en
Feedback
🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

Open in Telegram

እነሆ፥እኔ እላችኋለሁ፥ዓይናችሁን አንሱና እርሻው አሁን እንደ ነጣ እዩ።" — ዮሐንስ 4፥35 🔥 missional መነቃቃትን ማምጣት (Revival) 📢 የወንጌል ስምሪትን መፍጠር (Mobilization) 📖 አገልጋዮችን ለታላቁ ተልዕኮ ማብቃት (Mission) 👉 እርስዎም ባለራዕይ ከሆኑ ተቀላቅለው አብረውን ያገልግሉ!⚠️I'm missionary and mission mobilizer.

Show more
1 761
Subscribers
+4724 hours
+2857 days
+73530 days
Posts Archive
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ፣ኡሩልቾ ቃ/ሕ/ቤ/ክ እንገናኝ።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ፣ኡሩልቾ ቃ/ሕ/ቤ/ክ እንገናኝ።

የወንጌል መልእክት ያው አንድ ሆኖ ሳለ፣ባለአደራው ክርስቶስ ሕያው ሆኖ ሳለ፤የወንጌል መልእክት ለምን እንደጅማሬው ዘመን አልሆነም የሚል ጥያቄ ቢነሳ፤ልዩነቱ የመጣው አደራ ተቀባዮቹ ዘንድ ሆኖ እናገኘዋለን።የቤተክርስቲያን መሪዎች የክርስቶስ ልብ ሲኖራቸው ቅድሚያ የሚሰጡት አጀንዳ ወንጌል ይሆናል።የክርስቶስ አጀንዳ ወንጌል ነውና።መሪዎች ልባቸውን ሌላ ነገር ሲሞላው አጀንዳቸው በሚታይ ነገር ላይ መሆኑ የማይቀር ነው።​ይህን ለማረጋገጥ ቢያስፈልግ ቅድሚያ የሰጠናቸው አጀንዳዎቻችን ምን እንደሆኑ ማየት በቂ ይሆናል።በዚህ ረገድ ሁሉም ቤተክርስቲያናት በተመሳሳይ ሁኔታ ላይ ላይሆኑ ይችላሉ።ልዩነቱ የሚያመጣው የባለአደራውን ማንነት ማወቅና የተሰጠንን አደራ ምን እንደሆነ የመረዳት ደረጃችን ነው። ይህን በጥብቅ ከተገነዘብን የቅድሚያ ትኩረት የምንሰጠው አጀንዳችን የወንጌል ሥርጭት ይሆናል።ምክንያቱም የወንጌል ሥርጭት የእግዚአብሔር አጀንዳ ነውና።ስለሆነም ክርስቶስ ዛሬም በመካከላችን ሆኖ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ​ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ” ሲለን ይሰማል:: እስከ ዓለም ፍጻሜ ወንጌል መሰበክ እንዳለበት የተሰጠው ትእዛዝ ዛሬም ትኩስ ነው::​ስለዚህ የወንጌል አደራ ዛሬም ቸል የምንለው ጉዳይ አይደለም:: መጋቢ ሰሎሞን ወ/አምላክ

ከኬሪ ታሪክ የቀጠለ........ 📌ለታላቅ የሚስዮን ጥሪ የሚያነቃቃ ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጥያቄ የኬሪን ታሪክ መሠረት በማድረግ፦ ❓ዛሬ በዕለት ተዕለት የተለመደ ኑሮህ ውስጥ (ልክ ኬሪ ጫማ እንደሚጠግነው) ተወስነህ ሳለህ፤ከእግዚአብሔር ታላቅ ነገርን ጠብቅ፣ለእርሱም ታላቅ ነገርን ለማድረግ ሞክር' በሚለው እውነት ታምነህ፣ነገ የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል መለኮታዊ ተልእኮ የመጀመሪያውን የእምነት እርምጃ ከመውሰድ ወደ ኋላ የሚያስቀርህ ትልቁ ፍርሃትህ ምንድን ነው? ❓ኬሪ ጫማ በሚጠግንበት ጠበብ ያለች ክፍል ውስጥ ሆኖ የዓለምን ካርታ እየተመለከተ ያልተደረሱ ሕዝቦች ያሰብ ነበር።ዛሬ በምትሠራው የዕለት ተዕለት ሼል ወይም ባገኘኸው አነስተኛ አጋጣሚ ውስጥ ሆነህ፣ከራስህ ወሰን አልፈህ ትልቅ አህጉራዊ ወይም ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እያሰብክ ነው? ወይስ አሁን ያለህበት ሁኔታ ራዕይህን አጥቦታል?  ❓የሃይማኖት መሪዎች "አንተ ዝም በል፤እግዚአብሔር ያለ አንተም ማድረግ ይችላል" ሲሉት ኬሪ ግን አልተቀበላቸውም። በውስጥህ የተቀመጠውን ታላቅ ዓላማ "አይቻልም"፣"አቅም የለህም" ወይም "የአንተ ሼል አይደለም" ብለው የሚገታቱህ ድምፆች ሲበዙ፣ድምፃቸውን ሰብረህ የመራመድ ቆራጥነት አለህ? ❓ለምትኖርለት ዓላማ ወይም ለጀመርከው መልካም ሼል ላብህንና ጥረትህን አፍስሰህ ለረጅም ጊዜ ምንም ዓይነት ውጤት ባታይ፣ተስፋ ሳትቆርጥ እስከ መጨረሻው የመቆም እምነት እና ጽናት አለህ? ❓ዛሬ በሕይወትህ እግዚአብሔርን አምነህ ለመውሰድ የምትፈራው፣ነገር ግን ካደረግከው የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል "ታላቅ የእምነት እርምጃ" (Risk) ምንድን ነው? ❓ የአንተ መኖር እና መሰጠት ለአካባቢህ ማኅበረሰብ የሚያመጣው ተልዕኮዊ ለውጥ ምንድን ነው? ከእኔነት አልፈህ ለትውልድ የሚሻገር ምን አሻራ እየጣልክ ነው? 💫​እውነተኛ ሚስዮን (ጥሪ) ማለት የተቀመጥንበትን ምቾት ትታን የሌሎችን ሕይወት ለመለወጥ የሚደረግ ታላቅ ጉዞ ነው። 🧠 ሚሲዮናዊ አስተሳሰብ አላችሁ?     📢ሚሲዮናዊ ናችሁ?

ውዶቼ ፕሮግራም ተጀምሯል ኑ

ውዶቼ ዛሬ 3:00 ላይቭ አይቀርም እሺ፤ ታላቁ ተልእኮ በዘጸአት መጽሐፍ ምን እንደሚመስል በዝርዝር እንመለከታለን። ሼር በማድረግ ይህንን አገልግሎት አስፉ፤ጸጋ ይብዛላችሁ! 🔥እግዚአብሔር እውነተኛ የሆነ የወንጌል ስርጭት Revival ያመጣል!🔥

የዊሊያም ኬሪ አስገራሚ ታሪክ ዊሊያም ኬሪ በ18ኛው እና 19ኛው ክፍለ ዘመን (1761–1834) የኖረ እንግሊዛዊ ሲሆን፣በዓለም አቀፍ ደረጃ "የዘመናዊ ሚስዮን አባት" (The Father of Modern Missions) በመባል ይታወቃል። ኬሪ የተወለደው በድሃ ቤተሰብ ውስጥ ሲሆን፣ኑሮውን የሚመራው ጫማ በመጠገን (Shoemaker) ነበር።ይሁን እንጂ በውስጡ ከፍተኛ የሆነ የትምህርት ጥማት ነበረው።ጫማ እየጠገነ በተመሳሳይ ሰዓት መጽሐፍትን በማንበብ ላቲን፣ግሪክ፣ዕብራይስጥ፣ጣሊያንኛ፣ደች እና ፈረንሳይኛ ቋንቋዎችን በራሱ ጥረት በሚገባ አጠና። ኬሪ የዓለምን ካርታ እየተመለከተ ወንጌል ላልደረሰባቸው ሕዝቦች ትልቅ ሸክም ይሰማው ጀመር።በወቅቱ የነበሩ የሃይማኖት መሪዎች "እግዚአብሔር አሕዛብን ማዳን ከፈለገ ያለ እኛ እርዳታ ያደርገዋል" ብለው ራዕዩን ሲቃወሙት፣እርሱ ግን እንዲህ የሚል ታሪካዊ አባባል ተናገረ፡- ​"ከእግዚአብሔር ታላላቅ ነገሮችን ጠብቅ፤ ለእግዚአብሔር ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ ሞክር።" (Expect great things from God; attempt great things for God.) በ1793 ዓ.ም ኬሪ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ሕንድ አገር ተጓዘ።በዚያም እጅግ ከባድ ፈተናዎች ገጠሙት። የገንዘብ እጥረት፣አደገኛ በሽታዎች፣የአንዱ ልጁ ሞት፣እንዲሁም የባለቤቱ የአእምሮ ጤና መታወክ ተደራረቡበት።ከዚህ ሁሉ መከራ ጋር ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ለዓመታት ሰርቷል።ለሰባት ዓመታት ያህል ሰብኮ አንድም ሰው ወደ እምነቱ አልመጣም ነበር፤ነገር ግን ወደ ኋላ አላለም። 📌ለታላቅ የሚስዮን ጥሪ የሚያነቃቃ ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጥያቄ፦ ❓ዛሬ በዕለት ተዕለት የተለመደ ኑሮህ ውስጥ (ልክ ኬሪ ጫማ እንደሚጠግነው) ተወስነህ ሳለህ፤ከእግዚአብሔር ታላቅ ነገርን ጠብቅ፣ለእርሱም ታላቅ ነገርን ለማድረግ ሞክር' በሚለው እውነት ታምነህ፣ነገ የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል መለኮታዊ ተልእኮ የመጀመሪያውን የእምነት እርምጃ ከመውሰድ ወደ ኋላ የሚያስቀርህ ትልቁ ፍርሃትህ ምንድን ነው? ❓ኬሪ ጫማ በሚጠግንበት ጠበብ ያለች ክፍል ውስጥ ሆኖ የዓለምን ካርታ እየተመለከተ ያልተደረሱ ሕዝቦች ያሰብ ነበር።ዛሬ በምትሠራው የዕለት ተዕለት ሼል ወይም ባገኘኸው አነስተኛ አጋጣሚ ውስጥ ሆነህ፣ከራስህ ወሰን አልፈህ ትልቅ አህጉራዊ ወይም ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እያሰብክ ነው? ወይስ አሁን ያለህበት ሁኔታ ራዕይህን አጥቦታል? ❓የሃይማኖት መሪዎች "አንተ ዝም በል፤እግዚአብሔር ያለ አንተም ማድረግ ይችላል" ሲሉት ኬሪ ግን አልተቀበላቸውም። በውስጥህ የተቀመጠውን ታላቅ ዓላማ "አይቻልም"፣"አቅም የለህም" ወይም "የአንተ ሼል አይደለም" ብለው የሚገታቱህ ድምፆች ሲበዙ፣ድምፃቸውን ሰብረህ የመራመድ ቆራጥነት አለህ? ❓ለምትኖርለት ዓላማ ወይም ለጀመርከው መልካም ሼል ላብህንና ጥረትህን አፍስሰህ ለረጅም ጊዜ ምንም ዓይነት ውጤት ባታይ፣ተስፋ ሳትቆርጥ እስከ መጨረሻው የመቆም እምነት እና ጽናት አለህ? ❓ዛሬ በሕይወትህ እግዚአብሔርን አምነህ ለመውሰድ የምትፈራው፣ነገር ግን ካደረግከው የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል "ታላቅ የእምነት እርምጃ" (Risk) ምንድን ነው? ❓ የአንተ መኖር እና መሰጠት ለአካባቢህ ማኅበረሰብ የሚያመጣው ተልዕኮዊ ለውጥ ምንድን ነው? ከእኔነት አልፈህ ለትውልድ የሚሻገር ምን አሻራ እየጣልክ ነው? 💫​እውነተኛ ሚስዮን (ጥሪ) ማለት የተቀመጥንበትን ምቾት ትታን የሌሎችን ሕይወት ለመለወጥ የሚደረግ ታላቅ ጉዞ ነው። 🧠 ሚሲዮናዊ አስተሳሰብ አላችሁ?     📢ሚሲዮናዊ ናችሁ?

የእግዚአብሔር አጀንዳ ወንጌል ስለሆነ፤የእግዚአብሔርን ሃሳብ ለማገልገል የተመረጠች ቤተክርስቲያንም አጀንዳዋ ወንጌልና ወንጌል ብቻ መሆን አለበት። ❓ግን እሺ በእርግጥ በአሁኑ ጊዜ የቤተክርስቲያን ዋና አጀንዳ ምን ይሆን? ❓ታዲያ የቤተክርስቲያን በጀት ምን ያህሉ ለወንጌል ሥርጭት ተመድቦ ይሆን? ❓ቤተክርስቲያን በአካባቢዋ ወንጌልን ለማድረስ ምን ዓይነት ዕቅዶችን አውጥታለች? ወዳጆቼ ስለ ክርስቶስ መመስከር ልማድ አድርገን ከልሆነ በለመመስከራችን ምን ላይሰማን ይችላል ።

ቅዱሳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ ••••••••••••••••••••••••••••••••• እዚህ ቤት ስለ እግዚአብሔር ታላቁ ተልእኮ ብቻ ነው የሚወራው፤ከተለያዩ ሚሲዮናዊ ሀሳቦችና ሚሽነሪዎች ጋር የመገናኘት ዕድል የሚፈልግ ሁሉ ሰው ይቀላቀል!👇 ለ አምስት ሰው ሼር አድርጉ፤ፀጋ ይብዛላችሁ! https://t.me/onegodtruth

🧵የእግዚአብሔር ተልዕኮ በኦሪት ዘፍጥረት ውስጥ፦ በዘፍጥረት መጽሐፍ እግዚአብሔር ሰዎችን ወደ ዓለም ሁሉ የመላክ፣የመባረክና ስሙን የማስታወቅ ታላቅ ዓላማውን (Missio Dei) የጀመረበትን ምስል እናኛለን። [🙌  ] እግዚአብሔር ሰዎችን ፍለጋ የመውጣቱ ምልክት (ዘፍ 3፥9) ተመልከት። ♪♪♪የመጀመሪያው ጥሪ፦ ሰው ኃጢአት በሠራ ጊዜ እግዚአብሔር ሰውን ፍለጋ ወጥቶ “ወዴት ነህ?” አለው። ​♪♪♪የሚሽን መሠረት፦የሚሽን ዋናው መነሻ እግዚአብሔር ልሹ የጠፋውን የሰውን ልጅ ፍለጋ የሚወጣ (Missionary God) መሆኑን ነው።ተመልከቱ የምስራቹን ወንጌል የምስራች ብሎ የጀመረው እግዚአብሔር እራሱ ነው፤ይህ ደግሞ ለታላቁ ተልዕኮ ትልቅ መሠረት ጥሏል። ❄️የተልዕኮ ዝርዝሮች በኦሪት ዘፍጥረት ውስጥ፦ [ 1 ] የኖኅ መርከብና የምድር ሁሉ ዳግም መነሻ (The Rescue Station) ዘፍጥረት 6-9 ,,♪♪♪♪,,ዓለም በኃጢአት በጠፋች ጊዜ እግዚአብሔር ኖኅን መርጦ መርከብ እንዲሠራ አዘዘው።መርከቧ ፍጥረት ሁሉ ከጥፋት የደነባት የመጀመሪያዋ የማዳኛ ማዕከል ስትሆን፣ከጥፋት ውኃ በኋላ የተሰጠው “ምድርን ሙሉአት” የሚለው ትእዛዝ የእግዚአብሔር ስም በምድር ሁሉ እንዲታወቅ ያለውን ፍላጎት ያሳያል። [ 2 ] የሕዝቦች መበተንና የባሕል መፈጠር (The Challenge)ዘፍጥረት 11፥1-9     ♪♪♪♪የሰው ልጅ በአንድ ቦታ ተወስኖ እግዚአብሔርን ለመጋፈጥ በባቤል ግንብ ላይ በaccumulate ባደረገ ጊዜ፣እግዚአብሔር ቋንቋቸውን በመደባለቅ ወደ ምድር ሁሉ በተናቸው።ይህ መበተን በኋላ ላይ ለሚደረገው የዓለም አቀፍ ሚሽን (የተለያዩ ቋንቋዎችንና ሕዝቦችን የመድረስ) መድረክ ሆነ። [ 3 ] የዓለም አቀፋዊው ሚሽን ስምሪት (The Mandate of international mission)ዘፍጥረት 12፥1-3 ♪♪♪♪እግዚአብሔር አብርሃምን ከአገሩና ከምቾቱ ለይቶ ወደማያውቀው ምድር እንዲሄድ (Send እንዲሆን) ጠራው።ዋናው ዓላማውም “የምድር ነገዶች ሁሉ በአንተ ይባረካሉ” የሚል ሲሆን፣ይህ በብሉይ ኪዳን የዓለም አቀፍ ሚሽን ታላቁ ስምሪት ነው። [ 4] ያዕቆብ በስደት ምድር መባረኩ (Diaspora Mission) ዘፍጥረት 28-31 ያዕቆብ ወንድሙን ፈርቶ ወደ ባዕድ አገር (ሀረን) በተሰደደ ጊዜ እግዚአብሔር አብሮት ወጣ። ያ በሰው እይታ ስደት የነበረው ጉዞ፣ እግዚአብሔር የኪዳኑን ሕዝብ ያበዛበትና ስሙን በሌላ ምድር ያስተዋወቀበት መለኮታዊ የስደት (Diaspora) ስልት ነበር። [ 5 ] የሚሽን ኪዳን ለቀጣዩ ትውልድ መተላለፉ (The Continuity of mission covenant) ዘፍጥረት 26፥4 እና 28፥14 ♪♪♪♪ይህ ሁሉንም አሕዛብ በበረከት የመድረስ የሚሽን ዓላማ ከአብርሃም በኋላ ለልጁ ለይስሐቅ፣ከዚያም ለያዕቆብ በተመሳሳይ ቃል ተላለፈ።እግዚአብሔር ለሚሽን ያለው ዓላማ በትውልድ መካከል የማይቋረጥ መሆኑን ያሳያል። [ 6 ] ሕይወትን ለማዳን ወደ ባዕድ አገር መላክ (The Strategic Sending of Mission) ዘፍጥረት 45፥5-8 ♪♪♪♪በመጽሐፉ ማጠቃለያ ላይ የዮሴፍን ታሪክ እናገኛለን።ዮሴፍ በብዙ መከራ አልፎ ግብፅ ከደረሰ በኋላ፣ወንድሞቹን ሲያገኛቸው “ሕይወትን ለማዳን እግዚአብሔር ከፊታችሁ ሰደደኝ (ላከኝ)” በማለት፣እግዚአብሔር ሰዎችን ለብዙዎች መዳን ሲል ወደ ባዕድ ሕዝብና ባህል አስቀድሞ እንደሚልክ (Missionary Deployment) በተግባር አሳይቷል። ይቀጥላል...

ወዳጆቼ ነገ ቸርች እንዳትቀሩ፣ከሄዳችሁ ደግሞ ምናልባት ሀሳቡ ባይነሳ እንኳን በግላችሁም ቢሆን በወንጌል ስላልተደረሰ አንድ የህዝብ ክፍል ጸልዩ! ደህና እደሩ        •••••••••••••••••••••••••••••

ውዶቼ ዛሬ 3:00 ላይቭ አይቀርም እሺ፤ ስለ ታላቁ ተልእኮ ሁለቱ ገጽታዎች በዝርዝር እንመለከታለን። ሼር በማድረግ ይህንን አገልግሎት አስፉ፤ ጸጋ ይብዛላችሁ!

ተልእኳዊ የጸሎት፣የዝማሬና የቃል ጊዜ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ​ዛሬ ማታ እንደተለመደው ተልዕኮዊ የጸሎት፣የዝማሬና የቃል ጊዜ ይኖረናል። ከምሽቱ ሦስት ሰዓት(3:00-4:00) እስከ አራት ሰዓት በዚህ ቻናል በቀጥታ ስርጭት እናደርጋለን። ለሌሎችም ሼር አድርጉ፤ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

​🔔 ማንቂያ ደወል፡የ2019 ዓ.ም እቅዳችን እና የታላቁ ተልዕኮ ጉዳይ! ​እሺ፣የእግዚአብሔር ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ ወዳጆቼ! 🙏 እንግዲህ ባለፈው ስለ 2018 ዓ.ም የወንጌል ስርጭት ግምገማ ለማንሳት ሞክሬ ነበር።በክፍል አንድ ሁላችንም ራሳችንን አይተናል ብዬ አስባለሁ፤ከወዴት እንደወደቅንም ምናልባት አውቀናል ብዬ አምናለሁ።አሁንም የምለው፤ከወዴት እንደወደቅን ያስታውሰን እግዚአብሔር... 😔 ​አሁን ደግሞ እስኪ ስለ 2019 ዓ.ም እቅዶቻችን እናውራ።🗓️ በእርግጥ አሁን የዚህ ዓመት እቅድ የሚዘጋበት ጊዜ ላይ ሊባል በሚችል ደረጃ ተቃርበናል።አሁን ጊዜው ወደፊት የምናቅድበት ጊዜ ነው፤ማለትም ለመዝራት የምንዘጋጅበት ጊዜ ማለት ነው።ታዲያ በመጪው ዓመት ምን መዝራት ነው የምትፈልጉት? 🌱 ምክንያቱም ልትዘሩት የምትፈልጉትን ራሱን ዘር ማቀድ አለባችሁና።ካልሆነ ልትዘሩ የምትፈልጉትና ፍጆታችሁን የምታውሉበት ካልተመሳሰለ፣እመኑኝ የኪሳራ ዓመት ነው የሚሆንባችሁ።📉 መሬቱም በሚገባ ተፈትሾ በደንብ ሊዘጋጅ ይገባል።ለምን ካላችሁኝ፤አንዳንድ ጊዜ ዘሩ ችግር ባይኖርበትም ከመሬቱ የተነሳ ተመሳሳይ ዘር የማደግ፣የመበላሸት፣የማፍራት እና የማፍረክረክ እድል ሊያጋጥመው ይችላል። 🍂 ​ለዚህም ነው በነገራችን ላይ የታላቁ ተልዕኮ ጉዳይ አንዳንዱ ጋር በጣም ተራና በትርፍ ጊዜ፣በትርፍ ብር፣በአጠቃላይ በትርፍ ነገር የሚሰራ መስሎ የሚታየው።⚠️ ይሄ እራሱ አንዳንዱ ጋር ደግሞ የመኖሩ ብቸኛ ዓላማ ነው።ኑሮውን ሲያስብ ለዚህ ጉዳይ ብቻ ሲሆን፣ሌሎች ነገሮች ሁሉ በእግረ መንገድ የሚያደርጋቸው ነገሮች ናቸው፤ማለትም ታላቁን ተልዕኮ ለማገዝ ብቻ ማለቴ ነው። ስለዚህ እናንተስ ከየትኛው ወገን ናችሁ? ከወዴት እንደወደቅን እግዚአብሔር ያመልክተን! 🧭 እሺ፣አሁን የቤተክርስቲያን አመራር (Leadership) የዚህን ዓመት ሪፖርት በማሰራት እና የመጪውን ደግሞ ለማቀድ በብዙ ርብርብ ላይ ነው።እኔንም በጸሎታችሁ አስቡኝ፣በሁለት ቤተክርስቲያን ጥናት (Research) ሰርቼ በቅርቡ ስለዚሁ ዓመት የወንጌል ስርጭት "እንሆ" ልላችሁ ነው።📊 በእርግጥ እግዚአብሔር ይርዳኝ፣መገፋትንም ጨምሮ በጣም ፈተናዎች አሉት።ግን ለወንጌል እስከሆነ ደህና ነው! ዛሬ የምጠይቀው ጥያቄ በጣም አጭር ነው፣ዝርዝሩን ለሌላ ጊዜ ትቼዋለሁ! ​❓ ለመጪው ዓመት የታላቁ ተልዕኮ ጉዳይ በስንተኛ ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው ከእቅዶቻችን መካከል? ❓ ስለዚህ ጉዳይ መቼ ጸሎት ታሰበ? ❓ መቼስ ዝርዝር ስብሰባ ሊደረግ ነው? ❓ መቼስ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ሊሰራ ነው መጪው ዓመት ቤተክርስቲያን ያሉ ሰዎች ታላቁ ተልዕኮ ላይ እንዲያተኩሩ? ​እኔ አሁን በማገለግልበት ቤተክርስቲያን፣እንደ ሀገር ብዙ ሕጎች እየወረዱ ይገኛሉ፤ስለ ወንጌል ስርጭትስ ምንድነው የሚወርደው? ማንቂያ ደወል 🔔፣ቤተክርስቲያን በምድር ላይ የመኖሯ ብቸኛ ዓላማ እርሱ እንደሆነ አመልካች ነገር? ​"አንተ የምትተኛ ንቃ፥ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል።" (ኤፌሶን 5፥14) ✨

አለኝ ቀጠሮ •••••••••••• ​አለኝ ቀጠሮ (፪x) ኢየሱስ ከሚባል እንግዳ እስኪ ልነሳ ቤቴን ላሰናዳ (፪x) ፓስተር ታምራት ኃይሌ

የዚህ አገልግሎት ዋና ዓለማ •••••••••••••••••••••••••••••• ብዙ ሰዎች ስለ ሚሽን በምጽፋቸው ጽሑፎች ላይ ከብዙዎች ዘንድ የተሳሳተ እይታ ተመልክቻለሁ።የትኛውም የምጽፋቸው ጽሑፎች አንዳቸውም ከቤተክርስቲያን ስህተት መፈለግ አይደለም፤ይልቁንም ቤተክርስቲያንን ለታላቁ ተልዕኮ ማነሳሳት ነው።ክፍተቶችን በማሳየት ያንን ክፍተት እንዳይደገም አስተዋጽኦ ማድረግ ነው እንጂ ሌላ ምንም ዓላማ የለውም።ይህን አገልግሎት በእውነት የምትደግፉ ሰዎች ሼር (Share) በማድረግ ከአገልግሎታችን ጎን ቁሙ!

​"ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች።" (ዮሐንስ 9፥4)
በ40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር ከመሞቷ በፊት በዓለም ታዋቂው ዲዛይነር እና ደራሲ “ክሪስዳ ሮድሪጌዝ” እንዲህ ስትል ፅፋለች። 1. ጋራዥ ውስጥ የአለማችን ውድ መኪና ነበረኝ፣አሁን ግን በዊልቸር መንቀሳቀስ አለብኝ። 2. ቤቴ ሁሉንም አይነት ብራንድ ያላቸው ልብሶች፣ጫማዎች እና ውድ እቃዎች ይሸጣል፣አሁን ግን ሰውነቴ በሆስፒታሉ በተዘጋጀ ትንሽ ጨርቅ ተጠቅልሏል። 3. በባንክ ውስጥ ብዙ ገንዘብ አለኝ። አሁን ግን ከዚህ መጠን ምንም አልጠቀመኝም። 4. ቤቴ እንደ ቤተ መንግስት ነበር አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ በሁለት አልጋዎች ተኝቻለሁ። 5. ከባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ወደ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል. አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ ከአንድ ላብራቶሪ ወደ ሌላ በመንቀሳቀስ ጊዜዬን አሳልፋለሁ 🦋 በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ፊርማ ሰጥቻለሁ ነገርግን በዚህ ጊዜ የሕክምና መዝገቦች የእኔ ፊርማ ናቸው። እ.ኤ.አ. . ፀጉሬን ለመስራት ሰባት ፀጉር አስተካካዮች ነበሩኝ ፣አሁን ግን - በራሴ ላይ አንድ ፀጉር የለኝም። ፨ በግል ጄት ላይ፣የትኛውም ቦታ መብረር እችላለሁ፣አሁን ግን ወደ ሆስፒታል በር ለመራመድ ሁለት እርዳታዎች ያስፈልጉኛል። ፨ ምንም እንኳን ብዙ ምግቦች ቢኖሩም, አሁን የእኔ አመጋገብ በቀን ሁለት ጽላቶች እና ምሽት ላይ ጥቂት የጨው ውሃ ጠብታዎች ናቸው። ይህ ቤት፣ ይህ መኪና፣ይህ አውሮፕላን፣ይህ የቤት ዕቃ፣ይህ ባንክ፣ብዙ ዝና፣አንዳቸውም አይመጥኑኝም። ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም አያዝናኑኝም። ወዳጄ ቀን ሳለ ለእግዜር ታላቅ ለመንግሥት ጉዳይ ሊኖረን ይገባናል፤ምክንያቱም ወጣትነታችን ብዙ ነገራችንን የሚከዳን ጊዜ ይመጣልና!

በጣም ይቅርታ ቅዱሳን ለዛሬ የነበረውን ፕሮግራም ለማድረግ አልቻልንም ስለ ተፈጠረው ክፍተት በጣም ይቅርታ አርብ እንገኛለን🙏 መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ!