጥ ሕይወት እናግኝ። ጌታ ሆይ እኔ በአንተ ከተጠመድኹ፣ ወደ ልቤ ለማስገባት፣ በልቤም ለመሰወር ቃልህን ካጠመድኹ፤ ለዓለም የመገኘት፣ በሥጋ ሥራ የመጠመድ እድል አይኖረኝምና አቤቱ መሰማሪያዬ ቃልህ፣ አንተ ያለህበት ሁሉ ይሁን። አሜን!!

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³⁷ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ ፍርድህም ትክክል ነው። ¹³⁸ ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤ እጅግ አስተማማኝም ነው። ¹³⁹ ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ ቅናት አሳረረኝ። ¹⁴⁰ ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ ባሪያህም ወደደው። ¹⁴¹ እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤ ነገር ግን መመሪያህን አልዘነጋሁም። ¹⁴² ጽድቅህ ዘላለማዊ ጽድቅ ነው፤ ሕግህም እውነት ነው። ¹⁴³ መከራና ሥቃይ ደርሶብኛል፤ ነገር ግን ትእዛዝህ ደስታዬ ነው። ¹⁴⁴ ምስክርነትህ ለዘላለም የጽድቅ ምስክርነት ነው፤ በሕይወት እኖር ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።

"ታሪክ ሰንቀው የያዙ፤ በስምም በቁጥርም የበዙ፤ ብዙ መጽሐፎች አውቃለሁ፤ ሁሉም ግን የአንድ ሰሞን ነው፤ የኔ ግን መጽሐፍ ቅዱሴ፤ ያወራል ስለ ኢየሱሴ፤ ለዚህ ነው ሁሌ የማነበው፤ ጎህ ሲቀድ ማለዳ አዲስ ነው፤ ትናንትን ስገረም ስደነቅ፤ በርቶልኝ ብዬ እንደርሱ የለም፤ ለዛሬም ሌላ እውነት አለው፤ የማይለመድ ሁሌ እንግዳ ነው።" ✍️ - ሳሙኤል ተገኝ

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹²⁹ ምስክርነትህ ሁሉ ድንቅ ነው፤ ስለዚህ ነፍሴ ትጠብቀዋለች። ¹³⁰ የቃልህ ትርጓሜ ያበራል፤ አላዋቂዎችንም አስተዋዮች ያደርጋል። ¹³¹ ትእዛዝህን ናፍቄአለሁና፣ አፌን ከፈትሁ፤ አለከለክሁም። ¹³² ስምህን ለሚወዱ ማድረግ ልማድህ እንደሆነ ሁሉ፣ ወደ እኔ ተመልሰህ፣ ምሕረት አድርግልኝ። ¹³³ አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤ ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ። ¹³⁴ ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣ ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ። ¹³⁵ በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ ሥርዐትህንም አስተምረኝ። ¹³⁶ ሕግህ ባለመከበሩ፤ እንባዬ እንደ ውሃ ይፈሳል።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹²¹ ፍትሕና ጽድቅ ያለበትን ሠርቻለሁ፤ ለሚጨቍኑኝ አሳልፈህ አትስጠኝ። ¹²² ለባሪያህ በጎነት ዋስትና ሁን፤ እብሪተኛ እንዲጨቍነኝ አትፍቀድላቸው። ¹²³ ዐይኖቼ ማዳንህን፣ የጽድቅ ቃልህን በመጠባበቅ ደከሙ። ¹²⁴ ለባሪያህ እንደ ምሕረትህ መጠን አድርግ፤ ሥርዐትህንም አስተምረኝ። ¹²⁵ እኔ ባሪያህ ነኝ፤ ምስክርነትህን ዐውቅ ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ። ¹²⁶ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕግህ እየተጣሰ ነውና፣ ጊዜው አንተ የምትሠራበት ነው። ¹²⁷ ስለዚህ ከወርቅ፣ ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ፣ ትእዛዛትህን ወደድሁ። ¹²⁸ መመሪያህ ሙሉ በሙሉ ልክ ነው አልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹³ መንታ ልብ ያላቸውን ጠላሁ፤ ሕግህን ግን ወደድሁ። ¹¹⁴ አንተ መጠጊያዬና ጋሻዬ ነህ፤ ቃልህን በተስፋ እጠብቃለሁ። ¹¹⁵ የአምላኬን ትእዛዛት እጠብቅ ዘንድ፣ እናንት ክፉ አድራጊዎች፣ ከእኔ ራቁ። ¹¹⁶ እንደ ቃልህ ደግፈኝ፤ እኔም ሕያው እሆናለሁ፤ ተስፋዬም መና ቀርቶ አልፈር። ¹¹⁷ ያለ ሥጋት እቀመጥ ዘንድ ደግፈህ ያዘኝ፤ ሥርዐትህንም ዘወትር እመለከታለሁ። ¹¹⁸ መሰሪነታቸው በከንቱ ነውና፣ ከሥርዐትህ ውጭ የሚሄዱትን ሁሉ ወዲያ አስወገድሃቸው። ¹¹⁹ የምድርን ክፉዎች ሁሉ እንደ ጥራጊ አስወገድሃቸው፤ ስለዚህ ምስክርህን ወደድሁ። ¹²⁰ ሥጋዬ አንተን በመፍራት ይንቀጠቀጣል፤ ፍርድህንም እፈራለሁ።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰⁵ ሕግህ ለእግሬ መብራት፣ ለመንገዴም ብርሃን ነው። ¹⁰⁶ የጽድቅ ሕግህን ለመጠበቅ፤ ምያለሁ፤ ይህንኑ አጸናለሁ። ¹⁰⁷ እጅግ ተቸግሬአለሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ። ¹⁰⁸ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈቅጄ ያቀረብሁትን የአፌን የምስጋና መሥዋዕት ተቀበል፤ ሕግህንም አስተምረኝ። ¹⁰⁹ ነፍሴ ዘወትር አደጋ ላይ ናት፤ ሕግህን ግን አልረሳሁም። ¹¹⁰ ክፉዎች ወጥመድ ዘረጉብኝ፤ እኔ ግን መመሪያህን አልተላለፍሁም። ¹¹¹ ምስክርነትህ የዘላለም ውርሴ ናት፤ ልቤ በዚህ ሐሤት ያደርጋልና። ¹¹² ትእዛዝህን ለዘላለም፣ እስከ ወዲያኛው ለመፈጸም፣ ልቤን ወደዚያው አዘነበልሁ።

Yehywete Memeria.mp35.05 MB