ቬነስያ
Open in Telegram
ይህ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች የተለያዩ አስተማሪና ጣፋጭ ታሪኮች እና ልዩ መልእክቶች የሚተላለፉበት ገጽ ( ቻናል ነው)። ለጥያቄዎ @Abipru1
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
1 750
Subscribers
+124 hours
+537 days
+42530 days
Posts Archive
1 750
ማደግ ላጠፋችሁ..!
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
እስኪ ወደ ኋላ መለስ በሉና ያንን የልጅነት ዘመናችሁን አስታውሱት። ያኔ ለዝማሬ የነበራችሁ ንጹሕ ቅንዓት፣ ጠበል ለመጠመቅ የነበራችሁ ወደር የለሽ ትጋት ትዝ ይላችኋል? በተለይ በሩፋኤል የጠበል ዕለት፣ ብርዱና ዝናቡ ሳይበግራችሁ፣ ኃፍረታችሁን ከልብሳችሁ ጋር አውልቃችሁ ጥላችሁ በእምነት ስትጠመቁ፣ የክርስቶስን ሥጋና ደም ለመቀበል በጉጉት ስትጋፉ የነበረው ያ የንጽሕና ዘመን እንዴት ይረሳል?
ያ የሰንበት ትምህርት ቤት ደማቅ አገልግሎታችሁስ እንደዋዛ ተረሳ? "ማርያም ፊደል"፣ "ያከብርዋ ለሰንበት"፣ "ይዌድስዋ መላእክት" እያላችሁ በህብረት የዘመራችሁት ዝማሬ፣ የሰራችኋቸው መንፈሳዊ ትያትሮች፣ በመድረክ ላይ ቆማችሁ ያቀረባችሁት ያ ማራኪ ሥነ-ጽሑፍ ከህሊናችሁ ጠፋ?
"እምዬ ማርያም ምን ሆናለች፣ አንገቷን ደፍታ ታለቅሳለች..." እያላችሁ በጨዋታ መዝሙሮች እየተጫወታችሁ፣ ልባችሁ ተነክቶ አብራችሁ ያነባችሁበት ያ ጊዜስ ተዘነጋችሁ አይደል?
ሁሉን ብትረሱት እንኳ በመስቀል እና በቅዱሳን ስዕላት አሸብርቃችሁ፣ እንደ ዐይን ብሌን ስትሳሳሉላት የነበረችው ያቺ የመዝሙር ደብተራችሁ ዛሬ የት ደርሳ ይሆን? አቧራ ጠጥታ ይሆን ወይስ የሆነ ጥግ ተወርውራ?
ኧረ እንደው በዚያ የልጅነት ኃያልና ጥርት ባለ ድምፃችሁ፤ "አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ..." ብላችሁ በዜማ የደገማችሁት ያ ጣፋጭ የግዕዝ ጸሎትስ?
ይህ ጥሪ ለእናንተ ነው... ማደግ ብን አድርጎ ላጠፋችሁ! ያንን ሕያው ቃል ከልባችሁ ጓዳ ላራቀባችሁ፤ መንፈሳዊ ዝማሬውን በዘፈን ለቀየራችሁ... ከቤቱ ለራቃችሁ... ከሰንበት ትምህርት ቤት መቅረዝ ለተለያችሁ... እና በዓለም ግርግር ውስጥ ለምትባክኑ..
ኑ... ወደዚያ ንጹሕ የልጅነት ቤታችሁ ተመለሱ! በሩ ዛሬም ክፍት ነው፤ ቤቱ ዛሬም ይናፍቃችኋል።
✍ቬነስያ
1 750
ያ የሕፃንነት ዘመናችን... ብርዱን ሳናስበው፣ ቅዝቃዜው ሳይሰማን በረከቱ ይድረሰኝ ብለን በንጹሕ ልብ በዝናቡና በጸበሉ ስር የምንቆምበት ያ ቅን እምነታችን ......
በዓለም ውጣ ውረድና በኃጢአት ጥላሸት የጠቆረውን ልባችንን፣ በሥጋና በነፍስ የቆሸሸውን ማንነታችንን ፈዋሹ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በምህረቱ ጸበል ይጠብልን።
ዛሬ ማደግ ያሳጣንን ያን የሕፃንነት የየዋህነት እምነት ይመልስልን።በፈዋሽ ክንፎቹ ጥላ ስር ሰውሮ ከደዌ ሁሉ ይፈውሰን!
የቅዱስ ሩፋኤል ምልጃ፣ ፍቅርና በረከት ሁልጊዜም አይለያችሁ!!!
እንኳን አደረሳችሁ!
1 750
ከእናንተው ጥያቄ
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
..... .:
Selam wendme
ene yemteykh degmo kehonech lij gar ke hulet amet befit entewawekalen kezam just ende friend enaweralen eyetekerarebn metanna ene betam endemwedat ngerkuat ersuam endemtwedegn tnegregn neber bemehal zegachign behuala temelsen mawrat keteln ena hule yemiaschenkat endale teredahuat ena endtnegrign sasgeddat ketewawekn behuala betesebochua asgeddew endagebach ena baluan ttaw endemetach ena betam yemiastela tesfawan hiwetuan endachelemubat negerechign endenegerechign bebetechirstian sreat magbat endemtfelgna gn kagebach behuala hiwet chelema endehonebat negerechign betam asazenechign degmom ewedatalehu ena ene degmo yebetechurstian sreat beftsum metas alfelgm ene alagebahumm setm alawkm ena still now endemwedat new yemnegrat gn yemwedat mkniyatu betam slemtasaznegnm new ene ena ersua bebetechirstian sreat meseret meketel enchilalen
diyakon mehon eflgalhu gn lahunu zm bye new eyetemarku yalehut edme gedeb ysemagnal malet 22 amet eyehonegn new degmom endet egziabhern fkad endemteykm asbalehu
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
የቬነስያ መልስ
✨✨✨✨✨
ወንድሜ ፍላግትህንና እና የእህታችንን አሳዛኝ የሕይወት ገጠመኝ በግልጽ ስላካፈልከኝ ላመሰግንህ እወዳለሁ። በእሷ ላይ የደረሰው ነገር እጅግ ልብ የሚሰብር ነው። አንተም ለእርሷ ያሳየኸው ርኅራኄ ክርስቲያናዊ ነው። ሆኖም ይህን የሕይወት መስቀለኛ መንገድ በስሜት ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ብስለትና እርጋታ ልታየው ይገባል።
ከሁሉ በፊት ህይወት ከሁለት አጣብቂኝ ምርጫዎች ውስጥ እንድንመርጥ ስታደርገን ፈተናው የአንተ ብቻ እንዳልሆነ እና የብዙ ሰው እንደሆነ በመገንዘብ በጸሎት ሃይል ልትጋፈጠው ይገባሃል።
በሁለትና በሦስት መልካም ወይም ከባድ ምርጫዎች መካከል የመወሰን ጉዳይ ከባድ ሊሆን ይችላል። በእግዚአብሔር አጋዥነት የማይቻል ግን አይደለም።
በቅድሚያ ከውሳኔህ በኋላ ለማግኘት የምትፈልገውን ውጤት ማለትም መንፈሳዊ ሰላምህን እና የነገ ሕይወትህን ግልጽ አድርገህ እወቅ። ያንን ማድረግ ያለብህ የምትወስነው ውሳኔ ሊመዘን የሚገባው ከውጤቱ አንጻር ስለሆነ ነው። ከዚያም በመቀጠል ካሉህ ምርጫዎች የትኛውን ውሳኔ ብትከተል ወደዚያ ውጤት እንደሚመራህ ለመለየት ሞክር።
በእነዚህ ምርጫዎች መካከል ለመለየት ምርጫህን ተግባራዊ ለማድረግ የምትከተለው መንገድ መንፈሳዊ ጤናማነቱ የሚያስከፍልህ ዋጋ እንዲሁም ምርጫውን የመምረጥህ ሂደት ከምንም ዓይነት የፍርሃት፣ የሰዎች አጉል ተጽዕኖና ጊዜያዊ የርኅራኄ ስሜት ጫናዎች ውጪ የመሆኑ ጉዳይ በጥብቅ ሊታሰብበት ይገባል።
ይህን መሠረት በማድረግ በቀጥታ ከጥያቄህ ጋር የሚያያዙትን ቀጣዮቹን ሦስት እርምጃዎች እንድታስተውል ልጠቁምህ
ቅድሚያ ዲያቆን መሆንን አጥብቀህ የምትፈልግ ከሆነ ከእርሷ ጋር ወደ ትዳር ግንኙነት ውስጥ መግባት አትችልም! ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ዲያቆን የሚሆነው አገልጋይ ከዚህ ቀደም ትዳር ካልነበራት ድንግል ከሆነች እህት ጋር ብቻ እንዲጋባ ያዛል። ስለዚህ ከክህነት ጥሪህ እና ከእርሷ ከሁለቱ አንዱን በእርግጠኝነት መምረጥ ግድ ይልሃል። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፳፬።
በመቀጠል ክህነቱን ትተህ ከእርሷ ጋር በጋብቻ አብረሃት መሆን ከፈለግህ ይህ ትክክል ነው አይደለም የሚለውን የእርሷን የቀድሞ የትዳር ሁኔታና የአንተን ፍላጎት በማቅረብ የንስሐ አባትህን አጥብቀህ አማክር። ቤተክርስቲያን በምትፈቅደው መንገድ ሕይወታችሁን እንዲመሩህ የንስሐ አባትህ ውሳኔ ወሳኝ ነው። እዚህ ላይ እኔ ምንም ልልህ አልችልም።...የበርሃው ኮከብ ታላቁ ቅዱስ እንጦንስ "በምትሠራው ሥራ ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ምስክር አድርግ፤ ከታላላቆችህ ከንስሐ አባትህ ጋር ሳትመክር አንዳች አታድርግ" እንዲሉ
ሌላው አንተም የክህነትን ሐሳብ ትተህ ትዳሯን ፈታ ከመጣች እህት ጋር የመኖር ሐሳቡ ካለህ አስተሳሰብህን ከዚህም በላይ ማጠናከር አለብህ። የምወዳት ምክንያት በጣም ስለምታሳዝነኝ ነው ያልከው ሐሳብ አደገኛ ነው። መተዛዘን መልካም ቢሆንም፣ የትዳር መሠረት ርኅራኄ ብቻ ሊሆን አይችልም። ስለዚህ የሚገባትን እውነተኛ ፍቅር እና ክብር ለመስጠት ራስህን በሚገባ አዘጋጅ።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
በህይወታችሁ ብዙ የሆናችሁለት ሰው አብዝቶ ይጎዳችኋል፣ እናንተም እንዲሁ አብዝቶ የሚወዳችሁን አምላክ ትበድሉታላችሁ!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
አንድ አባት እንዲህ ሲሉ ሰማዋቸው
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
"የማይጣሉ መላእክት፣ የማይታረቁ አጋንንት አትሁኑ"
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
ምን ማለት ይመስላችኋል?
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
እርስዎ አደሉም
☦☦☦☦☦☦☦☦☦
አንድ ፈረንሳዊ ነጭ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለጉብኝት ይመጣል። በዘመናዊ ዕውቀት ከተካኑት የገዳሙ መናንያን መኻል አንድ አባት ይመደቡለትና ጉብኝቱን ይቀጥላል።
በጉብኝቱ መኻል ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የፈጸሙትን ተጋድሎ በተለይም ከዚያው ከገዳሙ ከሚገኘው ደብረ አስቦ ዋሻ ውስጥ ሃያ ሁለት ዓመት በሁለት እግራቸው፤ ሰባት ዓመት ደግሞ በአንድ እግራቸው በድምሩ ፳፱ ዓመት ለጸሎት ቆመው የተጋደሉትን ተጋድሎ ከአስጎብኚው የተረዳው ፈረንጅ በጣም በመገረምና በመደነቅ ሁለቱን እጆቹን እራሱ ላይ በመጫን "ይኽማ የማይሆንና የማይታመን ነገር ነው!" ብሎ ጮኸ.....
አያይዞም እኔ እራሴ ለሠላሳ ደቂቃ ቆሜ መቆየት አልችልም እናንተ ግን አንድ ሰው ሃያ ዘጠኝ ዓመት ቆመ ትላላችሁ። ይኽ እንዴት ሊሆን ይችላል ብሎ ተናገረ።
የፈረንጁን ባዶነት የተረዱት አስጎብኚ አባት እርባና ቢስ ንግግሩን ካስጨረሱት በኋላ "የተከበሩ ፈረንጅ ይኽንን ተጋድሎ የፈጸሙት ኢትዮጲያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው እንጂ እኮ እርስዎ አይደሉም" አሉት።
🔴⚪️⚫️⚪️🔵🔴⚪️🔵⚪️🔴⚫️⚪️
ሌባ እናት ልጇን አታምንም....እግዚአብሔር አስችሏቸውና ለተጋድሎ መርጧቸው ያጸናቸው ቅዱሳን የተጋደሉትን ገድል፣ የፈጸሙትን ተዓምራት መናቅ ለዚህ መዓረግ ያበቃቸውንና ያስቻላቸውን እግዚአብሔርን መናቅ ነው።
⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️
⬜️⬜️ ዮሐ ፲፬፤፲፪ ⬜️⬜️
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
መኖርም ሆነ መጸለይ አስጠልቷችሁ፣ ሁሉም ነገር ባዶ ሆኖባችሁ...መኖር ራሱ ትርጉም አቶባችሁ ያውቃል አይደል?
ይህ ሲሆን ከእራሳችሁ ጋር አትታገሉ! ዝም ብላችሁ ሁሉንም ለጊዜው ተወት አድርጉና "እግዚአብሔር ሆይ ደከምኩብህ፣ አቅምም የለኝም....አንተ ሥራህን በሉት" በሉት። በቃ! የቀረውን እርሡ ያበጀዋል።
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
🍀ከእግዚአብሔር ጋር ያላትን ግንኙነት በጸሎትና በትህትና ማጠናከር በንስሐና በቅዱስ ሥጋወደሙ ሕይወቷን በመጠበቅ መንፈሳዊ ንጽሕናዋንና ማንነቷን አጽንታ መያዝ።
🍀ራሷን ሁልጊዜ ለአዳዲስ እውቀቶች ክፍት በማድረግ መንፈሳዊ ሚዛኗን የጠበቁና ለዓለማዊ ሕይወቷ ስኬት የሚያስፈልጉ ትምህርቶችን በትጋት መከታተል።
🍀ለነገው የትዳርና የቤተሰብ ሕይወቷ ጠንካራ መሠረት የሚሆኑ ገቢ የሚያስገኙና ራሷን የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ሙያዎችንና ክህሎቶችን ማዳበር።
ከልጅነት አስተሳሰብና ስሜታዊነት በመውጣት ግንኙነቶቿን በጥበብ የምትመራበትን የሚጠቅማትንና የሚጎዳትን ለይታ የምትወስንበትን ማንነት ማሳደግ።
1 750
ለበጎ ነው
🍀🍀🍀🍀
በአንድ ወቅት አንድ መንፈሳዊ አባት ከነበሩበት ቦታ ወደ በረሃ መሰደድ ግድ ሆነባቸው። ከቅዱስ መጽሐፋቸው ሌላ ሦስት ነገሮች ነበሯቸው።
እነሱም፦ ቅዱስ መጽሐፉን በጨለማ ወቅት ለማንበብ የሚጠቅማቸው ኩራዝ ፣ጎህ ከመቅደዱ በፊት ከእንቅልፍ የሚቀሰቅሳቸው አንድ አውራ ዶሮ እና ለመጓጓዣነት የሚገለገሉበት አንድ አህያ ነበሩ።
አንድ ቀን ምሽት ከጉዞ የተነሣ በጣም ስለ ደከሙ እኚህ መንፈሳዊ አባት ወደ አንድ መንደር ቀርበው ማደሪያ ቢጠይቁም መንደርተኛው ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማንም አላሳደራቸውም። ስለዚህም ከመንደሩ አቅራቢያ አንድ ጉድጓድ ያገኙና በዚያ ውስጥ ገብቶ ለማደር በመወሰን ገብተው አደሩ። እንደ ወትሮው ቅዱስ መጽሐፋቸውን ለማንበብ ኩራዛቸውን ቢለኩሱትም የነበረው ብርቱ ነፋስ አጠፋባቸው።
ስለዚህም ለመተኛት ጋደም እንዳሉ ተኩላ መጥቶ አውራ ዶሮዋቸውን፣ አንበሳም አህያቸውን በሉባቸው። የተደራረበ ጉዳት ስለደረሰባቸው ሽማግሌው እርዳታን በመሻት ወደዚያ መንደር ቢመለሱ ዘራፊ ሽፍታዎች የመንደሩን ነዋሪዎች በሙሉ ገድለው ንብረት ዘርፈው ዖና መንደር ሆኖ አገኙት።
ሽማግሌው ይህን ሁሉ ባጤኑ ጊዜ እግዚአብሔር ምን ያህል መልካም ነገርን እንዳደረገላቸው አስተዋሉ። በዚያች ምሽት በመንደርተኞቹ በአንዱ ቤት ቢያድሩ ኖሮ የዘራፊዎች ሰለባ ሆነው ሊገደሉ በቻሉ ነበር። ቀንዲላቸውንም ነፋስ ባያጠፋው የብርሃኑ ወጋገን እዚህ ጋር ሰው አለ በማለት ለሽፍታዎቹ ያሳብቅ ነበር። አውራ ዶሮአቸውና አህያቸውም ባይበሉ ኖሮ ከሽፍታዎቹ ተደብቀው ማደር ባልቻሉ ነበር።” እግዚአብሔር ከክፉ ነገሮች ውስጥ መልካም ነገር ማውጣት የሚችል አምላክ ነው።"
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ስለዚህ እንዲህ በሉ፦ "የሚደርስብኝ ፤ የሚገጥመኝ ፈተናና መከራ ሁሉ አምላኬ ሆይ ለበጎ ታደርግልኛለህና አመሰግንሐለሁ"
ይህን የጻፍኩላችሁ በቀደመው ፖስቴ ትንሽ ቀን አልኖርም ብዬ ለቅቄላችሁ ነበር....ነገር ግን በዓመታት የሚፈታ ያልመሰለኝን ችግር እግዚአብሔር በአንድ ቀን ነው ፈቶት መልስ የሰጠኝ.... ሁሉም ነገር ለበጎ ነው!
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
ኃጢአታችሁ እንደ ደም ቢቀላ፣ የመውደቃችሁ ብዛት ተስፋ ቢያስቆርጣችሁ እንኳ እግዚአብሔር ከእናንተ የሚፈልገው ሙሉ አቅማችሁን ሳይሆን፣ ወደ እሱ ለመመለስ የምታደርጓትን ትንሿን የንስሐ ጥረት ብቻ ነው።
እርሱ የልባችሁን ስብራት እንጂ የፍጹምነታችሁን ልክ አይመዝንም! ስለሆነም ያችን ወደ እሱ የምትዘረጓትን አንዲት ቅንጣት ትጋት በፍጹም አትጡት! እርሷ እጅግ ታላቁን ምህረት ታመጣለችና!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
ውድ ታዳሚዎቼ ለትንሽ ቀናት ላልኖር እችላለው.....ያልመለስኩላችሁ ሰዎች ይቅርታ አድርጉልኝ....እግዚአብሔር በረዳኝ ስመለስ እመልሳለው!
ብትችሉ ኃይለ ጊዮርጊስ ብላችሁ በጸሎት አስቡኝ
1 750
አንድ የገጠር ገበሬ በታላቁ የቅዱስ ገብርኤል ንግሥ ቀን ድንገት ከብቱ ጠፍቶበት መላው ይጠፋዋል። ተስፋ በመቁረጥና በጭንቅ ተሞልቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ደጅ አመራ። በሩ ላይ እንደቆመ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ በታላቅ ድምፅ....
«ቅዱስ ገብርኤል አባቴ ሆይ! እባክህ ይህን የጠፋውን በሬዬን ፈልገህ ካስገኘኸኝ ከሚሸጠው ዋጋ እኩል ግማሹን ሙሉ በሙሉ ለቤተ ክርስቲያንህ እሰጣለሁ!» ብሎ በጽኑ ተሳለ።
ስእለቱን ተናግሮ ገና ፊቱን እንደመለሰ፡ በሬው እዚያው አቅራቢያ ሳር ሲጋጥ ድንገት ዓይኑ ላይ ወደቀ። ገበሬው በደስታ ከመፈንጠዝ ይልቅ የተሳለውን ግማሽ ዋጋ ማጣቱ ቁጭት ስላደረበት ወዲያው ፊቱን ወደ ደጁ መልሶ....
«ቅዱስ ገብርኤል ሆይ... በቃ ተወው ራሴው አገኘሁት!» አለ ይባላል።
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
የተሳልነው ሲደርስልን የተናገርነውን የምንረሳ ስንቶቻችን እንሆን?
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
በፍጹም! አንድ ሰው ሁለት ሰው ሊያፈቅር አይችልም.... ሁለተኛው ላይ የፍቅር ስሜት ካደረበት ቀድሞውኑ ከመጀመርያው ጋር ፍቅር አልነበረውም! ኧረ እንደውም የፍቅር ትርጉሙም አልገባውም!!!!!!!
ለሁለት ጌቶች መገዛት አትችሉም ይላል ቃሉ🍀
1 750
ከእናንተው ጥያቄ (ውጤት ላልመጣላችሁ)
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
ሰላም ቬነስያ
ጎበዝ ተማሪ ሆነን ግን አሁን entrance result ላልመጣልን ተማሪዎች የሆነ ነገር በለን ?
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
የቬነስያ መልስ
🍀🍀🍀🍀🍀
ይህ ውጤት ላንቺም ሆነ ሌሊት ከቀን ሲያጠኑ ለነበሩ ብዙ ጎበዝ ተማሪዎች ምን ያህል ልብ ሰባሪ እና አስደንጋጭ እንደሆነ በሚገባ እረዳለሁ። ሆኖም በዚህ ፈታኝ ወቅት አእምሮሽን አረጋግተሽ የሚከተሉትን እውነታዎች በጽሞና እንድታስተውይ እመክርሻለሁ.....
በመጀመሪያ ደረጃ ፈተና ማለፍም ሆነ መውደቅ አንድ አጭር የሕይወት ምዕራፍ ነው እንጂ፣ የሕይወት ብቸኛው አካል አይደለም። ዛሬ ላይ ውጤት አልመጣልሽም ማለት ሕይወት ቆመች ማለት አይደለም። ሕይወት እጅግ ብዙ ዘርፎች እና የተሻሉ መንገዶች ያሏት ሰፊ መጽሐፍ ናት።ውድቀት የሕይወት መጨረሻ አይደለም።
ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በማንኛውም የሕይወት ፈተና ውስጥ ስናልፍ ሁሉ ለበጎ ነው ብለን እንድናመሰግን ታስተምረናለች። አንዳንዴ ማለፋችን መጥፊያችን ሊሆን ስለሚችል የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ እኛ ከማናውቀው የሕይወት ገደልና ፈተና እየጠበቀሽ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ አለብሽ። ፈጣሪ የዘጋብሽ የሚመስለው አንድ በር ለነፍስሽም ለሥጋሽም የሚጠቅሙ ሺህ የተሻሉ በሮችን ሊከፍትልሽ ነው።
እስከዛሬ በሕይወት ተሞክሮ ከተረዳሁት ነገሮች መካከል ፈተናን ወድቀው የተለያዩ የሙያ መስኮችን ተምረው ያሉ ሰዎች ዛሬ ላይ እጅግ የተሻለ ሕይወት ላይ እንደሚገኙ የማይደበቅ ሃቅ ነው። መደበኛውን የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እያጣጣልኩ ባይሆንም፣ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው በቅጥር ሕይወት ውስጥ ብቻ ተወስነው ከሚቀሩ ሰዎች ይልቅ በአጫጭር ሙያዎች የተማሩ ሰዎች የራሳቸውን ሥራ የሚከፍቱበት እና ራሳቸውን የሚቀይሩበት መንገድ እጅግ የሰፋ ነው። ከዚህ በኋላ ካንቺ የሚፈለገው ጥረትሽ ብቻ ነው!
በሌላ በኩል ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መግባቱን በብዙ የምትፈልጊው ከሆነ አሁን ካለሽበት ድክመት ተምረሽ፣ ጠንክረሽ በማንበብ ድጋሜ መፈተንና በቀላሉ ማሳካትም ትችያለሽ።
ውጤት ያልመጣላችሁ ታናናሽ ወንድሞቼና እህቶቼ ይህንን ጊዜያዊ ውድቀታችሁን እንደ መንደርደሪያ ተጠቅማችሁ የነገ ሕይወታችሁን የምትቀይሩበት አቅም አድርጉት። ማንነታችሁ የሚለካው በወረቀት ውጤት ሳይሆን፣ ከውድቀት በኋላ በምታሳዩት መነሳት ነው።
እግዚአብሔር በጉዟችሁ ሁሉ ይምራችሁ!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
1 750
ከእናተው ጥያቄ ለሚለው ከሆነ....
🍀በምትጠይቁት ዙርያ የተጻፉትን መጽሐፍት አነባለው
🍀 አባቶችን እጠይቃለው
🍀 በእውቀት የሚበልጡኝን ጓደኞቼን አማክራለው
🍀 በዚህ ጉዳይ ላይ ያለፉትን ሰዎች አማክራለው
በመጨረሻም ሃሳቡን ሰብስቤ ፣ በጣም ሳይረዝም፣ በተቻለ መጠን ልባችሁን ሊነካ እና ልትማሩበት በምትችሉበት መልኩ አቀርበዋለው
1 750
🍀አጫጭር ታሪኮች ላይ አተኩራለው
🍀በቀን በትንሹ 5 ገጽ አነባለው
እንድታነቡት Recommend የማረጋችሁ መጽሐፍ
✨ የመሰጠት ህይወት (ዲ/ን ኅሊና በለጠ)
1 750
ሐዋርያው መነኩሴ አባታችን ተክለሃይማኖት በድካማችንና በፈተናችን መካከል፣ በቃኝ፣ ከዚህ በላይ አልችልም ብለን ተስፋ በቆረጥንበት፣ ድካምና መንፈሳዊ ዝለት በተጫነን ነገሮች ላይ የፃድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ድንቅ ረድኤትና ምልጃ ይጠብቀን።
የኢቲሳው አንበሳ፣ ያ የጸሎት ጀግና በቆሙበት አንድ እግራቸው ፍቅርና ትዕግሥትን ያስተማሩን፣ የጠላትን ሰራዊት ሁሉ ድል የነሱበት ያ የብርታት መንፈሳቸው ይደርብን!
በእውነት በመንፈሳዊ መንገዳችን ላይ የሚቆሙትን እሾሆች ሁሉ ያርቁልን፤ ድካማችንን ወደ ብርታት፣ እረፍታችንን ወደ ተጋድሎ፣ ተስፋ መቁረጣችንን ደግሞ ወደ አዲስ መንፈሳዊ ድል ይለውጡልን!
በረከታቸው፣ ፍቅራቸውና ጠባቂነታቸው ሁልጊዜም ከእኛ ጋር ይሁን! አሜን።
