282
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-130 days
Posts Archive
282
በቃ እንዲሁ ኑሩ ተብሎ እንደተፃፈብን ፣በሁሉም ነገር መሀል ፣ላይ ሁኖ መቅረት ፣ወይ የሚከሰተውን ነገር መቀበል ፣መውደድ አንችል ፣ወይ ደግሞ የምንወደው ነገር አይከሰት::🤔
282
ከራስ ጋር መታረቅ ተስኗቸው ፣እድሜያቸውን ሙሉ ራስን በመርገምና በመጥላት እስር ላይ የነበሩ ሚስኪኖችን ፣ ሊቀይሩት ከማይችሉት ማንነት ጋር ሲታገሉ የነበሩ ድኩሞችን ፣ በሰው አጀባ ተከበውም በባይተዋርነት የሚጮሁ ድምፆችንም ሸሽጋለች። ታልሞ የተሳካ አልያም የታቀደ ደግነትንም ክፋትንም ከአፈሯ ቀላቅላለች:: 🙇♀
282
ምድር በውስጧ የሸሸገቻቸው፣ ፈራሽ ገላዎችን ብቻ አይደለም። ታልመው የነበሩ ነገዎችን ፣ ያልተኖሩ ህልሞችን ፣ እምቡጥ ተስፋዎችን ፣ ቸርና ደጋግ ልቦችን ፣ የመኖርን ጣዕም ገና ያልቀመሱ ለጋ ነፍሶችን ፣ እምባቸው ደርቆ ገና ፈገግታን በመለማመድ ላይ ያሉ ያልቦረቁ ሀዘኖችንም ሸሽጋለች። የሰከነ አካሄድን ያልለመዱ ወልካፋ የልብ እርምጃዎችን ፣
282
😞ሁሉም የራሱ ህልም ብቻ ሳይሆን፣ ሊገፋው የሚታገለው አልያም ሊወጣው ሚያጣጥረው ወይም የሚንደረደርበት ተራራ አለው።
ተራራው አናት ላይ ደርሶ የረጋ ከመዝገበ ህይወት ላይ አልሰፈረም። ሁሉም በመሞከር ላይ ሳለ ፣እጣ ፈንታው ቀድሞት ያለመውና ሊያሳካቸው ከሚሹ እልፍ መሻቶች ጋር መሬት ሆድ ውስጥ ተሸሽጎዋል።
282
😞ሁሉም የራሱ ህልም ብቻ ሳይሆን፣ ሊገፋው የሚታገለው አልያም ሊወጣው ሚያጣጥረው ወይም የሚንደረደርበት ተራራ አለው።
ተራራው አናት ላይ ደርሶ የረጋ ከመዝገበ ህይወት ላይ አልሰፈረም። ሁሉም በመሞከር ላይ ሳለ ፣እጣ ፈንታው ቀድሞት ያለመውና ሊያሳካቸው ከሚሹ እልፍ መሻቶች ጋር መሬት ሆድ ውስጥ ተሸሽጎዋል።
ምድር በውስጧ የሸሸገቻቸው፣ ፈራሽ ገላዎችን ብቻ አይደለም። ታልመው የነበሩ ነገዎችን ፣ ያልተኖሩ ህልሞችን ፣ እምቡጥ ተስፋዎችን ፣ ቸርና ደጋግ ልቦችን ፣ የመኖርን ጣዕም ገና ያልቀመሱ ለጋ ነፍሶችን ፣ እምባቸው ደርቆ ገና ፈገግታን በመለማመድ ላይ ያሉ ያልቦረቁ ሀዘኖችንም ሸሽጋለች። የሰከነ አካሄድን ያልለመዱ ወልካፋ የልብ እርምጃዎችን ፣
ከራስ ጋር መታረቅ ተስኗቸው ፣እድሜያቸውን ሙሉ ራስን በመርገምና በመጥላት እስር ላይ የነበሩ ሚስኪኖችን ፣ ሊቀይሩት ከማይችሉት ማንነት ጋር ሲታገሉ የነበሩ ድኩሞችን ፣ በሰው አጀባ ተከበውም በባይተዋርነት የሚጮሁ ድምፆችንም ሸሽጋለች። ታልሞ የተሳካ አልያም የታቀደ ደግነትንም ክፋትንም ከአፈሯ ቀላቅላለች:: 🙇♀
282
“ሰላም እፈልጋለሁ” ትላለህ…
ግን ሰላምህን የሚያጠፋውን ነገር ለመልቀቅ ትፈራለህ።
ምክንያቱም አንዳንዴ የምንይዘው ነገር ጥሩ ስለሆነ አይደለም…
ለመልቀቅ ስለለመድነው ነው።
የሚያሰቃየንን ሰው እንይዛለን።
የሚያደክመንን ቦታ እንቆያለን።
የማይጠቅመንን ልማድ እንደገና እንደገና እንደግማለን።
ከዚያም “ለምን ሰላም የለኝም?” እንላለን።
ምናልባት ሰላም ከእኛ አልሸሸም።
እኛ ሰላም የሚጠይቀውን ነገር ለመልቀቅ ነን የፈራነው።
እና አንድ ቀን ራስህን ጠይቅ፦
“የምይዘው ነገር በእውነት የምፈልገው ነው…
ወይስ ለመልቀቅ የምፈራው?”
282
Someone said
አንዳንዴ ከፈራሽውም ከተመኝሽውም ላትጎኚ ላትጎኝም ትችያለሽ። ሕይወት ቀደረን ከመውደድ የበለጠ ማስዋቢያ የላትም። አንዳንድ ነገር መፈለግ ብቻ ሳይሆን፣ ለመተውም ድፍረት ያስፈልጋል። 🤗
282
_መልካም ማሰብ፣ መልካም መናገር፣ መልካም መሥራት።ከፍ ብሎ ማሰብና ማድረግ፣አመስጋኝ መሆን ሰዎችን እና ፈጣሪን፣ ስለሰዎች ትቂት መልካምነት መናገርና ከፍ ማድረግ እንጂ ስለብዙ ድክመታቸው ባንደክም። ሁሉም ሰው እኩል መሆኑን መረዳት። የጊዜ፣ የቦታ እና የሁኔታዎች ተጽዕኖ እንጂ ማንም ከማንም ያላነሰ እንደሆነ አለመዘንጋት። ሰዎችን እኩል ለማየት ይረዳናል።
ልባችንን ለመልካም በር ክፍት እናድርገው🤗
282
ለመኖር ስል እየነካካው ያለኋቸው ርዕሶች ሁላ ከመኖር ሲያርቁኝ ነው የማስተውለው ። አማኝ ለመሆን ስጥር ከጌታዬ መራቅ ለምን ይሰማኛል ? ለማወቅ ስጥር የውሸት ትርክት የማጎር አይነት ስሜት....ለመጠንከር ስሞክር ድካም... ለምን ?
ጊዜያቶች ባለፉ ቁጥር እቺ አለም የውሸት ሹራብ እየደረበች ...የእውነትን ብርሀን እያደበዘዘች ...የመኖርን ጣዕም እያጎመዘዘች ነው ።
እቺ አለም እንደነበረችው አይደለችም...መሆን እንዳለባትም አይደለችም ። ከዘመናት በፊት የተቀየሰ አዲስ መንገድ ሳይኖር አይቀርም ። ይህ መንገድ ሁሉን ነገር አሳጥቶናል ...እምነታችንን ፣ ህይወታችንን ፣ እኛነታችንን ሁሉ ነጥቆናል ። አማኝነትን በራስ ወዳድነትና በተጨቃጫቂነት ለውጦብናል...ህይወታችንን ለሌሎች በማቀበል ስለሌሎች የሚገበር ተራ የጊዜያት ጥርቅም አድርጎብናል...እኛነታችንን ለማናውቀው እና ፍፁም ደስታችንን ለሚመጠው ሌላ ነገር አሳልፎ ሰጥቶብናል!
📚📚
282
Work hard for the woman you want to become. Work hard that someday you'll whisper to your self "This is the woman that i built!"😊
Better,Stronger,Wiser!!!
282
😊ብዙ ጊዜ ሌሎች ትክክል እንዲሆኑ ፍቀድላቸው
ራስህን መጠየቅ ካለብህ መሰረታዊ ጥያቄዎች አንዱ "ትክክል መሆን ነው የምፈልገው ወይስ ደስተኛ"? የሚለው አንዱ ነው።
ብዙ ጊዜ ሁለቱ ዘይትና ውሃ ናቸው። ትክክል መሆንና አቋማችንን ለማስጠበቅ መሞከር ብዙ የአዕምሮ ጉልበት ይጠይቃል።እንዲሁም ከሰዎች እያራቅን ይመጣል 😍
282
😊ብዙ ጊዜ ሌሎች ትክክል እንዲሆኑ ፍቀድላቸው
ራስህን መጠየቅ ካለብህ መሰረታዊ ጥያቄዎች አንዱ "ትክክል መሆን ነው የምፈልገው ወይስ ደስተኛ"? የሚለው አንዱ ነው።
ብዙ ጊዜ ሁለቱ ዘይትና ውሃ ናቸው። ትክክል መሆንና አቋማችንን ለማስጠበቅ መሞከር ብዙ የአዕምሮ ጉልበት ይጠይቃል።እንዲሁም ከሰዎች እያራቅን ይመጣል.......👉👉👉
282
ብዙ ጊዜ ሌሎች ትክክል እንዲሆኑ ፍቀድላቸው
ራስህን መጠየቅ ካለብህ መሰረታዊ ጥያቄዎች አንዱ "ትክክል መሆን ነው የምፈልገው ወይስ ደስተኛ"? የሚለው አንዱ ነው።
ብዙ ጊዜ ሁለቱ ዘይትና ውሃ ናቸው። ትክክል መሆንና አቋማችንን ለማስጠበቅ መሞከር ብዙ የአዕምሮ ጉልበት ይጠይቃል።እንዲሁም ከሰዎች እያራቅን ይመጣል.......👉👉👉
282
ከራስ ጋር መተዋወቅ ፣ከዛም ሰላም መፍጠር፣ በሕይወታችን ውስጥ፣ ከምንወስናቸው ውሳኔዎች ፣ሁሉ ከባዱ ነው።
ውስጥህ ከተሰራ ሌላው የሕይወት ጉዳይ እዳው ገብስ ነው።😊
