en
Feedback
🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥

Open in Telegram

እነሆ፥እኔ እላችኋለሁ፥ዓይናችሁን አንሱና እርሻው አሁን እንደ ነጣ እዩ።" — ዮሐንስ 4፥35 🔥 missional መነቃቃትን ማምጣት (Revival) 📢 የወንጌል ስምሪትን መፍጠር (Mobilization) 📖 አገልጋዮችን ለታላቁ ተልዕኮ ማብቃት (Mission) 👉 እርስዎም ባለራዕይ ከሆኑ ተቀላቅለው አብረውን ያገልግሉ!⚠️I'm missionary and mission mobilizer.

Show more
1 747
Subscribers
+5024 hours
+2697 days
+68730 days
Posts Archive
​ቅዱሳን ዛሬ ማታ እንደጀመርነው ተልዕኮው የጸሎት እና የትምህርት ጊዜ ይኖረናል። በስደት ስለተስፋፋው የወንጌል ስርጭት ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እናያለን፤ሼር አድርጉ፣ተባረኩ! ወደዚህ ቻናል ያልገባችሁ ደግሞ ተቀላቀሉን🙏

ወዳጆቼ ኢየሱስ ክርስቶስን ከሰማይ ክብር ለወረደ ታላቁ ተልዕኮ እኛ መሰናከያ እንዳንሆን ጸጋው ይርዳን ምክንያቱም ይህንን ተልዕኮ ባንሰራ እንኳን መሰናከያ ልንሆን አይገባምና!

ተልእኳዊ የጸሎት ጊዜ •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ​ዛሬ ማታ እንደተለመደው ተልዕኮዊ የጸሎት፣ጊዜ ይኖረናል። ከምሽቱ ሦስት ሰዓት(3:00-4:00) እስከ አራት ሰዓት በዚህ ቻናል በቀጥታ ስርጭት እናደርጋለን። ለሌሎችም ሼር አድርጉ፤ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

የክርስቶስ መሞት ካልደበዘዘብን፣ተልዕኮው አይደበዝዝብንም። ክርስቶስ ኢየሱስ ከፊታችን እንደተሰቀለ ሆኖ የሚኖር ከሆነ፤ስለ ታላቁ ተልእኮ ጉዳይ በፍጹም ሊደበዝዝብንና ዓይናችንን፣ብራችንንና ጉልበታችንን በሌሎች ተጨማሪ ነገሮች ላይ አናውልም ነበር። ምክንያቱም ሚስዮናዊነት ክርስቶስን ደጋግሞ ማየት፣መሞቱንና መነሳቱን ዘወትር ማስታወስ የሚፈልግ ጉዳይ ነው።ስለዚህ ራሳችንን መመልከት ያስፈልገናል።የታላቁ ተልእኮ ጉዳይ ደብዝዞብን ይሆን? ወይስ በእኛ ዘንድ ትኩረት አግኝቷል?

ተልዕኮ የሁሉም እንጂ የ'ኢቫንጅ ቲም' አይደለም! እግዜር አንድያ ልጁን አሳልፎ የሰጠው ለተልዕኮ ጉዳይ ነው።ስለዚህ ዛሬም ቢሆን የእግዜር ተልዕኮ ለትውልድ ሁሉ ኢየሱስን መናገር፣የምስራች ከኃጢአት ያድናል ማለት ስለሆነ፤ስላልተደረሱት ማለትም ኢየሱስ ከዘላለም ፍርድ እንደሚያድን ላልሰሙት ቅድሚያ ልንሰጥ ይገባናል።ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደምለው ሁሉ፣ይሄ የሁለት ሺህ ዘጠኝ ዓ.ም የኢቫንጅ ቲም እቅድ ብቻ ሳይሆን የአማኝ ሁሉ የመጀመሪያና በጣም አንገብጋቢ አጀንዳ ሊሆን ይገባል።በመሠረቱ የኢቫንጅ ቲም ደግሞ ሊኖረን አይገባም ምክንያቱም የሆነ ለሚሽን ጉዳይ የተመረጡ ቡድኖች የሉምና።«ኢቫንጅ ቲሞች» ተብለው በተለምዶ የሚጠሩትም አመለካከታቸውን አስተካክለው፣ሚሽን እራሳቸውን ለብቻቸው እንደሚመለከታቸው ሳይሆን የሁሉም ግዴታ እንደሆነ በመረዳት ማስተባበር አለባቸው።ይሄንን የምለው ዝም ብዬ አይደለም፤'ኢቫንጅ ቲም' የሚለው ሀሳብ ብዙዎች የወንጌል ጉዳይ የሚመለከታቸው እነርሱ ብቻ እንደሆኑ በማሰብ እጅ አጣጥፈው እንዲቀመጡ አድርጓል ብዬ አምናለሁ፤ደግሞም በቸርች ውስጥ አስተውዬዋለሁ! ስለዚህ ኢቫንጅ ቲም የሚባል ነገር ለማስተባበር ካልሆነ በቀር ይታሰብበት! ስላሴያው ነኝ በጸሎታችሁ አስቡኝ። መልካም ቀን               ••••••••••••••••

ሰላም እንዴት ነችሁ ቅዱሳን ዛሬ ፕሮግራም ላይ ስለነበርኩ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ማድረግ አልቻልኩም ይቅርታ፤ፕሮግረማችን አርብ ይቀጥላል

ሁላችንም ሚስዮናውያን ብንሆን ኖሮ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ነግረነቸው ወደ ጌታ የመጡት ሚስዮናውያን ይሆኑ ነበር፤ ኢየሱስ እርሱ እራሱ ሚስዮናዊ ስለነበር ጠርቶ ያመጣው ደቀመዝሙርት ሁሉ ሚስዮናውያን ነበሩ፤ሕይወታቸውንም ሰጥተው የጨረሱት ለዚህ አገልግሎት ነበር፤ሚስዮናዊናት መሞትም አለበትና። መልካም ቀን ••••••••••••••••

ቤተክርስቲያን የግዴታ outreach መሠረት ያለበትን አከባቢ እና inreach(ደቀመዝሙር የማድረግ ሥራ መሠረት ያለበትን አከባቢ ለይታ መሥራት መቻል አለበት ምክንያቱም አንዳንድ ቦታዎች ደቀመዝሙር የማድረግ ሥራ ብቻ በመሥራት ተልእኮው ስኬታማ የሚሆንበት ሁኔታ እያለ outreach ላይ ጊዜ፣ጉልባትና ብር ማባከን የለብንም ስለዚህ የሥርጭት አከባቢዎችን ስንመርጥ የትኛው አካባቢ outreach እንደሚያስፈልግ እናም የትኛው ቦታ ደቀመዝሙር የማድረግ ሥራ እንደሚያስፈልግ መለያት አለብን! ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ🙌

እጅግ በጣም ድንቅ መዝሙር ነው አድምጡት!🔥 https://youtu.be/57NCd1yPACs?si=yqnrEjWJo4LoJIJX

ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለላትን ዋጋ ሁልጊዜ የምታስታውስ ቤተክርስቲያን የእግዜርን ተልእኮ ከምንም ነገር ታስቀድማለች።ቤተክርስቲያን ግን የጌታን የኢየሱስ ሞት እየዘነጋች በሄደች ቁጥር ትኩረቷ ሌላ ቁሳቁስ ይሆናል፤የምታደርገውን ሁሉ ደግሞ ታላቁን ተልእኮ መሠረት ባደረገ መልኩ ማድረጓን ትታ በፕሮግራም ብዛት የተወጣጠረች ትሆናለች።ሁሌም ሚሲዮናዊት ቤተክርስቲያን የእግዜርን ተልእኮ ታስቀድማለች!

👉እንግዳ፡ ሚስዮናዊ አበራ ዶታሞ (ከሃያ ዓመታት በላይ በሚስዮናዊነት ያገለገሉ) 👉አሁን ማታ ከ 3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት ​ 👉በዚህ ቻናል 🎯​(ፕሮግራሙ እንዳያመልጣችሁ፣ለሌሎችም አሁኑኑ ያጋሩ!)

📌ከሚስዮናዊ አበራ ዶታሞ ጋር የምስክርነት ጊዜ። ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ ቅዱሳን! ​ዛሬ ቃል ገብቼ እንደነበረው ከሚስዮናዊ ጋር ስለ ወንጌል ተልዕኮ የምንወያይበት ልዩ ፕሮግራም ይዘንላችሁ ቀርበናል። በተለይም አገልጋዩ ለሃያ ዓመታት ሚስዮናዊ ሆኖ እያገለገለ የቆየ እንደመሆኑ መጠን፤ሚስዮናዊነት ምን እንደሚመስል በሰፊው እናነሳለን፤እንዲሁም መንፈሳዊ ቅንዓታችንን እንካፈላለን። ​ይህንን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ፕሮግራማችሁን አስተካክላችሁ እንድትጠብቁን በጌታ ፍቅር እናሳስባለን። የወንጌል ተልዕኮ ራዕይና ሚስዮናዊ አስተሳሰብ ያለውን ትውልድ ለመፍጠር አብረን እንታገላለን፤እግዚአብሔር ደግሞ እውነተኛ የወንጌል ስርጭት መነቃቃትን ያስነሳል! ​ እንግዳ፡ ሚስዮናዊ አበራ ዶታሞ (ከሃያ ዓመታት በላይ በሚስዮናዊነት ያገለገሉ) 👉ዛሬ ማታ ከ 3፡00 እስከ 4፡00 ሰዓት ​ 👉በዚህ ቻናል 🎯​(ፕሮግራሙ እንዳያመልጣችሁ፣ለሌሎችም አሁኑኑ ያጋሩ!)

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ፣ኡሩልቾ ቃ/ሕ/ቤ/ክ እንገናኝ።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ፣ኡሩልቾ ቃ/ሕ/ቤ/ክ እንገናኝ።

የወንጌል መልእክት ያው አንድ ሆኖ ሳለ፣ባለአደራው ክርስቶስ ሕያው ሆኖ ሳለ፤የወንጌል መልእክት ለምን እንደጅማሬው ዘመን አልሆነም የሚል ጥያቄ ቢነሳ፤ልዩነቱ የመጣው አደራ ተቀባዮቹ ዘንድ ሆኖ እናገኘዋለን።የቤተክርስቲያን መሪዎች የክርስቶስ ልብ ሲኖራቸው ቅድሚያ የሚሰጡት አጀንዳ ወንጌል ይሆናል።የክርስቶስ አጀንዳ ወንጌል ነውና።መሪዎች ልባቸውን ሌላ ነገር ሲሞላው አጀንዳቸው በሚታይ ነገር ላይ መሆኑ የማይቀር ነው።​ይህን ለማረጋገጥ ቢያስፈልግ ቅድሚያ የሰጠናቸው አጀንዳዎቻችን ምን እንደሆኑ ማየት በቂ ይሆናል።በዚህ ረገድ ሁሉም ቤተክርስቲያናት በተመሳሳይ ሁኔታ ላይ ላይሆኑ ይችላሉ።ልዩነቱ የሚያመጣው የባለአደራውን ማንነት ማወቅና የተሰጠንን አደራ ምን እንደሆነ የመረዳት ደረጃችን ነው። ይህን በጥብቅ ከተገነዘብን የቅድሚያ ትኩረት የምንሰጠው አጀንዳችን የወንጌል ሥርጭት ይሆናል።ምክንያቱም የወንጌል ሥርጭት የእግዚአብሔር አጀንዳ ነውና።ስለሆነም ክርስቶስ ዛሬም በመካከላችን ሆኖ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ​ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ” ሲለን ይሰማል:: እስከ ዓለም ፍጻሜ ወንጌል መሰበክ እንዳለበት የተሰጠው ትእዛዝ ዛሬም ትኩስ ነው::​ስለዚህ የወንጌል አደራ ዛሬም ቸል የምንለው ጉዳይ አይደለም:: መጋቢ ሰሎሞን ወ/አምላክ

ከኬሪ ታሪክ የቀጠለ........ 📌ለታላቅ የሚስዮን ጥሪ የሚያነቃቃ ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጥያቄ የኬሪን ታሪክ መሠረት በማድረግ፦ ❓ዛሬ በዕለት ተዕለት የተለመደ ኑሮህ ውስጥ (ልክ ኬሪ ጫማ እንደሚጠግነው) ተወስነህ ሳለህ፤ከእግዚአብሔር ታላቅ ነገርን ጠብቅ፣ለእርሱም ታላቅ ነገርን ለማድረግ ሞክር' በሚለው እውነት ታምነህ፣ነገ የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል መለኮታዊ ተልእኮ የመጀመሪያውን የእምነት እርምጃ ከመውሰድ ወደ ኋላ የሚያስቀርህ ትልቁ ፍርሃትህ ምንድን ነው? ❓ኬሪ ጫማ በሚጠግንበት ጠበብ ያለች ክፍል ውስጥ ሆኖ የዓለምን ካርታ እየተመለከተ ያልተደረሱ ሕዝቦች ያሰብ ነበር።ዛሬ በምትሠራው የዕለት ተዕለት ሼል ወይም ባገኘኸው አነስተኛ አጋጣሚ ውስጥ ሆነህ፣ከራስህ ወሰን አልፈህ ትልቅ አህጉራዊ ወይም ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እያሰብክ ነው? ወይስ አሁን ያለህበት ሁኔታ ራዕይህን አጥቦታል?  ❓የሃይማኖት መሪዎች "አንተ ዝም በል፤እግዚአብሔር ያለ አንተም ማድረግ ይችላል" ሲሉት ኬሪ ግን አልተቀበላቸውም። በውስጥህ የተቀመጠውን ታላቅ ዓላማ "አይቻልም"፣"አቅም የለህም" ወይም "የአንተ ሼል አይደለም" ብለው የሚገታቱህ ድምፆች ሲበዙ፣ድምፃቸውን ሰብረህ የመራመድ ቆራጥነት አለህ? ❓ለምትኖርለት ዓላማ ወይም ለጀመርከው መልካም ሼል ላብህንና ጥረትህን አፍስሰህ ለረጅም ጊዜ ምንም ዓይነት ውጤት ባታይ፣ተስፋ ሳትቆርጥ እስከ መጨረሻው የመቆም እምነት እና ጽናት አለህ? ❓ዛሬ በሕይወትህ እግዚአብሔርን አምነህ ለመውሰድ የምትፈራው፣ነገር ግን ካደረግከው የብዙዎችን ሕይወት ሊለውጥ የሚችል "ታላቅ የእምነት እርምጃ" (Risk) ምንድን ነው? ❓ የአንተ መኖር እና መሰጠት ለአካባቢህ ማኅበረሰብ የሚያመጣው ተልዕኮዊ ለውጥ ምንድን ነው? ከእኔነት አልፈህ ለትውልድ የሚሻገር ምን አሻራ እየጣልክ ነው? 💫​እውነተኛ ሚስዮን (ጥሪ) ማለት የተቀመጥንበትን ምቾት ትታን የሌሎችን ሕይወት ለመለወጥ የሚደረግ ታላቅ ጉዞ ነው። 🧠 ሚሲዮናዊ አስተሳሰብ አላችሁ?     📢ሚሲዮናዊ ናችሁ?

ውዶቼ ፕሮግራም ተጀምሯል ኑ