Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
Open in Telegram
Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
215
Subscribers
No data24 hours
+17 days
No data30 days
Posts Archive
ጌታ ችኩል የነበረውን ፣ በአቋሙ ማይጸናውን ፣ ፈጥኖ መርቆ ፈጥኖ የሚክደውን ስምዖንን ጴጥሮስ ብሎ አዲስ ስም አወጣለት። ትርጉሙም ዐለት ማለት ነው። ይህ ስያሜ በጊዜው የነበረውን የስምዖንን ጠባይ የማከለ ባይሆንም እንኳን ጌታ የጸና ብርቱ፣ መሠረት ብሎ ሊጠራው አላንገራገረም። ምክንያቱም ለጌታ ይታየው የነበረው ያ ሀሳቡ በየሰዓቱ የሚዋዥቀው ፣ በችኮላ የሚመላለሰው ስምዖን ሳይሆን በንስሐ እንባ ተመልሶ ወንጌልን ከወንዶሞቹ ሀዋርያት ጋር ድምጹን ከፍ አድርጎ የሚሰብከው፤ ለማያምኑ በጥብዓት ስለ ጌታ ሳይታክት የሚያስተምረው፤ በነገሥታቱ ፊት እንኳን ስለ ስሙ ለመመስከር የማያፍረው የጸና ዐለቱ ጴጥሮስ ነበር።
እኛ ሁላችንም አሁን ያለንበት ህይወት ስማችንን የማይወክል የዘቀጠ ማንነት ውስጥ ልንሆን እንችላለን። የእግዚአብሔር ልጆች የሚለው ስም የማይገባን አንዴ ወደ ጽድቅ አንዴ ወደ ኃጥያት የምንቀላውጥ ጥቂት ነገር የሚያስደነብረን ልንሆን እንችላለን። ጌታ ግን አሁንም በከበረው ስማችን ልጄ ብሎ ይጠራናል። እንዲህ ብሎ የሚጠራን በንስሐ በመመላለሳችን በእርሱ ረዳትነት ወላዋይነታችንን አስቀርቶ ጽኑአን እንደሚያደርገን፤ የኃጥያትን ጣዕም ከውስጣችን አሟጦ በጽድቅ መዓዛ እንደሚያውደን፤ በጥቂት ማዕበል ከመናወጽ አውጥቶ የጸና ወደብ ላይ እንደሚያሳርፈን ስለሚያውቅ ነው፤ ለእርሱ የሚታየው ይህ ነው።
ወዳጄ በሰው ዘንድ ስማችን የፈለገ ቢጎድፍ፤ ስማችንና አነዋወራችን ለየቅል ቢሆንም አንድ ነገር ግን መርሳት የለብንም ለአባትህ ለእግዚአብሔር አሁንም ልጁ ነህ፤ በአምላክህ ዘንድ አሁንም ስምህ አልጎደፈም። እግዚአብሔር አሁንም ወደ እርሱ በንስሐ ተመለስህ ራስህን እንደምታነጻ ተስፋ ስለሚያደርግብህ በከበረ ስምህ ነው የሚጠራህ - ልጄ እያለ።
❝...We demand justice!
We demand Accountability!
We demand Action!❞
Prince Asfawesen Asrate kassa.
ይኸው ትናንት የአውሮጳ ኅብረት ራሱ ቁጭ ብሎ ልዑል አስፈወሰን አሥራተ ካሣን ሲያዳምጥ የዋለው በኢትዮጵያ በአሩሲ የወሀቢያ እስላሞች እንደ ዶሮ ስለሚያርዷቸው ዐማሮች እና የኦሮሞ ኦርቶዶክሶች ጉዳይ ነው።🔥🔥🔥
ለዘብተኛ ክርስቲያን በመሆኔ የወንድሞቼ ቁስል ስር ሰዶ ላልተሰማኝ ለኔ ወዮልኝ።
ስንቴ ለማይረባው ጉዳይ እንባዬን ያዘራሁ ለወንድሞቼ ሞት ሲሆን እንባዬ ለከዳኝ ለኔ ወዮልኝ።
ወንድሞቼ ማረፊያ አጥተው እንደ በግ በተኩላ ሲታረዱ፣ በተመቸ አልጋ ላይ ተኝቼ ለማድረው ለኔ ወዮልኝ።
እኔን ከዚህ ሀኬተኛነት በቸርነቱ እንደሚያወጣኝ የምተማመንበት እግዚአብሔር፤ የሚያሳድዱንን፣ ወንድሞቻችንን የገደሉብንን ሁሉ በፈራጅነቱ እንደሚበቀላቸው ፍጹም እተማመናለሁ።
ለዘብተኛ ክርስቲያን በመሆኔ የወንድሞቼ ቁስል ስር ሰዶ ላልተሰማኝ ለኔ ወዮልኝ።
ስንቴ ለማይረባው ጉዳይ እንባዬን ያዘራሁ ለወንድሞቼ ሞት ሲሆን እንባዬ ለከዳኝ ለኔ ወዮልኝ።
ወንድሞቼ ማረፊያ አጥተው እንደ በግ በተኩላ ሲታረዱ፣ በተመቸ አልጋ ላይ ተኝቼ ለማድረው ለኔ ወዮልኝ።
እኔን ከዚህ ሀኬተኛነት በቸርነቱ እንደሚያወጣኝ የምተማመንበት እግዚአብሔር፤ የሚያሳድዱንን፣ ወንድሞቻችንን የገደሉብንን ሁሉ በፈራጅነቱ እንደሚበቀላቸው ፍጹም እተማመናለሁ።
ልባችንን ኃጥያት እያሰናከለው ነው እንጂ የያዕቆብ መሰላል በሆነችው በበአዛኝቷ እመቤት ተስበን እስካሁን ከሰማየ ሰማያት ከልጇ አጠገብ ደርሰን ነበር።
እንኳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ለተገለጠችበት አመታዊ በአል አደረሳችሁ።
Repost from Theo-Sophia
ይህንን story በማድረግ እና share በማድረግ ተባበሩን ። እንደሁል ጊዜው መልካም ፈቃዳችሁ እና ቀና ልቡናችሁ ያስፈልገናል ። ያልሰማ ሰው እንዳይኖር ሰምቶም ቸላ ያለ እናም ለመስጠት የሰሰተ እንዳይኖር የሰማ ሁሉ የአቅሙን እንዲያደርግ እና የነዳያንን ረሃብ እንድናስታግስ እንለምናችኋለን።
"የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።"(ሉቃ 1:27)
ዓለም በኃጥያት አዘቅት ወስጥ ተዘፍቆ በነበረበት ዘመን፤ ሁሉም ተባብሮ ይበድልበት በነበረበት ዘመን አንዲት በኃጥያታቸው ያልተባበረች፣ ከበደላችው ያልተሳተፈች ድንግል ነበረች። የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
እግዚአብሔር ከሰማይ ሆኖ ሲመለከት በንጽሕናዋ የታየችሀው ፤ በጎ መአዛን ፍለጋ ሲያሸት ያገኛት የናርዱስ ሽቱ፤ በጨለማው ዘመን በቤተ መቅደስ የምታበራ አንዲት እንቁ ድንግል ነበረች፤ የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
እግዚአብሔር አብ ለልጁ ማድሪያን ሲሻ ንጽህናዋ የማረከው፤ ወልድም ከእርሷ ይወለድ ዘንድ የመረጣት፤ መንፈስ ቅዱስም ለጽድቅ ያላትን ዝንባሌና ፍቅር ተመልክቶ ከክፉ ነገር የጋረዳት አንዲት ድንግል ነበርች፤ የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
መልአክት እሕታችን እያሉ የሚጠሯት፤ ሊያዩአትም የሚናፍቋት፣ በንጽሕና የምትመስላቸው፤ አምላካቸውን እንድትወልድ የተመረጠች አንዲት ድንግል ነበርች፤ የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
ገብርኤል በስድስተኛው ወር የተላከላት፤ ልዑልን እንደምትወልድ ሊያበስራ የታዘዘላት፤ ሀርና ወርቁንም ስትፈትል ያገኛት አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
ደስታ ገንዘብ የሆነላት፤ ጸጋን የተመላች፤ እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር የሆነ፤ ከሴቶች ተለይታ የተባረከች አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያችም ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
በእግዚአብሔር ዘንድም ባለሟልነት ያገኘች፤ ፀንሳ፣ ወንድ ልጅን እንደምትወልድ ስሙንም ኢየሱስ እንደምትለው የተነገራት አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
ወንድ የማታውቅ፤ ሀሳቡም ያልነበራት፤ የብስራቱ ነገር እንዴት እንደሚፈጸም የጠየቀች አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
መንፈስ ቅዱስ እንደሚያድርባት፤ የልዑል ኃይልም እንደሚጋርዳት፤ ከእርሷ የሚወለደውም ቅዱስ የሆነው የልዑል እግዚአብሔር ልጅ እንደሚባል የተነገራት አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም በሚለው ቃል ልቧ የጸና፤ እነሆኝ የእግዚአብሔር ባርያው እንደ ቃልህ ይሁንልኝ ብላ በትህትና የተናገረች አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
በሰውነቷ እግዚአብሔርን የምታከብር፤ ልቡናዋም በአምላኳ በእግዚአብሔር ሐሴት የሚያደርግ፤ ትሕትናዋን ፈጣሪ የተመለከተላት፤ ከዚያ ዘመን ጀመሮ ትውልድ ሁሉ ብጽእት እያሉ የሚያወድሷት አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
የተባለው ሁሉ ጊዜው ደርሶ ያለ ወንድ ዘር የጸነችውን ልጇን ድንግልናዋ ሳይለወጥ በበረት የወለደች፤ እረኞችና መላእክት መጥተው የጠየቋት አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
የምትሳሳለትን ልጇን ሄሮድስ ሊገልባት ሲል እንባ እያዘራች የሸሸች፤ በረሃ ለበረሃ እንደ ወፍ የተንከራተተች፤ የልጇ እንባና የውኃ ጥም አንጀቷን ያንሰፈስፋት፤ የፀሐዩ ሙቀት የአሸዋው ግለት ከምሽቱ ቅዝቃዜ ጋር እየተፈራረቀ ያጠወለጋት ከዚያ በፊት መከራ ያለመድች አንዲት ድንግል ነበረች፤ የዚያች ድንግል ስምዋ ማርያም ይባል ነበረ።
እንኳን ለዚህች ቅድስት ለሆነች ድንግል የልደት ቀን አደረሳችሁ።
ትዕቢት የነፍስ መጋረጃ ነው። የእግዚአብሔርን ብርሃን ፣ የሰውን ክብር ፣ የተዘጋጀልንን ሰማያዊ መንግስት እንዳናይ የሚያደርግ ወፍራም መጋረጃ።
"ከፊተኛይቱ የምትከፋ የኋለኛይቱ ስህተት"
(ከትንሣኤ ንባብ የተቀነጨበ ሃሳብ)
ሊቃነ ካህናቱ ጌታን አሳልፎ እንዲሰጣቸው ለይሁዳ የከፈሉት 30 ዲናር ነበር::እነሱ አምላክ አይደለም ብለው የሰቀሉት ከዚያም በቅንዓት ተነሳስተው የገደሉት ጌታ ከሙታን መነሳቱን ጠባቂዎቹ አረዷቸው::
ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም እንደሚባለው ጌታን በሐሰት ምስክር እንዲገድሉ ያነሳሳ ሰይጣን የጌታን ትንሣኤ እንዲያስተባብሉ ልቦናቸውን አደነደነው:: 'ዝክራቸውንም በአንድነት ታጠፋለህ' የተባለን የጌታን ዝክር ሊያጠፉ ተነሱ ትንሳኤውን ለማስተባበል " 'እኛ ተኝተን ሳለን ደቀ መዛሙርቱ በሌሊት መጥተው ሰረቁት' በሉ።" ብለው ለጠባቂዎቹ 400 ዲናር ከፈሉ:: (መዝ 9፥6 ፣ ማቴ 29 ፥ 13)
በመሰረቱ ጠባቂዎቹ በሉ የተባሉትን ሲናገሩ የሰማ ሰው ብዙ ጥያቄዎችን ማንሳቱ አይቀርም:: 'እናንተ ተኝታችሁ ከነበረ ሐዋርያት መሆናቸውን በምን አወቃችሁ?' 'ሐዋርያት ከሰረቁትስ ለምን ሄዳችሁ አትይዟቸውም?( የኃይል ችግር እንደሌለባቸው ይታወቃልና)' 'ከመቼ ወዲህ ነው ደግሞ ጠባቂ 'ተኝቼ ነው የተዘረፍኩት' ብሎ የምስክርነት ቃል የሚሰጠው?' እና የመሳሰሉትን ይጠይቃል። ምንም እንኳ መልስ እንደሌለው ቢታወቅም::
በጣም የሚገርመው ሊቃነ ካህናቱ ጌታ ተላልፎ እንዲሰጣቸው ከከፈሉት በላይ የገደሉት ጌታ መነሳቱን ለማስተባበል ያወጡት ወጪ እጅግ ብዙ ነው::
ከነሱ ወገን ባልሆነው በይሁዳ ተለምነው 30 ዲናር የሰጡ ሹማምንት 400 ዲናር ለምነው ለጭፍሮቻቸው ከፈሉ::(ግብረ ሕማማት)
ከዚህ የምንረዳው አንድ ኃጢያት ለመስራት ከምንፈጀው ጊዜና ገንዘብ በላይ የኃጢቱን ውጤት ለመካድ ፣ ኃጢአቱ ያመጣብንን በሽታ ለመሸፋፈን የምንፈጀው ጊዜና ገንዘብ ምን ያህል አንደሚልቅ ነው ፤ ሊያውም ተዳፍኖ ላይቀር ነገር::
ዳዊት የኦርዮንን ሚስት ከማስነወሩ በላይ ኃጥያቱን ለመሸፈን ኦርዮንን ማስገደሉ በጣም ብዙ ዋጋ አስከፍሎታል::
ሊቃነ ካህናቱ ጲላጦስ ጋር ሄደው ክርስቶስን ሐዋርያት ሰርቀው ተነሳ እንዳይሉ መቃብሩን አስጠብቅልን ካሉት በኋላ እንዲህ አሉ:-
"የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና"
ማቴ 27 ፥ 64
ወዳጄ ከፊተኛው ስህተትህ ይልቅ የኋለኛው ይልቃልና ኃጢአትህን ለመሸፋፈን ብለህ ሌላ ወደማትወጣው አዘቅት ውስጥ ራስህን ከምትከት ምንም ሳታቅማማ ንስሐ ብትገባ ነው ሚበጅህ::
"ኃጢአቱን የሚሰውር ሰው አይለማም፤ የሚናዘዝና ራሱን የሚዘልፍ የሚተዋትም ግን ምህረትን ያገኛል።" መጽሐፈ ምሳሌ 28:13
ክርስቶስ ተነሳ፤ በእውነት ተነሳ።
ዲ/ን ዘለዓለም ዓለማየሁን
2016 ዓ.ም በዓለ ፋሲካ
Repost from Theo-Sophia
ፓሊካርፐስም ወደ ሜዳው ሲገባ "ፓሊካርፐስ ሆይ በርታ ፤ ጽኑ ኹን! " የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ተናጋሪውን ያየው ማንም የለም ፤ ነገር ግን በዚያ የነበሩት ወንድሞች ድምፁን ሰሙ ።
በመጨረሻም ወደ ፊት ሲያቀርቡት ሀገር ገዢው ፓሊካርፐስ እርሱ መኾኑን ጠየቀው ፤ እርሱም መኾኑን ሲያምን ሃይማኖቱን እንዲክድ ሊያግባባው እየሞከረ እንዲህ አለው "ለሽምግልናህ እዘን ደግሞም እነርሱ እንደሚያደርጉት ኹሉ በቄሳር መልካም እድል ማል ፤ ሐሳብህንም ለውጥና 'አምላክ የሌላቸው ይጥፉ' በል " አለው ። ያንጊዜም ፓሊካርፐስ በመሰብሰቢያው የነበሩትን ዓመፀኞች አረማውያን ኹሉ በእርጋታ ተመለከተ ፤ በእጁም እነርሱን አመለከተ ቃተተም ወደ ሰማይም ቀና ብሎ "አምላክ የሌላቸው ይጥፉ ! " አለ ።
ከዚያም ሀገረ ገዢው እየገፋፋው "ማል ፤ እኔም ነጻ አወጣሃለሁ ፤ ክርስቶስን ስደብ " አለው ። ፓሊካርፐስም "ሰማንያ ስድስት ዓመት አገልግዬዋለሁ ፤ እርሱም ከቶ ምንም አልበደለኝም ። ታዲያ ንጉሤንና መድኃኒቴን እንዴት ልሰድብ እችላለሁ ? " ብሎ መለሰለት ።
ዜና ስምዑ ለቅዱስ ፖሊካርፐስ ፤ ሐዋርያውያን አበው ገጽ 127
ቤተ ክርስቲያናችን የሐዋርያትን ትምህርት መያዟን፣ ሐዋርያት ባስተማሩበት ትምህርት ላይ መሰረት ማድረጓን ከምንረዳባቸው መንገዶች መካከል ከሐዋርያት እግር ስር ከተማሩና በሕይወትም በመጸሐፍም ክርስቶስን ከሰበኩ የሐዋርያት ደቀ መዛሙርት (ሐዋርያን አበው) ካስተማሩት ትምህርት ጋር አንድ መሆኑ ነው።
ይህንን የሐዋርያን አበው(Apostolic fathers) መጸሐፍ ወደ አማርኛ እጅግ ውብ በሆነ መንገድ ተተርጉሟል። ስለዚህ ሁላችንም መጸሐፉን ገዝተን ሕሊና አበውን ገንዘብ እናድርግ።
መጸሐፉን አንብባችሁ ስትጨርሱ በአበው ተጋድሎና ለክርስቶስ ባላቸው ፍቅር እየተደነቃችሁ ነፍሳችሁ የፈለገችው ክርስቶስን እንደምታገኙት አልጠራጠርም።
መጸሐፉ የፊታችን ረቡዕ ገበያ ላይ ይውላል።
Pre-order ስለተጀመረ ሁላችሁም ሳያልቅባችሁ አስቀድማችሁ እዘዙ።
መልካም ንባብ!
መጸሐፉን ለማዘዝ
https://t.me/Theo_Sophia_apology/922
"ጽኑ፥ አይዞአችሁ፥ አትፍሩ፥ ከፊታቸውም አትደንግጡ፤ አምላክህ እግዚአብሔር እርሱ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ አይጥልህም፥ አይተውህም።"
ኦሪት ዘዳግም 31:6
ንዒ ኃቤየ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከእኛ ጋር እንድትሆን የምንማጸናት አስሬ 'ንኢ ንኢ' የምንላት እርሷ ስትመጣ አብሯት የምንናፍቀው የአይናችን ማረፊያ፣ ረሀባችንን ሰውሮ በሥጋው መብልነት የሚያጠግበን፣ ጥማችንን አርቆ በደሙ መጠጥነት የሚያረካን፣ ሸክማችንን ሁሉ አቅልሎ ከድካማችን የሚያሳርፈን ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ አብሯት እንደሚመጣ ስለምናምን ነው።
አሁንም ከአፈ በረከት ከአባታችን ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጋር ሆነን እንዲህ እንላታለን፦
"ንኢ ኃቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ። - ድንግል ሆይ ልጅሽ ወዳጅሽ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሆነሽ ወደ እኔ ነይ።"ሰዓታት ዘሌሊት
"ትእዛዜን ብትሰማ ኖሮ፥ ሰላምህ እንደ ወንዝ ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር"
ትንቢተ ኢሳይያስ 48:18
ጌታዬ ሆይ ክፉ ነገር በማየት አይኖቼ ከታመሙብኝ ዘመናት ተቆጠሩ፣ ዝሙትና የዓለም ውበት ዓይኔን መጻጉዕ አድርጎታል፤ ጆሮዬም በዓለም ጫጫታና ዘፈን ደንቁሮ ያንተን ቃል መስማት ካቆምኩኝ አዕላፍ ጊዜያት አለፉ። የመዳን ቀንዴ ክርስቶስ ሆይ ክፋኛ ታምሜያለሁ።
"ልትድን ትወዳለህን" አልከኝ?
አዎ ጌታዬ! ነገር ግን ብዙ ጊዜ የምህረት ባህርህ ሲናወጥ ሰይጣን ቀድሞ ወደ ልቤ እየገባ በቅዱሱ ስፍራ እንዳልመለከትህ ድምጽህንም ሰምቼ እንዳልፈወስ እንቅፋት እየሆነብኝ፣ ከጽድቅ ስራ አፍአ ከተቀመጥኩኝ ስንት ጊዜዬ?! ወደ አንተ ለመምጣት ስንት ቀን መሰለህ ጉዞ የጀመርኩት?! አንዳንዴ በክፉ አመሌ ሌላም ጊዜ እጄ ላይ ባለው ስልክ ተሰነካክዬ ከመንገዴ ቀረሁ።
አይኔና ጆሮዬ ደግሞ እንጥፍጣፊ ንጽሕናዬን ከልቤ አሟጠው ባዶ ካደረጉኝ ሰነባብተዋል። ጌታዬ የኃጥያት ቁራኛ የሰይጣን ባርያ መሆን ሰልችቶኛልና ከካህኑ ጋር ሆኜ እንዲህ እማጸንሐለው፦
"ነፍስን የምታሻግር ለጻድቃን መሪ ለቅዱሳን መመኪያ፣ አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን፣ ዘወትር አንተን ያዩ ዘንድ ጆሮቻችንም ያንተን ብቻ ቃል ይሰሙ ዘንድ ፣ ሰውነታችን ከጸጋህ ከጠገበች ዘንድ ንጹሕ ልቡናን ፍጠርልን።"
አሜን!
የጌታ ቅዳሴ(ኃዳፌ ነፍስ)
መጻጉዕ 2018 ዓ.ም
