en
Feedback
Temary Education Hub

Temary Education Hub

Open in Telegram

💡ይህ ቻናል ለHighschool ተማሪዎችን የሚያግዝ እና ለጥሩ ውጤት የሚያበቃ ቻናል ነው ። ✨ለትምህርት የሚያስፈልጉ Material ✨ለተማሪዎች ምክር እና ልምድ ልውውጥ ✨ትምርህት መረጃዎች ይለቀቅበታል።

Show more
1 045
Subscribers
-324 hours
-177 days
-7630 days
Posts Archive
ውድ የ Temary Education ቤተሰቦች በ 2018 የ entrance exam ተፈትናችሁ የ university መግቢያ ውጤት ያላመጣችሁ በድጋሚ entrance ለመፈተን ያሰባችሁ አላችሁ ?

የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!   በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡   የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም   የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇 https://student.ethernet.edu.et/   የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።   @TemaryEducation_2018

የቻይንኛ ቋንቋ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሊሰጥ ነው! 🇨🇳📚 ከመስከረም 2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። 📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦ • የመምህራን ዝግጅት፦ ትምህርቱን የሚያስተምሩ መምህራንን ከቻይና ለማስመጣት እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ። • የዓላማው ግብ፦ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤታማ እንዲሆኑና የውጭ ሀገር የትምህርት ዕድሎችን በተሻለ ሁኔታ እንዲጠቀሙ ለማስቻል ነው። • ተጨማሪ ቋንቋዎች፦ ከቻይንኛ በተጨማሪ ሌሎች ዓለም አቀፍ ቋንቋዎችንም የማጠናከር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል። 💬 የእርስዎ አስተያየት፦ በትምህርት ቤቶች የቻይንኛ ቋንቋ መሰጠቱ ለተማሪዎች ምን ያህል ይጠቅማል ብለው ያስባሉ? ሀሳብዎን በኮሜንት ያጋሩን! 👥 መረጃው ለተማሪዎችና ወላጆች እንዲደርስ ሼር (Share) ያድርጉ! 🏳️join : @TemaryEducation_2018

#Remedial result የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ 250 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (5 የትምህርት አይነቶች) እና 200 ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (4 የትምህርት አይነቶች) መሆኑ ታውቋል። @TemaryEducation_2018

☺️ውድ የ TEH ቤተሰቦች 2018 አመቱ እንዴት አለፈላችሁ ?

#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። @TemaryEducation_2018

እንዲህ ይቻላል እንዴ! 🤯
እንዲህ ይቻላል እንዴ! 🤯

እድሜው 66 ነው 46 ያልነውን በስህተት ነው

በደቡብ ትግራይ በ46 ዓመታቸው የ12ኛ ክፍል ፈተናን የተፈተኑ የባንክ ጥበቃ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ውጤት ማምጣታቸው ተገለጸ በደቡብ ትግራይ ስለዋ ወረዳ በአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዴላ
በደቡብ ትግራይ በ46 ዓመታቸው የ12ኛ ክፍል ፈተናን የተፈተኑ የባንክ ጥበቃ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ውጤት ማምጣታቸው ተገለጸ በደቡብ ትግራይ ስለዋ ወረዳ በአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዴላ ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ የሚገኙት የ46 ዓመቱ አቶ ሰይፉ ተስፋይ ካህሳይ፣ የዕድሜና የሥራ ጫና ሳይገድባቸው ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት በ2018 ዓ.ም በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 320.25 በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ውጤት አምጥተዋል። የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሓጎስ መዝገበ እና የሥራ ባልደረቦቻቸው በአቶ ሰይፉ አስደናቂ ጽናትና ስኬት የተሰማቸውን ታላቅ ኩራት የገለጹ ሲሆን፣ ለመጪው የከፍተኛ ትምህርት ጉዟቸውም መልካም ተመኞታቸውን አስተላልፈዋል። @TemaryEducation_2018 🏳️

የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኑ። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል። በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ያሳውቃል። ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ሁልጊዜ ትክክለኛ የትምህርት ምዘናናነ ፈተናዎች መረጃን ለማግኘት የትምህርት ምዘናና ማህበረዊ ትስስር ገጾችን ይከታተሉ። https://eaes.et https://web.facebook.com/eaes.eaes http://www.youtube.com/@eaes.ethiopia https://x.com/eaesEt

Social Science Congrats!
Social Science Congrats!

Congratulations 🎉
Congratulations 🎉

photo content
+1

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ምን አሉ ? (የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ) - የዘንድሮው ውጤት ከአምናው በጥሩ ደረጃ ተሻሽሏል። - ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርስቲ አስገብቶ ማስፈተን በተጀመረበት የመጀመሪያ አመት ያለፉ 3.2% ፣ በሁለተኛው 2.9% ፣ በሶስተኛው 5.2% ፣ በአምናው አራተኛው ዓመት 8.9% ደረሰ አሁን በአምስተኛው ዓመት 12.8% ነው ያለፉት። - ዘንድሮ በ2018 ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ተማሪ ቁጥር 563,960 ሲሆን  550,210 ተማሪ ነው የተፈተነው። - ፈተናውን ያለፈው ተማሪ ብዛት 70,544 ነው። - ከተፈጥሮ ሳይንስ 16.6% አልፈዋል። ከማህበራዊ ሳንይስ 8.3% አልፈዋል። #በፐርሰንት - ክልሎች ካስፈተኗቸው ተማሪዎች ምን ያህል ተማሪ አሳለፉ ? (ያሰፈተኗቸው ተማሪዎች ቁጥር ይለያያል) 1. አዲስ አበባ 32.3% 2. ሀረሪ 22.67% 3. አፋር 15.6% 4. አማራ 15.56% 5. ድሬዳዋ 11.29% 6. ትግራይ 11.2% 7. ኦሮሚያ 10.53% 8. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 9.23% 9. ሶማሌ 9.2% 10. ሲዳማ 6.95% 11. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 6.12% 12. ደቡብ ኢትዮጵያ 5.82% 13. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 4.92% 14. ጋምቤላ 3.74% በቁጥር ምን ያህል ተማሪ ከየክልሉ አለፉ ? (ያስፈተኑት ቁጥር ይለያያል) 1. ኦሮሚያ ➡ 20,807 ተማሪዎች 2. አዲስ አበባ ➡ 18,646 ተማሪዎች 3. አማራ ➡ 15,225 ተማሪዎች 4. ትግራይ ➡ 3,146 ተማሪዎች 5. ደቡብ ኢትዮጵያ ➡ 3,011 ተማሪዎች 6. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ➡ 2,800 ተማሪዎች 7. ሲዳማ ➡ 1,827 ተማሪዎች 8. ሶማሌ ➡ 1,616 ተማሪዎች 9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ➡ 835 ተማሪዎች 10. አፋር ➡ 705 ተማሪዎች 11. ሀረሪ ➡ 599 ተማሪዎች 12. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ➡ 457 ተማሪዎች 13. ድሬዳዋ ➡ 410 ተማሪዎች 14. ጋምቤላ ➡ 280 ተማሪዎች - ባለፈው ዓመት ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች 1,232 ነበሩ ዘንድሮ ምንም ተማሪ ያላሳለፉ 565 ናቸው። - ከዚህ ቀደም ምንም ተማሪ ካላሳለፉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በኮፒዩተር ፈተና ወደ 4,500 ተማሪዎች አልፈዋል። ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች በክልል ምን ያህል ናቸው ? • ኦሮሚያ 156 • አማራ 98 • ደቡብ ኢትዮጵያ 86 • ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 69 • ትግራይ 48 • ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 29 • ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 22 • አፋር 21 • ሲዳማ 16 • ሶማሌ 9 • ድሬዳዋ  5 • ሀረሪ 3 • ጋምቤላ 2 • አዲስ አበባ 1 - ሁሉንም ያስፈተኑትን ተማሪዎች ያሳለፉ 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ባለፈው አመት 62 ነበሩ ዘንድሮ 88 ሆነዋል። በክልሎች ምንም ያህል ትምህርት ቤቶች 100% አሳለፉ ? • ኦሮሚያ 37 • አዲስ አበባ 24 • አማራ 8 • ደቡብ ኢትዮጵያ 4 • ትግራይ 4 • ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 3 • ሲዳማ 2 • አፋር 1 • ድሬዳዋ 1 • ሀረሪ 1 • ሶማሌ 1 • ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 1 - በኮምፕዩተር እና በወረቀት በተፈተኑ ተማሪዎች መካከል ያለው የማለፍ ምጣኔ ትልቅ ልዩነት አለው። ኦንላይ የተፈተኑ 18.3% አልፈዋል። በወረቀት የወሰዱ 4.2% ናቸው ያለፉት። አንዱ ቶሎ በወረቀት ከመፈተን መውጥቶ ኦላይን ለመስጠት እቅድ አለው 60% ነው ዘንድሮ ቀጣይ አመት 100% ኦንላይን ሁሉንም። - የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት ስንት ነው ? • በተፈጥሮ ሳይንስ • 🥇 ከወንድ 👉 591/600 ኦዳ ስፔሻል ቦርንዲግ ትምህርት ቤት አዳማ 🥇 ከሴት 👉 583/600 ከአገው ምድር ትምህርት ቤት እንጅባራ • በማህበራዊ ሳንይንስ • 🥇 ከወንድ 👉  576/600 ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት 🥇 ከሴት 👉 569/600 አዲስ አበባ ቦሌ ሱፐርሆሊሴቪየር ትምህርት ቤት -  ስልክ ይዘው የገቡ 265 ተማሪዎች ከፈተናው ተሰርዘዋል። - ኮምፒዩተር ላይ ባለ " ኢሬጉላተሪ " ተብለው ጉዳያቸው እየተጣራ ያለ አለ። - ከዚህ በፊት ከነበረው መሻሻል እየታየ ስለሆነ በጣም ደስተኞች ነን። - ዘንድሮም ወደ ሬሜዲያል የሚገቡ ተማሪዎች ይኖራሉ። - ሬሜዲያል ሁሌ የሚኖር አይደለም። በሚያልፈው ተማሪ ብዛት ነው የሚወሰነው። ዘንድሮ 70 ሺህ ተማሪ ስላለፈ ዘንድሮ ሬሜዲያል የሚገባው ይቀንሳል። 📌 ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ሰኞ ወይም ከነገ ወዲያ ማክሰኞ ጀምሮ ውጤታቸው ማየት ይችላሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎች ውጤት የሚመለከቱባቸውን አማራጮች ተከታትሎ ያቀርባል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia 🏳️join : @TemaryEducation_2018

ቀጣይ 595+ ግድ ይላል
2018 ከፍተኛ ውጤት Natural Science 591.6 / 600 ወንድ 583 / 600 ሴት Social Science 576 / 600 ወንድ 569 / 600 ሴት እንኳን ደስ አላቹ
የካሊድ ዉጤት ላይ ጭራሽ ሊደረስበት አይችልም ብለዉ ለሚያምኑት ሼር አድርጉላቸዉ።

ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
ውጤት መቼ ይታያል ? ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ። በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia @TemaryEducation_2018

ሰላም guys እንዴት ናችሁ 2018 የ12 ክፍል Entrance Exam የፈተናችሁ ተማሪዎች ጥያቄ? አለኝ የምትሉ Comment ላይ ጥያቄዎቻችሁን ፃፋልን ሁሉንም አንድ ላይ አርገን አንመልስላችኋለን።

ራስህን የምትቀይርበት ወርቃማ ጊዜ! ☀️📖 የሁለት ወራት የክረምት እረፍት ለተማሪዎች ዝም ብሎ ጊዜ የሚያሳልፉበት ሳይሆን ራሳቸውን በአዲስ መልክ የሚገነቡበት ወርቃማ አጋጣሚ ነው። ብዙ ተማሪዎች ይህንን ጊዜ በጨዋታና በምቾት ብቻ ሲያሳልፉ፣ አንተ ግን ራስህን በማብቃት መስከረም ላይ ወደ ትምህርት ገበታ ስትመለስ "ሌላ ሰው" ሆነህ መገኘት ትችላለህ። ለዚህም ኢንተርኔትንና ዩቲዩብን እንደ ግራፊክስ ዲዛይን፣ ኮዲንግ ወይም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ያሉ አዳዲስ ክህሎቶችን ለመቅሰም በመጠቀም የወደፊት አቅምህን ማሳደግ ይኖርብሃል። ከትምህርት ቤት መጽሐፍት ውጭ ያሉ የሳይኮሎጂ፣ የታሪክና የግል እድገት መጽሐፍትን በማንበብም አእምሮህን ማሳልና ሰፊ እውቀት መገብየት ትችላለህ። ከእውቀት ጎን ለጎንም ለአካላዊና ለመንፈሳዊ ዝግጁነትህ ትኩረት መስጠት እጅግ አስፈላጊ ነው። በየቀኑ መጠነኛ አካላዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ጤናህን መጠበቅና ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ምን ማሳካት እንደምትፈልግ አሁኑኑ ግልጽ እቅድ ማውጣት ይኖርብሃል። በተለይም ቀደም ባለው ዓመት ደካማ የነበርክባቸውን ትምህርቶች በቀን ለአንድ ሰዓት ያህል በመከለስ ክፍተቶችህን መሙላት ትችላለህ። እነዚህ ስልሳ ቀናት ወይ ይገነቡሃል ወይም ያባክኑሃል፤ ስለዚህ ዛሬ በዝምታ የምታፈሰው ላብና የምታደርገው ጥረት ነገ በታላቅ ውጤት እንዲከፍልህ ጊዜህን በአግባቡ ተጠቀም። © 2026 @TemaryEducation_2018

🏫 ሁላችሁም ወደ University ብታልፋ ምን አይነት Department ትመርጣላችሁ ? 👇

ያጋራናችሁን መረጃ ላላመናችሁ ይሄንን Vidio ተመልከቱ ፈተና በ AI የሰሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  ውጤታቸው 100% ይሰረዛል።  ይሄ ሚታወቅበት የራሳችንን አሰራር  ዘርግተናል ብለዋል:: የትምህርት  ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጸሀፊ።  join us : @TemaryEducation_2018