en
Feedback
የነብዩ ﷺ ሶሂህ ሐዲሶች በአማርኛ

የነብዩ ﷺ ሶሂህ ሐዲሶች በአማርኛ

Open in Telegram

በአላህ ፍቃድ በዚህ ቻናል ላይ የነቢያችንን ﷺ ሶሂህ ሐዲሶችን የምንለቅበት ይሆናል። ኢንሻ አላህ!!!

Show more
3 585
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1830 days
Posts Archive
አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ما مِن أيّامٍ العملُ الصّالحُ فيها أحبُّ إلى اللَّهِ من هذِهِ الأيّام يعني أيّامَ العشرِ، قالوا: يا رسولَ اللَّهِ، ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ؟ قالَ: ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ، إلّا رَجلٌ خرجَ بنفسِهِ ومالِهِ، فلم يرجِعْ من ذلِكَ بشيءٍ “በእነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም። ‘በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ጭምር?’ ተባሉ። እርሳቸውም ‘ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሃድም ከዚህ አይበልጥም’ አሉ።” (📚ቡኻሪ ዘግበውታል 969)           የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

የጧት እና የማታ አዝካሮች በደንብ አንብቡት ሸምዱዱት ሁሌም በሉት ደግሞ መቼም አታቋርጡ።
ዚክር የሕይወታችን መሠረት ሊሆን ይገባል።
          የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Tawhid_And_Sunah

اَلسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ ያ ጀመዓ ከዚህ በፊት በቻናላችን ላይ የተለቀቀውን
አርበዒን ኪታብ (42 የነብዩን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሐዲሶች) በጽሑፍ ከነ ማብራሪያው።
በቀላሉ ለማግኘት ከታች ሊንኩን በመጫን ማግኘት ማንበብና ማስነበብ ትችላላችሁ።
እንዲሁም ለሌሎችም ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ሁኑ ባረከላሁ ፊኩም።
የአርበዒን ኪታብ Pdf https://t.me/Amharic_Hadith/477 ሀዲስ ቁጥር አንድ https://t.me/Amharic_Hadith/480 ሀዲስ ቁጥር ሁለት https://t.me/Amharic_Hadith/482 ሀዲስ ቁጥር ሶስት https://t.me/Amharic_Hadith/486 ሀዲስ ቁጥር አራት https://t.me/Amharic_Hadith/489 ሀዲስ ቁጥር አምስት https://t.me/Amharic_Hadith/492 ሀዲስ ቁጥር ስድስት https://t.me/Amharic_Hadith/495 ሀዲስ ቁጥር ሰባት https://t.me/Amharic_Hadith/497 ሀዲስ ቁጥር ስምንት https://t.me/Amharic_Hadith/502 ሀዲስ ቁጥር ዘጠኝ https://t.me/Amharic_Hadith/505 ሀዲስ ቁጥር አስር https://t.me/Amharic_Hadith/508 ሀዲስ ቁጥር አስራ አንድ https://t.me/Amharic_Hadith/511 ሀዲስ ቁጥር አስራ ሁለት https://t.me/Amharic_Hadith/515 ሀዲስ ቁጥር አስራ ሶስት https://t.me/Amharic_Hadith/518 ሀዲስ ቁጥር አስራ አራት https://t.me/Amharic_Hadith/521 ሀዲስ ቁጥር አስራ አምስት https://t.me/Amharic_Hadith/524 ሀዲስ ቁጥር አስራ ስድስት https://t.me/Amharic_Hadith/526 ሀዲስ ቁጥር አስራ ሰባት https://t.me/Amharic_Hadith/529 ሀዲስ ቁጥር አስራ ስምንት https://t.me/Amharic_Hadith/534 ሀዲስ ቁጥር አስራ ዘጠኝ https://t.me/Amharic_Hadith/538 ሀዲስ ቁጥር ሀያ https://t.me/Amharic_Hadith/542 ሀዲስ ቁጥር ሀያ አንድ https://t.me/Amharic_Hadith/547 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ሁለት https://t.me/Amharic_Hadith/551 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ሶስት https://t.me/Amharic_Hadith/555 ሀዲስ ቁጥር ሀያ አራት https://t.me/Amharic_Hadith/559 ሀዲስ ቁጥር ሀያ አምስት https://t.me/Amharic_Hadith/566 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ስድስት https://t.me/Amharic_Hadith/574 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ሰባት https://t.me/Amharic_Hadith/579 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ስምንት https://t.me/Amharic_Hadith/584 ሀዲስ ቁጥር ሀያ ዘጠኝ https://t.me/Amharic_Hadith/589 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ https://t.me/Amharic_Hadith/595 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ አንድ https://t.me/Amharic_Hadith/598 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ሁለት https://t.me/Amharic_Hadith/603 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ሶስት https://t.me/Amharic_Hadith/609 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ አራት https://t.me/Amharic_Hadith/612 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ አምስት https://t.me/Amharic_Hadith/617 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ስድስት https://t.me/Amharic_Hadith/622 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ሰባት https://t.me/Amharic_Hadith/626 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ስምንት https://t.me/Amharic_Hadith/630 ሀዲስ ቁጥር ሰላሳ ዘጠኝ https://t.me/Amharic_Hadith/634 ሀዲስ ቁጥር አርባ https://t.me/Amharic_Hadith/638 ሀዲስ ቁጥር አርባ አንድ https://t.me/Amharic_Hadith/644 ሀዲስ ቁጥር አርባ ሁለት https://t.me/Amharic_Hadith/648
الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِين
     የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎ ያ ጀመዓ ዐፉወን ከዚህ ቦሃላ ለብዙ ጊዜ ያሕል ሐዲስ መልቀቅ አልችልም። ዒልም ፍለጋ ከሚዲያው አለም ለብዙ ጊዜያት ስለምርቅ ማለት ነው። እና ከዚህ በፊት ብዙ ሐዲሶችን መልቀቄ ይታወቃል። እና ወደኋላ በመመለስ ከዚህ ጀምራችሁ ማንበብ ትችላላችሁ።
👇
Amharic_Hadith Amharic_Hadith የአላህ ፍቃድ ከሆነ ለወደፊቱ በተሻለ መልኩ ለመምጣት እንሞክራለን ኢንሻ አላህ!! እና ይህን ደካማ ወንድማችሁን በዱዓ አትርሱት። ባረከላሁ ፊኩም።         የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ሸሪዓዊ እውቀትን መማር ረሱል ( ﷺ ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿طلَبُ العلْمِ فريضةٌ على كُلِّ مسلِمِ﴾ “ሸሪዓዊ እውቀትን መፈለግ (መማር) በሁሉም ሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነው።” (📚ሶሂህ አልጃሚዕ 3914)           የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ነብዩ (ﷺ) በአላህ የተጠበቁበት 34 ነገሮች።          የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith https://t.me/Amharic_Hadith

🌹ለራስሽ ቦታ ስጪ ራስሽን አትጣይ ማለት!! ተኳክለሽ ውጪ ማለት አይደለም። 🌹ቤትሽም መዋብ ትችያለሽ ለራስሽም ተዋቢ።           የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ሰባት አይነት ሰዎች ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿سَبْعَةٌ يُظِلُّهُمُ اللَّهُ في ظِلِّهِ، يَومَ لا ظِلَّ إلّا ظِلُّهُ: الإمامُ العادِلُ، وشابٌّ نَشَأَ في عِبادَةِ رَبِّهِ، ورَجُلٌ قَلْبُهُ مُعَلَّقٌ في المَساجِدِ، ورَجُلانِ تَحابّا في اللَّهِ اجْتَمعا عليه وتَفَرَّقا عليه، ورَجُلٌ طَلَبَتْهُ امْرَأَةٌ ذاتُ مَنْصِبٍ وجَمالٍ، فَقالَ: إنِّي أخافُ اللَّهَ، ورَجُلٌ تَصَدَّقَ، أخْفى حتّى لا تَعْلَمَ شِمالُهُ ما تُنْفِقُ يَمِينُهُ، ورَجُلٌ ذَكَرَ اللَّهَ خالِيًا فَفاضَتْ عَيْناهُ.﴾ “ሰባት አይነት ሰዎች አላህ ከእሱ ጥላ ውጪ ጥላ በሌለበት በቂያማ ቀን በጥላው ስር ያስጠልላቸዋል። እነሱም፦ ፍትሃዊ መሪ፣ አላህን በማምለክ ላይ ያደገ ወጣት፣ ልቡ ከመስጂዶች ጋር የተንጠለጠለን ሰው፣ ለአላህ ብለው ተዋደው በዚያም ላይ ተገናኝተው በዚያው ላይ የተለያዩ፣ የልቅናና የቁንጅና ባለቤት የሆነች ሴት (ለዝሙት) ጠርታው ‘እኔ አላህን እፈራለሁ’ ያለ ሰው፣ ምፅዋትን (ሰደቃ) የሚሰጥ ሆኖ ቀኝ እጁ የሚመፀውተውን ግራው እስከማያውቅ ድረስ የሚደብቅ ሰው፣ አላህን በማስታወስ አይኑ የሚያነባ ሰው ናቸው።" (📚ቡኻሪ 1423 ሙስሊም 1031 ዘግበውታል)           የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ጥበባዊ ምክሮች ➛ኸሊፋው ዑመር ኢብኑል ኸጣብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦ ➣እኔ ሁሉንም አይነት ጓደኞች አይቻለሁ፤ ነገር ግን ምላስን ከመጠበቅ የበለጠ ጓደኛ አላገኘሁም። ➣እኔ ሁሉንም አይነት ልብሶች አይቻለሁ፤ ነገር ግን ከተቅዋ (አላህን ከመፍራት) የበለጠ ልብሶችን አላገኘሁም። ➣እኔ ሁሉንም አይነት ሀብት አይቻለሁ፤ ነገር ግን ከመብቃቃት የበለጠ ሀብት አላገኘሁም። ➣እኔ ሁሉንም አይነት መልካም ስራዎች አይቻለሁ፤ ነገር ግን መልካም ምክር ከመስጠት የበለጠ መልካም ስራ አላገኘሁም። ➣እኔ ሁሉንም አይነት ምግብ አይቻለሁ፤ ነገር ግን እኔ ከትዕግስት (ከሶብር) የበለጠ ጣፋጭ ምግብን አላገኘሁም። https://t.me/Tbebawi_Mkroch

ወንጀል ከሰሩ በኋላ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿ما من عبدٍ يُذنِبُ ذنبًا فيُحسِنُ الطَّهورَ ثمَّ يقومُ فيُصلِّي ثمَّ يستغفرُ اللهَ إلّا غفر اللهُ له.﴾ “አንድ ባሪያ ወንጀል በሚፈፅምበት ወቅት ውዱእ በትክክል ያድርግ፡፡ ከዚያም ሁለት ረከዓዎችን ይስገድና አላህን ምህረት ይማፀን፡፡ አላህ ምህረትን ይለግሰዋል፡፡” (📚አቡ ዳውድ 1521 ቲርሚዚ 406 ዘግበውታል)         የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

አዳምጡት እስከ ነገ ማታ ድረስ የሚቆይ ነው። ከዚያ ይጠፋል።

የውዱ ነቢያችን ሙሐመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰላም ታሪክ በአጭሩ። ሁላችሁም አዳምጡት። ለሌሎችም ሼር በማድረግ አስደምጡ። የአጅሩ ተካፋይ ሁኑ።     የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Seyfedin_Apologetic

ጁሙዓ ሰለዋት ዱዓ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿إنَّ مِن أفضَلِ أيّامِكم يومَ الجُمعةِ، فأكْثِروا عليَّ الصلاةَ فيه؛ فإنَّ صلاتَكم مَعروضةٌ عليَّ.﴾ ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁሙዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በእኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለእኔ ይቀርብልኛልና። (📚አቡ ዳውድ ሰሂህ ብለውታል 1531) ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿أكثِروا الصَّلاةَ عليَّ يومَ الجمُعةِ و ليلةَ الجمُعةِ، فمَن صلّى عليَّ صلاةً صلّى اللهُ عليهِ عَشرًا.﴾ በጁሙዓ ቀንና ሌሊት በእኔ ላይ ሰለዋት ማውረድን አብዙ። በእኔ ላይ አንድን ሰለዋት ያወረደ አላህ አስር ሰለዋትን ያወርድለታል። (📚ሰሂህ አልጃሚ 1209) ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿إنّ في الجُمُعَةِ لَساعَةً، لا يُوافِقُها مُسْلِمٌ، يَسْأَلُ اللهَ خَيْرًا، إلّا أعْطاهُ إيّاهُ.﴾ በጁሙዓ ቀን አንዲት ሰዓት አለች። በዛች ሰዓት አንድ ሙስሊም አላህን መልካምን ነገር እየጠየቀ አይገጥምም፤ ለእሱ የጠየቀው የሚሰጠው ቢሆን እንጂ። (📚ሙስሊም ዘግበውታል 852) وَاذْكُرِ اسْمَ رَبِّكَ بُكْرَةً وَأَصِيلًا የጌታህን ስም በጧትና በማታ አውሳ። فَاذْكُرُونِي أَذْكُرْكُمْ وَاشْكُرُوا لِي وَلَا تَكْفُرُونِ አስታውሱኝም፤ አስታውሳችኋለሁና ለኔም አመስግኑ፤ አትካዱኝም፡፡ - «سُبْحَانَ اللهِ». - «الحَمْدُ للهِ». - «لَا إلَهَ إلَّا اللهُ». - «اللهُ أكْبَرُ». - «لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إلَّا بِاللهِ». - «لَا إلَهَ إلَّا أَنْتَ سُبْحَانَكَ إنِّي كُنْتُ مِنَ الظَّالِمِينَ». - «رَبِّ اغْفِرْ لِي وَتُبْ عَلَيَّ إنَّكَ أنْتَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ».       የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ጥበባዊ ምክሮች አል‐ኢማሙ ሻፊዒይ (رحمه الله) እንዲህ ይላሉ፦ ﴿من أحب أن يفتح الله قلبه ويرزقه العلم فعليه بالخلوة وقلة الأكل وترك مخالطة السفهاء وبعض أهل العلم الذين ليس معهم إنصاف ولا أدب﴾ “አላህ ልቡን እንዲከፍትለትና እውቀትን እንዲለግሰው የሚወድ ሰው በብቸኝነት፣ ምግብ በማቅለል እንዲሁም ከቂላቂሎችና አንዳንድ ሚዛናዊነትና አደብ ከሌላቸው የእውቀት ሰዎች ጋር ከመቀላቀል በመራቅ ላይ ያተኩር አደራውን።” 📙ቡስታኑል ዓሪፊን፡ 1/53 https://t.me/Tbebawi_Mkroch

ከኩራት ተጠንቀቁ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿لا يَدْخُلُ الجَنَّةَ مَن كانَ في قَلْبِهِ مِثْقالُ ذَرَّةٍ مِن كِبْرٍ قالَ رَجُلٌ: إنّ الرَّجُلَ يُحِبُّ أنْ يَكونَ ثَوْبُهُ حَسَنًا ونَعْلُهُ حَسَنَةً، قالَ: إنّ اللهَ جَمِيلٌ يُحِبُّ الجَمالَ، الكِبْرُ بَطَرُ الحَقِّ، وغَمْطُ النّاسِ﴾ “በልቡ ውስጥ የሰናፍጭ ፍሬ እንኳን ኩራት ያለበት ጀነት አይገባም። አንድ ሰው እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦ ሰውዬው ልብሱ ቆንጆ ጫማውም ቆንጆ እንዲሆን ይወዳል’ ይህ ከኩራት ነውን? እሳቸውም እንዲህ አሉት፦ አላህ ቆንጆ ነው ቆንጆን ነገር ይወዳል። ኩራት የሚባለው ሐቅን አለመቀበልና ሰዎችን አሳንሶ መመልከት ነው።” (📚ሙስሊም ዘግበውታል 91)      የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ምድርን የሞላ ምህረት ከአነስ ኢቢኑ ማሊክ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿يقولُ: قال اللهُ: يا ابنَ آدَمَ، إنَّك ما دَعَوْتَني ورجَوْتَني غفَرْتُ لك على ما كان فيك ولا أُبالي، يا ابنَ آدَمَ، لو بَلَغَتْ ذُنوبُك عَنانَ السَّماءِ ثمَّ استَغفَرْتَني غَفَرْتُ لك ولا أُبالي، يا ابنَ آدَمَ، إنَّك لو أَتَيْتَني بقُرابِ الأرضِ خَطايا ثمَّ لَقيتَني لا تُشرِكُ بي شَيئًا، لَأَتَيْتُك بقُرابِها مَغفرةً.﴾ “የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ የኣደም ልጅ ሆይ! ከለመንከኝና ከከጀልከኝ ባንተ ላይ ላለው (ወንጀል) ደንታ አይኖረኝም እምርልሃለሁ፡፡ የኣደም ልጅ ሆይ! ወንጀሎችህ የሰማይ ደመናን ቢደርሱ ከዚያም ምህረትን ከጠየቅከኝ እምርልሃለሁ፡፡ የኣደም ልጅ ሆይ! አንተ ምድርን ሊሞላ የቀረበ ወንጀል ጋር ብትመጣኝ፣ ከዚያ በኔ ላይ ምንም ሳታጋራ ካገኘሀኝ እሷኑ ሊሞላ የቀረበ ምህረትን ይዤ እመጣሀለሁ፡፡” (📚ቲርሚዚ ሀሰን ብለውታል 3540)          የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

የነቢያችንን ﷺ ታሪክ ማዳመጥ የፈለገ በዚህ ሊንክ ገብቶ ያዳምጥ።
👇
https://t.me/Seyfedin_Ibnu_Shifa/1494

አላህ እጆቹን ይዘረጋል ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿إنَّ اللَّهَ عَزَّ وَجَلَّ يَبْسُطُ يَدَهُ باللَّيْلِ لِيَتُوبَ مُسِيءُ النَّهارِ، وَيَبْسُطُ يَدَهُ بالنَّهارِ لِيَتُوبَ مُسِيءُ اللَّيْلِ، حتّى تَطْلُعَ الشَّمْسُ مِن مَغْرِبِها.﴾ “የላቀው አላህ በሌሊት እጆቹን ይዘረጋል። ቀን ሲያምፁት የነበሩት ወደ እርሱ እንዲመለሱ። በቀንም እጆቹን ይዘረጋል ሌሊት እርሱን ሲያምፁት የነበሩት ወደ እርሱ እንዲመለሱ። ፀሐይ በመግቢያዋ እስከምትወጣ ጊዜ ድረስ።” (📚ሙስሊም ዘግበውታል 2759)    የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith

ለፈተናዎች መከሰት ምክንያት ከሰውባን (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፦ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿يُوشِكُ الأممُ أن تداعى عليكم كما تداعى الأكَلةُ إلى قصعتِها. فقال قائلٌ: ومن قلَّةٍ نحن يومئذٍ؟ قال: بل أنتم يومئذٍ كثيرٌ، ولكنَّكم غُثاءٌ كغُثاءِ السَّيلِ، ولينزِعنَّ اللهُ من صدورِ عدوِّكم المهابةَ منكم، وليقذِفَنَّ اللهُ في قلوبِكم الوهْنَ. فقال قائلٌ: يا رسولَ اللهِ ! وما الوهْنُ؟ قال: حُبُّ الدُّنيا وكراهيةُ الموتِ﴾ “ልክ ተመጋቢዎች ማእድ ላይ እንደሚጠራሩት ህዝቦች በእናንተ ላይ ሊጠራሩባችሁ ይቀርባሉ አሉ። አንዱ ተናጋሪ ‘ያኔ እኛ ቁጥራችን ስለሚቀል ነውን?’ አላቸው ‘እንዲያውም ያኔ ብዙ ናችሁ! ነገር ግን ጉፋፊ (አረፋ) ናችሁ! ልክ ቦይ እንደሚወስደው ጉፋፊ (አረፋ)። አላህ ከጠላቶቻችሁ ልቦና ውስጥ እናንተን መፍራትን ያነሳል። ከእናንተ ልቦና ውስጥ ደግሞ ድካምን ይጥላል’ አሉ። ‘ድካሙ ደግሞ ምንድን ነው የአላህ መልእክተኛ ሆይ?!’ ሲባሉ ‘ዱንያን መውደድና ሞትን መጥላት ነው’ አሉ።” (📚አቡ ዳውድ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል: 5298)      የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Amharic_Hadith