6 587
Subscribers
-124 hours
-147 days
+1230 days
Posts Archive
6 586
እንደምን ቆያችሁ? አዎን ጠፍቻለሁ … ቢሆንም በኔ ዙሪያ ያላችሁን ማንኛውንም አይነት አስተያየት፣ ትችት እና ወቀሳ በዚህ አቅርቡልኝ፦ @Ahmedresbot
6 586
አሰላም አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
በአረብ ሀገር በሳዉዲ አረብያ የምትኖር እህታችን ሀናን አህመድ በዚሁ የቲክቶክ መድረክ ወንድሞችንና ኡስታዞችን ስታግዝ ስታበረታታና ለበጎ ስራ ስትሽቀዳደም የነበረች መልካም እህታችን ነች። ሆኖም ግን በድንገት ባጋጠማት ከፍተኛ የጤና እክል ምክንያት ሶስት ጊዜ ያህል አባድ የሰርጀሪ ህክምናዎችን ለማድረግ ተገዳለች።
በዚህም ምክንያት ያላትን ጥሪት በሙሉ ለመድኃኒትና ለሕክምና ጨርሳ አሁን ላይ ከባድ የሰው ዕዳ ውስጥ ወድቃ ትገኛለች። ትናንት ካላት ላይ በማካፈልና ሰዎችን በመርዳት የምትታወቀው እህታችን ዛሬ የእኛን እጅና ድጋፍ አጥብቃ ትፈልጋለች።
ከአላህ ቀጥሎ ለእህታችን ሀናን እኛ ከጎኑዋ አለንላት ብለን ካለባት የሕመም ስቃይና የዕዳ ጭንቀት እንድትገላገል በቻልነው አቅም ልንደርስላት ይገባል። ይህ እህታችንን ብቻ ሳይሆን በአረብ ሀገር የሚገኙ እህቶቻችንን ድጋፍ የምናሳይበት ነዉ። የአረብ ሀገር እህቶች እስከዛሬ ለብዙዎች ሲሆኑ አይተናል ዛሬ ለነሱም መሆናችንን እናሳይ ።
ስለሆነም ሁላችሁም ከታች በተቀመጠው የባንክ ሂሳብ ቁጥር አቅማችሁ የፈቀደውን በመለገስ ወይም የተከፈተውን የቴሌግራም ግሩፕ በመቀላቀል ከጎኗ እንድትቆሙ በአላህ ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን።
አካውት እህታችንን ለመርዳት
ንግድ ባንክ፡1000586128977
አሚነት ጡሃ ዑመር
የቴሌግራም ግሩፕ https://t.me/+R3jwr9j2xJdkNTI0
በሁሉም በእህት ወንድሞች ቻናሎች የሚለቀቅ
6 586
“One apple fell and the whole world knew gravity however, millions of bodies fell and no one knew humanity!“
6 586
Repost from N/a
በነቢይነታቸው አሥረኛ ዓመት፣ ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ባለቤታቸውን እናታችን ኸዲጃን እና አጎታቸውን አቡ ጣሊብን በሞት ካጡ በኋላ፣ በቁረይሾች በኩል የሚደርስባቸው መከራና እንግልት በእጅጉ በረታ። በዚህም ምክንያት የመካ ሰዎች ጥሪያቸውን ባለመቀበላቸው፣ የእስልምናን መልእክት ለማድረስና ድጋፍ ለማግኘት ከአጎታቸው ልጅ ዘይድ ኢብኑ ሐሪሳ ጋር በመሆን ወደ ጣኢፍ ለመሄድ ተነሱ።
ወደ ጣኢፍም በሄዱ ጊዜ የሰቂፍ ጎሳ መሪዎች ወደሆኑት ወደ ሦስቱ ወንድማማቾች — ዐብድ ያሊል፣ መስዑድ እና ሐቢብ — ዘንድ በመሄድ የእስልምናን ጥሪ አቀረቡላቸው፤ ከቁረይሾች ጥቃትም እንዲጠብቋቸው ጠየቋቸው። ነገር ግን መሪዎቹ በጥሪው ላይ አፌዙ፤ በጣም ባልተገባና ነቀፌታ በተሞላው መንገድ ጥሪያቸውን ውድቅ አደረጉት። መሪዎቹ ጥሪውን ውድቅ ከማድረጋቸውም በላይ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በአስቸኳይ ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ አዘዙ። ከከተማዋ ሲወጡም የከተማዋን እብዶች፣ ባሪያዎችና ሕፃናት በሁለት መስመር አሰልፈው ድንጋይ እንዲወረውሩባቸው አደረጉ። ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እና ዘይድ ኢብኑ ሐሪሳ ከተማዋን ለቀው እስኪወጡ ድረስ በድንጋይ ተደበደቡ፤ እግራቸው በደም ተለወሰ፤ ዘይድም ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ለመከላከል ሲሞክር ራሱ ላይ ከባድ ጉዳት ደረሰበት።
ከከተማዋ ትንሽ ራቅ ብሎ በሚገኘው የቁረይሽ ከበርቴዎች በነበሩት በኡትባ እና ሸይባ የአትክልት ስፍራ በደረሱና ባረፉ ጊዜም፣ ውዱ ነቢይ ወደ አላህ እንዲህ ሲሉ ጥሪያቸውን አሰሙ፦
"اللَّهُمَّ إِلَيْكَ أَشْكُو ضَعْفَ قُوَّتِي، وَقِلَّةَ حِيلَتِي، وَهَوَانِي عَلَى النَّاسِ، أَنْتَ رَبُّ الْمُسْتَضْعَفِينَ وَأَنْتَ رَبِّي، إِلَى مَنْ تَكِلُنِي؟ إِلَى بَعِيدٍ يَتَجَهَّمُنِي؟ أَمْ إِلَى عَدُوٍّ مَلَّكْتَهُ أَمْرِي؟ إِنْ لَمْ يَكُنْ بِكَ غَضَبٌ عَلَيَّ فَلَا أُبَالِي، وَلَكِنَّ عَافِيَتَكَ هِيَ أَوْسَعُ لِي، أَعُوذُ بِنُورِ وَجْهِكَ الَّذِي أَشْرَقَتْ لَهُ الظُّلُمَاتُ، وَصَلَحَ عَلَيْهِ أَمْرُ الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ، مِنْ أَنْ تُنْزِلَ بِي غَضَبَكَ، أَوْ يَحِلَّ عَلَيَّ سَخَطُكَ، لَكَ الْعُتْبَى حَتَّى تَرْضَى، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِكَ».
አላህ ሆይ የጉልበቴን ደካማነት የመላዬን (የብልሃቴን)ማነስ በሰዎች ዘንድ ማነሴን (መናቄን) አቤቱታዬን ወደ አንተ አቀርባለው ።አንተ የደካሞች ጌታ ነህ ፤ አንተም ጌታዬ ነህ ። ለማን አሳልፈህ ትሰጠኛለህ? በጭካኔ ለሚያስተናግደኝ ሩቅ ሰው ወይስ ጉዳዬን ለሰጠኸው ጠላት? አንተ ካልተቆጣህብኝ ሌላው ግድ አይሰጠኝም ፤ ሆኖም የአንተ ጥበቃና እዝነት ለእኔ የበለጠ ሰፊና በቂ ነው ። ቁጣህ በኔ ላይ እንዳይወርድ መዓትህም በኔ ላይ እንዳይሆን ጨለማን በሚያበራውና የዚህን ዓለምም ሆነ የመጨረሻውን ዓለም ጉዳዮች በሚያስተካክለው በፊትህ ብርሃን እጠበቃለው ። አንተ እስክትረካ ድረስ ይቅርታህን እሻለው ፤ ከአንተ ውጪ ምንም ዓይነት ሃይልም ብርታትም የለም ።ይህን ሁኔታቸውን በአትክልት ስፍራው የሚያገለግል አንድ ባሪያ ባየ ጊዜ፣ በሁኔታቸው አዝኖ ወደ እነሱ ተጠግቶ የወይን ፍሬ ሰጣቸው። ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ፍሬውን ከመብላታቸው በፊት "ቢስሚላህ" ባሉ ጊዜ፣ ይህ ባሪያ በንግግራቸው በመደነቅ «የዚህ አካባቢ ሰዎች ይህን ቃል አይጠቀሙም» አለ። ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) የየት ሀገር ሰው እንደሆነና ሃይማኖቱ ምን እንደሆነ ጠየቁት። እርሱም የነይነዋ (የነቢዩላህ ዩኑስ ሀገር) ሰው እንደሆነና ሃይማኖቱም መሲሐዊ (ክርስቲያን) እንደሆነ ነገራቸው። ዓዳስ (ባሪያው) ስለ ነቢዩላህ ዩኑስ በምን እንደሚያውቁ በጠየቃቸው ጊዜ «እርሱ ወንድሜ ነው፤ ነቢይም ነበር፤ እኔም ነቢይ ነኝ» አሉት። ይህን በሰማ ጊዜ ባሪያው ግንባራቸውን፣ እጃቸውን እና እግራቸውን በመሳም እስልምናን ተቀበለ። ይህንን ያየው አሳዳሪውም «ወየውልህ! የዚህን ሰው እጅ፣ እግርና ግንባር ትስማለህ?» ብሎ በጠየቀው ጊዜ፣ ባሪያውም «ከዚህ የተሻለ ነገር ምን አለ? ነቢይ እንጂ ሌላ የማያውቀውን ነገር ነገረኝ» በማለት መለሰለት። ከዚህም በኋላ ጉዟቸውን በመቀጠል ላይ ሳሉ፣ 'ቀርኑል መናዚል' የሚባል ስፍራ ላይ በደረሱ ጊዜ አላህ መላእክትን ላከላቸው። የመላእክት አለቃ ጅብሪልም ሰላምታ ካቀረበ በኋላ እንዲህ አላቸው፦ «አላህ የሕዝቦችህን ምላሽ ሰምቷል። የተራሮችን መልአክም እነሱ ላይ የፈለግከውን እንድታዝባቸው ልኮልሃል።» የተራሮች መልአክም ሰላምታ ካቀረበ በኋላ «ጌታህ በእርግጥም ወደ አንተ ትእዛዝህን እንድፈጽም ልኮኛል። ከፈለግክ እነዚህን ሁለቱን ተራሮች በጣኢፍ ሕዝቦች ላይ አጣብቄ ላጥፋቸው።» አለ። መልአኩ ይህን ቢላቸውም፣ ለዓለማት እዝነት ሆነው የተላኩት የኛ ነቢይ መልስ ግን በጣም አስገራሚ ነበር። «በእርግጥ ከእነዚህ ሕዝቦች ውስጥ ወደፊት አላህን በብቸኝነት፣ ማንንም ሳያጋሩ የሚያመልኩ ትውልዶች ይፈጠራሉ ብዬ እከጅላለሁ።» በማለት እነዚህን ሕዝቦች ከመጥፋት ታደጓቸው።
