en
Feedback
FACE THE TRUTH

FACE THE TRUTH

Open in Telegram

አብዱልከሪም እባላለሁ ! እዚህ ቻናል ላይ እስልምናን የተመለከቱ ፖለቲካዊ ሀሳቦችን , ታሪካዊ ክስተቶችን እንዲሁም የኃይማኖት ንፅፅር መረጃዎችን አቀርባለሁ። [ የትኛውም ማህበር እንዲሁም ፓርቲ አባል አይደለሁም ] --- ዘና በሉ... ፈገግ እያልን እንማማር አላህ ያግዘን !! (B T G O G).

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel FACE THE TRUTH

Channel FACE THE TRUTH (@facethetruth22) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 437 subscribers, ranking 5 920 in the Religion & Spirituality category and 2 369 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 437 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -43 over the last 30 days and by -28 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 17.56%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 24.39% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 536 views. Within the first day, a publication typically gains 3 523 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 228.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“አብዱልከሪም እባላለሁ ! እዚህ ቻናል ላይ እስልምናን የተመለከቱ ፖለቲካዊ ሀሳቦችን , ታሪካዊ ክስተቶችን እንዲሁም የኃይማኖት ንፅፅር መረጃዎችን አቀርባለሁ። [ የትኛውም ማህበር እንዲሁም ፓርቲ አባል አይደለሁም ] --- ዘና በሉ... ፈገግ እያልን እንማማር አላህ ያግዘን !! (B T G O G).”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 437
Subscribers
-2824 hours
-447 days
-4330 days
Posts Archive
ከአንዱ ወገናችን መልስ አግኝተናል። ወገናችን ቃሌ ከውይይት ሸሽቷል። በቃ ጨርሰናል ከአንተ ጋ። ሁለተኛ ስሜን አታንሳ ለሌላ ጊዜ ። በነገራችን ላይ pdf አዘጋጅላቹሃለሁ ። ህልሜ ነው በነገራችን ላይ። የምን pdf ካላችሁ በንፅፅር ቆይታዬ ትላልቅ የክርስቲያን ንፅፅር ሰሪዎች ባሳለፍኩት አመታት በቻሉት አቅም ከእኔ ጋ መወያየትን አይፈልጉም አይመርጡም። ጠርተውኝ ስመጣ የሆነ ሰበብ ፈልገው ይጠፋሉ። እናም በመረጃ ኦርቶዶክስ ላይ ያሉትንም ፕሮቴስታንት ላይ ያሉትንም ስም እና ፎቶ ያላቸውን ተከታይ ከዛ ለውይይት የጠሩኝን ከዛ የጠፉበት በpdf በመረጃ አዘጋጅላቹሃለሁ። ለመወያየት ተስማምተው ነውኮ ቀን ቆርጠው ይጠፋሉ። እግሬ አውጪኝ ብለው ይጠፋሉ። ህልሜ ለኢስላም መወያየት ነው ግን ማንም ሳይወያየኝ ሳደፍረኝ ከንፅፅር ቢወጣ ደስታዬ ነው 😁። የሆነ ሰው ሊወያየኝ ከመጣ ለእኔ ይህ በራሱ ሽንፈት ነው። አሸንፈዋለሁ ብሎ አሰቦ ነውኮ የሚመጣው። ማሰቡ ራሱ ያናድዳል። ደግነቱ እስካሁን አልተደፈርኩም 😁 (ትቀልዳለህ እንዴ ) አሁን የዳንኤልን መልስ ብቻ ጠብቃለሁ። ከላይ ያለውን ቪድዮ ውይይት የጠራሁትን አድርሱለት። ራሱ ስሜን ጠርቶ ካልመጣ በቃ። pdfፉ ሰርቼ ለቅላቹሃለሁ ማለት ነው :: ተወያይቼ ባግዛችሁ ደስ ይለኛል ችግሩ ክርስቲያኖች ይፈራሉ። በpdf ለቅላቹሃለሁ። ከዛ ውይይት ጥሪ መጥራት ሲጠራ መቀበል እናቆማለን። ላይቭ ላይ እና በቪድዮ እንቀጥላለን ማለት ነው። አለቀ ። ጠብቁ pdf 💪💪 ✍️ Abdulkerim

ላይቭ እንግባ እንዴ ?? አንድ ሁለት አንድ ሁለት ነው ውስጥ ነኝ 😁

ተው ተው ኢብሮ ። ከራስ ጋ አትጣላ ። የራስህን ንግግር ላሰማህ። ከረሳከው ። እኔ ራሴ ቃሌን አልፈልገውም ነበር ። አንተ እምቢ ስላልክ ተቀበልኩት። ከዛ አንተ After 8 minutes እኔ እንደተቀበልኩት መጣህ 😁 🔴 ቢያንስ ግን የማትፈልገውን ሰው እንድትፈልገው አደረኩህ 😁😁። ይህ ራሱ ትልቅ ስራ ነው። ✍️ Abdulkerim

i think ወንድማችን ኢብራሂም ከቃሌ ጋ መወያየት ፈልጓል። እንደማይፈልግ ነበር የማውቀው የነገረኝም። suddenly ግን ዛሬ ፈልጓል 😁። እኔ ከከለቀቅኩ ከ8ደቂቃ በኃላ ነው የፈለገው 😁 የእኔ point እኔ ስሜን ማንም እንዳያነሳ ነው። ካነሳ መጥቶ ይወያየኝ ነው እንጂ እኔ ከሚዲያ ምንም የማገኘው ነገር የለም። ተረጋጉ ሀጂ። 😁። Anyways ቃሌም ይሁን ዳንኤል ስሜን አንስታቹሃል ። ጉዳያችሁን ጨርሳችሁ ውይይት መወያየት ትችላላችሁ ። ካልፈራችሁ ። ጨረታ አያስፈልግም። ከሚዲያ የምሰራው ቢዝነስ ስለሌለ አልቸኩልም። 2 ወር አላችሁ። እስከ መስከረም 15 ድረስ።    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

+1
ዳንኤል  አንተም ከእኔ ጋ መወያየት ከፈለክ እንችላለን ። ኡስታዝ ቃል አሚን  ጋ ስታወራ አብዱልከሪም እምቢ አለ እያልክ ስታወራ  እዛው እሱ በሁለቱም ተወያዩ ሲልህ ተርበተበትክ 😁😁 ቆይ ቆይ አልክ 😁😁 ሰበብ አትፍጠር ። ከፈለክ በሁለቱም ከፈለክ አንዱን መርጠህ ። ነገሩን ወደ እኔ አታሳብብ። ደፈር ብለህ ና በco-host መወያየት እንችላለን ። አድርሱለት ለዚህም !! 🌪 guys ሾለ እኔ የሆነ ሰው ዳር ሆኖ ሊያወራ ይችላል ደፍሮ ግን አይመጣም ። ከመጣም መጨረሻው ይሆናል።    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

🌐ወገናችን ቃሌ እኔ በግሌ ውይይቱን ተቀብያለሁ!! 🎆 Date ከነሀሴ 14 በኃላ የትኛውም ቀን co-host ሲሜ join ያደርገናል። 🎆 Format 15 min OP .. , 10 min F.R , 10 min S.R , 10 min C.E , 5 min Conclusion 🔴 ማስጠንቀቂያ 🔴 - ደጋግሜ መናገር አይጠበቅብኝም 22 ሰዎች ነው የሚሰሙህ በዚህ ሁኔታህ ደግሱልኝ አትበለን። ባይሆን ወገኖችህ ሰፈር ማስታወቂያ ሾል ። አደራ እነዛ 22 ሰዎች ከሆኑ የዛን ቀን የሚመጡት ምንም ሼም ሳይዘኝ ውይይቱን ሰርዘዋለሁ።Try your level best!    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

🔴 በጥንቃቄ አንብቡት ለህይወታችሁ ይጠቅማቹሃል እኔ የተማርኩት ነገር ነው የሆነ ነገር አየሁና ለምን አልነግራቸውም ብዬ አሰብኩ። ይኸውላችሁ መልካም ሰው ሆናለሁ ብላችሁ ውስጣችሁ ጥሩ እና መልካም
🔴 በጥንቃቄ አንብቡት ለህይወታችሁ ይጠቅማቹሃል እኔ የተማርኩት ነገር ነው የሆነ ነገር አየሁና ለምን አልነግራቸውም ብዬ አሰብኩ። ይኸውላችሁ መልካም ሰው ሆናለሁ ብላችሁ ውስጣችሁ ጥሩ እና መልካም ስለሆነ ብቻ ዙራያችሁን ሙሉ በሙሉ በድሆች አትሙሉ። አንድ ቀን ይጎዳቹሃል። የምሬን ነው ይህ የተማርኩት ትልቅ ነገር ነው።  ንፁህ ልብ የሆነ ገለመሌ ምናምን አይጠቅምም። 🔴እኔ ያለሁበትን ነገር ቀጥታ ሳልነግራችሁ  በምሳሌ አድርጌ ልንገራችሁ የሆነ የሳይክል ውድድር ነበረ እየተወዳደርኩ ሊያልቅ ነው። እኔ በረጅም ርቀት እየመራሁ ነው። የሆነ ቦታ ላይ የሳይክሉ ጎማው ተበላሸ። ወርጄ ሳየው መቀየር አለበት ። ok አልኩኝ ። ደዋወልኩ የማቃቸው ልጆች ጋ ። ገምቱ ,  ከዛ እኔ የምደውልላቸው ሰዎች ሁሉም ድሆች ናቸው። እኔ ሳይክሌን ይዤ ቁጭ ብያለሁ። Still  ሌሎች ተወዳዳሪዎች አልደረሱብኝም ርቂያቸው ስላለሁ አልመጡም። ያው ግን የጊዜ ጉዳይ ነው ደርሰው ያልፉኛል። ቁጭ ብዬ እያሰብኩ ያለሁት ዙሪያዬን በድሆች ሞልቼው እንደነበር ነው የተረዳሁት። የምነግራችሁ ነገር ዙሪያችሁ ዋጋ ሳያስከፍላችሁ በፊት አስተካክሉት  !!!!    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

🌐ተመልሻለሁ !! መልካም ሰው ሆናለሁ ውስጣችሁ ጥሩ ስለሆነ ዙራያችሁን ሙሉ በሙሉ በድሆች አትሙሉ። የምሬን ነው ይህ የተማርኩት ትልቅ ነገር ነው። ንፁህ ልብ የሆነ ገለመሌ ምናምን አይጠቅምም። 🔘
🌐ተመልሻለሁ !! መልካም ሰው ሆናለሁ ውስጣችሁ ጥሩ ስለሆነ ዙራያችሁን ሙሉ በሙሉ በድሆች አትሙሉ። የምሬን ነው ይህ የተማርኩት ትልቅ ነገር ነው።  ንፁህ ልብ የሆነ ገለመሌ ምናምን አይጠቅምም። 🔘እኔ ያለሁበትን ነገር ቀጥታ ሳልነግራችሁ  በምሳሌ አድርጌ ልንገራችሁ የሆነ የሳይክል ውድድር ነበረ እየተወዳደርኩ ሊያልቅ ነው። እኔ በረጅም ርቀት እየመራሁ ነው። የሆነ ቦታ ላይ የሳይክሉ ጎማው ተበላሸ። ወርጄ ሳየው መቀየር አለበት ። ok አልኩኝ ። ደዋወልኩ የማቃቸው ልጆች ጋ ። ገምቱ ,  ከዛ እኔ የምደውልላቸው ሰዎች ሁሉም ድሆች ናቸው። እኔ ሳይክሌን ይዤ ቁጭ ብያለሁ። Still  ሌሎች ተወዳዳሪዎች አልደረሱብኝም ርቂያቸው ስላለሁ አልመጡም። ያው ግን የጊዜ ጉዳይ ነው ደርሰው ያልፉኛል። ቁጭ ብዬ እያሰብኩ ያለሁት ዙሪያዬን በድሆች ሞልቼው እንደነበር ነው የተረዳሁት። የሚያስቀኝ part አይዞህ ለኸይር ነው የተሻለ አስቦልህ ነው ይሉሃል ። አስበው 1 የሳይክል ጎማ መቀየር አቅቷቸው ሀዲስ ይነግሩሃል ።   😁😁 ።  ይሄስ ህይወት አይደለም ። አሞኝ ሆስፒታል ብገባስ ?? አሁን ሳይክልን ይዣት ቁጭ ብዬ  ከኃላ ያሉት ይለፉኝና ተስፋ ልቁረጥ ። የምነግራችሁ ነገር ዙሪያችሁ ዋጋ ሳያስከፍላችሁ በፊት አስተካክሉት  !!!!    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

የኦርቶዶክስ የእርስበርስ ግጭት ኦርቶዶክስ ሰሞኑን ከባድ ድንጋጤ እና ጭቅጭቅ ላይ ናቸው። ባለፈው ውይይት ላይ ካስታወሳችሁ አላህ ፍጡር አይደለም ። ከፍጡራን ጋ በምንም የማይመስል በአዕምሮ ሊሳልም
+1
የኦርቶዶክስ የእርስበርስ ግጭት ኦርቶዶክስ ሰሞኑን ከባድ ድንጋጤ እና ጭቅጭቅ ላይ ናቸው። ባለፈው ውይይት ላይ ካስታወሳችሁ አላህ ፍጡር አይደለም ። ከፍጡራን ጋ በምንም የማይመስል በአዕምሮ ሊሳልም ሆነ ሊታሰብ የማይችል መለኮታዊ አካል አለው ስንል አበዱ ። (አካል ስል ሰውነት ምናምን እያልኩ አይደለም) እኛ የማንገመግው ልሹ ብቻ የሚያውቀው መለኮታዊ አካል አለው ስንላቸው በቃ ግርግር ፈጠሩ ።ኦርቶዶክስ ወገኖች ይህን ግርግር በመጠቀም ኢስላም ላይ ለማላገጥ ሲሞክሩ ነበር ግን  የራሳቸው የቤተክርስቲያን መምህራን እግዚአብሔር አካል አለው ከማለትም በላይ ፆታ እንዳላቸው ሲናገሩ ቲክቶክ መንደር ያሉ ምንም የማያውቁ የመንደር ሰባኪዎች በድንጋጤ ተውጠው ይገኛሉ። መሬት ላይ ያለችው ኦርቶዶክስ የምታስተምረውን ደብቀው ነበር ለህዝብ የሚሰብኩት። እውነታው እየወጣ ሲያዩ ቤተክርስቲያን በይፋ የሾመቻቸው ትላልቅ መምህራኖችን የቤተክርስቲያን አባቶችን እየተቹ እያሸማቀቁ ይገኛሉ። ከላይ ቪድዮው ላይ   አንደምታዩት ይህ የቤተክርስቲያን አባት የደረባቸውን የሰሙትን  እየገለፁ ይገኛሉ ። መምህራንን ለማስጠመድ እና ቤተክርስቲያንን ባዶ ለማድረግ ነው በማለት ይህ ተናግረዋል ። ክርስቲያን ወገኖች የምትከተሏቸው የቲክቶክ አስተማሪዎች በዚህ ልክ ሀይማኖታቸው ላይ ከዋሹ እና እስልምና ላይ ደግሞ አስቡት... አላህ ይምራችሁ !!! ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

ቲክቶክ ላይ ይህን ቪድዮ አይቼ ትንሽ ቀልቤን ሳበው ። ቋንቋ ላይ ቃላት ማወቅ ብቻ ላይጠቅም ይችላል ። አንድ አረፍተነገር ሆኖ የሆነን ቃል ረግጣችሁ በማንበባችሁ ብቻ መልዕክቱ ግን ሊቀየር ይችላል። ከላይ ቪድዮው ላይ ያለውን ለምሳሌ ላሳያችሁ I never said she stole my money . 🌐" I" never said she stole my money . " I " 👈 ይህን ረግጦ አንብቦ ሌሎችን normal ካነበበ ትርጉሙ እኔ አይደለሁም ብሬን ሰርቃለች ያልኩት ሌላ ሰው ነው ያለው እያለ ነው። እሱ አላለም ግን ሌላ ሰው ብሏል።) 🌐 I "never" said she stole my money . " Never " 👈 ይህን ረግጦ ሌሎቹን normal ሲያነበው ደግሞ ( በየትኛውም ጊዜ ብሬን ሰርቃለች አላልኩም) 🌐 " said " ይህን ረግጦ ሌሎቹን normal ካነበበ ደግሞ ሰርቃለች አላለም ግን የሆነ ምልክት ሰጥቷል። ወደዛ የሚያመራ። ለምሳሌ ሌባ ነው አላልኩም ግን ብዙ አሮጌ ስልክ በኪሱ ይዞ አየዋለሁ። እንዲህ እንደማለት። 🌐 " she " ይህን ሲረግጠው ደግሞ ብሩ ተሰርቋል ግን እሷ ሰርቃለች አላልኩም እያለ ነው ። የሆነ ሰው ግን ሰርቋል ብሩን። 🌐 "Stole " ይህን ሲረግጠው ደግሞ ብሩ እሷ ጋ ነው ግልፅ ነው ግን ሰወየው ሰርቃለች አላልኩም ግን ተሳስታ ቦርሳ ውስጥ አስገብታ ወስዳ ይሆናል ወይ ተበድራ ይሆናል። ብሩ ግን እሷ ጋ ነው። ብቻ ግን ሰረቀችኝ አላልኩም እያለ ነው 🌐" My " ይህን ከረገጠው ደግሞ ልጅቱ ብር ሰርቃለች ግን ሰውየው እያለ ያለው የእኔን ብር ሰረቃች አላልኩም ነው። ብሩ የአበበ የከበደ ይሆናል ። ብቻ ግን ሰርቃለች። 🌐" Money " ይህን ረግጦ ካነበበው ደግሞ የእኔን ብር ሰርቃለች አላልኩም እያለ ነው ብር አልተሰረቀም እንጂ ሌላ ነገር ሰርቃለች ። ሞባይሉን ሊሆን ይችላል ። 🔴 አሁን ጥያቄው text ስትፃፃፉ ያ ሰው የፈለገውን ቃል ረግጦ ቢያነብስ ??😁 ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

ፎቶህን አጥፋ ይለዩሃል የምትሉኝ ሲጀመር አይታይምኮ ፊቴ ተሸፍኗል ። ሲቀጥል ይህ ፎቶ ከ3-4 አመት በፊት ምናምን ነው አሁን ጭራሽ አትለዩኝም ። አሁንኮ አረጀሁ 26 አመት ።  30 አመቴ ሲሞላ ቁጭ ብዬ የማለቅሰው። ወንድ ልጅ አያለቅስም ግን ይሄ ያስለቅሳል። ለራሴ ነውኮ የማለቅሰው ለልጅነቴ ምናምን። እዬዬ እያልኩ ነው የማለቅሰው ።

ፀጉሬ ላይ ፈትዋ ይሰጥበታል 😁😁 jake አንተ ጀምር ፈትዋ ..... ትክክል ነው አላልኩም እቆረጣለሁ ! ተናግሪያለሁ ። አትድከሙ በፈትዋ
ፀጉሬ ላይ ፈትዋ ይሰጥበታል 😁😁 jake አንተ ጀምር ፈትዋ ..... ትክክል ነው አላልኩም እቆረጣለሁ ! ተናግሪያለሁ ። አትድከሙ በፈትዋ

ይህ ፅሁፍ እንደ ራሴ ነው እንጂ እንደ ኃይማኖት ፅሁፍ አይደለም ።  እነ management , accounting ... ሰሞኑ አፍልተዋል እንርገጣቸው። ታውቃላችሁ ትምህርት ለጨረሱ Exit Exam ነበረ እና አሁን በቃ ሚዲያ ላይ እነ ማኔጅመንት ቢዝነስ ዘርፍ ምናምን እየወጡ ፈጣሪ አዳነኝ ፈጣዬ ከጭንቅ አሶጣኝ ምናምን ይላሉ። የሆነ ከባድ ነገር  ይመስል .. ከመነሻው የምን ጭንቅ ውስጥ ነበራችሁ ? የእኛ የ1 semester ትምህርት የእናንተ የ2 አመት ትምህርት ያክላል።  እንኳን ፈጣሪ.... የኢትዮጵያ ትምህርት ራሱ ስለ እናንተ አይጨነቅም። ምክንያቱም Exit ካለፋችሁ በቃ አለቀ ። እኛ ጋ ነውኮ Exit exam ፈተና ብታልፍ ሁላ ከዛ ድጋሚ ጤና ሚኒስትር የሚያወጣውን COC ማለፍ አለብህ በሞያህ ለመስራት።  engineering ዘርፍ ያሉትም ስለሚለፉ አያወሩም ብዙም የተወሰኑት ሲቀሩ። እነ ማኔጅመንት አፈላችሁኮ። ፈጣሪ ከጭንቁ አስወጣኝ አላሳፈረኝም ምናምን ምናምን የሆነ ከቤተክርስቲያን ደጃፍ ወይ ደግሞ የቁርዓን አያ ምናምን እንትን እያሉ ... ፈጣሪ በራስህ ውጣ አላግዝህም ቢልህ  እንኳን ከነ ማኔጅመንት አካውንቲንግ ቆይ በራስህ አትወጣም ??

🔘  ምን እያለን ነው ይህ ክርስቲያን ሰባኪ የክርስቲያን ወገኖቻችን ጤና ከእለት እለት እያሳሰበኝ ነው ።  ፈጣሪያችሁ ድካም አለበት ተፈጥሮ ላይ ጥገኛ ነው ሲባሉ ነብዩ ሙሐመድ (ሰዐወ ) ድካም አለባቸው ምግብ ይበላሉ ብለው ይገረማሉ። ነብይ ምግብ አይበላም ነው ? ምን እያልከን ነው ? ሁሌ ይመጡና ፈጣሪያቸውን  ከነብዩ ሰዐወ በማወዳደር ሾለ ሲያወሩ ይገርመኛል ። እኛ ነብዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ፈጣሪ ናቸው መች አልን :: ይመጣና ሙሐመድ ሞቷል ኢየሱስ ግን ሞቶ ከዛ ተነሳ ይልሃል ።  Bro እኛኮ ከመነሻው አምላካችንን ጭራሽ የማንፈልግበት ቦታ መቃብር መንደር ነው። ጭራሽ መቃብር መንደር ገብተን ሙታንን አወዳድረን ለአምላክነት እንሹም ??  ምግብ መብላት አየር መተንፈስ መሞት .... እነዚህ ሁሉ ተፈጥሮ ላይ ጥገኛ እና ተፈጥሮ በዛ አካል ላይ የበላይነት እንዳላት የሚያረጋግጥ ነው። ለዛ ነው አምላካችን አላህ በተከበረ ቃሉ በቁርዓን ላይ  በማይሞተው በአላህ ተመኩ እያለ  ሌላው ሁሉ በተፈጥሩ ሾር ነው መሆኑን እሱ ብቻ ምንም ነገር የማይሰለጥንበት መሆኑን የነገረን። 📕 ቁርዓን ምዕራፍ  25:58 وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ وَسَبِّحْ بِحَمْدِهِ ۚ وَكَفَىٰ بِهِ بِذُنُوبِ عِبَادِهِ خَبِيرًا በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ ከማመስገንም ጋር አጥራው፡፡ በባሮቹ ኀጢኣቶችም ውስጠ ዐዋቂ በእርሱ በቃ፡፡ አላህ ሂዳያ ይስጣችሁ !! ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

ክርስቲያኖች ሾለ ኢየሱስ  እነሱ ልሹ አልገባቸውም ። አልተግባቡም አባቶቻቸው ጥንትም ሲከራከሩ ነበር ይኸው ዛሬም አለ ክርክሩ 🌠 የሚጨቃጨቁበትን ጉዳይ  ልንገራችሁ ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ላይ ስልጣን ተሰጠኝ በማለት እንደተቀበለ ይናገራል ። 📕 ማቴዎስ 28፥18 “ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ።” 🔘 አሁን ጥያቄው ኢየሱስ አምላክ ከሆነ  እንዴት ይቀበላል ነው  ? 🌐 አንደኛው መምህር (ነጠላ የጠመጠመው) ኦርቶዶክስ ነው። ኢየሱስ ማለት 100% የሰው ባህሪ  ሲደመር 100% የአምላክ ባህሪ  = ከሁለቱ የተዋሃደ 1 ባህሪ ብሎ ነው የሚያምነው ።ለዛ ኢየሱስ ስልጣን ተቀበልኩ ሲል ለስጋ ወይም ሰው ለሆነበት ጎኑ ነው እያለው  ነው 🌐 ሌላኛው መምህር  ደግሞ  (ጥቁር ጃኬት ያደረገው ) ኢየሱስ ወደ ምድር ሲመጣ  አምላክነቱን ትቶት ነው የመጣው  ለዛ ነው ተቀበልኩ  እያለ ነው። መጨረሻ ላይ ከሰማችሁት ይህ ካልገባህ ወንጌል አልገባህም አለው 😁 🌠 አንተ ምን ትላለህ ካላችሁኝ ለጭቅጭቅ የዳረጋቸው ነገር መጀመሪያ ያለ መረጃ የተቀበሉት ነገር አለ ሁለቱም። ኢየሱስን እንዲህ ብለው የምናሉ :- 🔴 የእግዚአብሔር ቃል ነው ብለው ያምናሉ እሱ ግን ነኝ ብሎ አያውቅም 🔴 አምላክ ነው ብለው ያምናሉ ነኝ ብሎ ግን አያውቅም 🔴 አምላክ በመለኮት 1 በአካል ሶስት ነው ብለው ያምናሉ እሱ ግን አስተምሮ  አያውቅም ... ኢየሱስ ለልሹ ያልሰጠውን ምንነት ሰጥተህ አምላክ ነው ብለህ ከገባህ ስልጣን ተቀበልኩ ሲል አምላክ ነው ብለህ የተሸከምከው ሀሳብ ሊወድቅ ይንገዳገዳል ።ስለዚህ  አንድ ውሸት ሁሌም ሌላ ውሸት ስለሚፈልግ ሀሳቡ እንዳይወድቅ ሌላ ውሸት መጨመር ያስፈልጋል። ሁለተኛው ውሸት ላይ ነው መስማማት አቅቷቸው የሚከራከሩት።    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

ማስጠንቀቂያ 🔴 በውስጥ አብዱልከሪም የንፅፅር ትምህርት ያስተምራል እያሉ እህት ወንድሞችን የሚቀፍሉ ልጆች እንዳሉ ሰማሁ ። አንዲት እህት 15 ሺህ ብር እንደበሏት አሳየችኝ ። guys እኔ ቻናል አ
ማስጠንቀቂያ 🔴 በውስጥ አብዱልከሪም የንፅፅር ትምህርት ያስተምራል እያሉ እህት ወንድሞችን  የሚቀፍሉ ልጆች እንዳሉ ሰማሁ ። አንዲት እህት 15 ሺህ ብር እንደበሏት አሳየችኝ ።   guys እኔ ቻናል  አለኝኮ ትምህርት ቤት ቢኖረኝ እዚህ እናገራለሁ ። በቲክቶክም አሳውቃለሁ።  ደግሞ በምን ሂሳብ ነው 15 ሺህ ብር የማስከፍለው ?  ይሁን ቢያንስ በድብቅ ነው የሚያስተምረው ብትባሉ እንኳን በራሱ በሚታወቀው  የቲክቶክ አካውንት ራሱ ያናግረኝ አትሉም ? እሺ በቴሌግራም በስሜ ከፍተው ቢያናግሯችሁ አብዱልከሪም መሆንህን ለማወቅ  በድምፅ አውራኝ አትሉም ?? በጣም አዝኛለሁ! በዲን ስም የምትነግዱ ደግሞ አላህን ፍሩ ! 🌠 እኔ ምንም አይነት የንፅፅር ትምህርት ቤት የለኝም !!  ሲኖረኝ ራሴ እዚህ እናገራለሁ ። አለቀ  ተጠንቀቁ

በሀሳብ ለፈጠሩት ለራሳቸውም ያልገባቸውን አምላክ ሲያስረዱ የሚሰጡት አስቂኝ ምሳሌ ኦርቶዶክስ ወገኖች ስላሴን እናስረዳለን እያሉ  አንዴ በፀሀይ አንዴ በእንቁላል  አንዴ በባጃጅ ጎማ.. ..ወዘተ..... እየሞከሩ ሲያስቁን ከርመው ይኸው አሁን ፕሮቴስታንቶችም ስላሴ ተጥዶ የሚፈላ የሚገነፍል ነገር አድርገው ማቅረብ ጀመሩ። አብ ይጣዳል ወልድ ይፈላል መንፈስ ቅዱስ ይገነፍላል ሲባል እንዴት ነው ነገሩ 1️⃣ አብ ሲጣድ ወልድ እና መንፈስቅዱስን ይዞ ተጥዶ ገብቶ ከዛ ሙቀቱን እሱ ተቋቁሞ ነገር ግን ከሙቀቱ የተነሳ ወልድ ፈልቶ መንፈስ ቅዱስ ነው የገነፈለው ? 2️⃣ አብ ብቻውን ተጥዶ በሙቀቱ  ምክንያት ሲፈላ ወደ ወልድ ተቀይሮ ነው ? ከዛ ወልድ ከሙቀቱ የተነሳ ከመፍላት ወደ መገንፈል ውስጥ ገብቶ ነው መንፈስ ቅዱስ የተባለው  ? የሚያፈላቸውስ ማን ነው ?? 🌠 በምንነትም በማንነትም አንድ አምላክ ማምለክ እየቻለ እንዴት ሰው 3 አምላክ ለማምለክ ይታገላል ? አላህ ይምራችሁ !! 🌐 ኢየሱስ በአጭር ቃል እንደማንኛውም ፍጡር አምላክ እንዳለው  ወደ ሁላችንም አምላክ እንደሄደ ተናግሯል። 📕   ዮሐንስ 20፥17 “ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።” 🌐 ጳውሎስም አምላኩን ያውቃል ። አምላኩን በኢየሱስ ነበር የሚያመሰግነው። ኢየሱስን ሳይሆን አምላክን በኢየሱስ በኩል። 📕 ሮሜ 1፥8 “እምነታችሁ በዓለም ሁሉ ሾለ ተሰማች አስቀድሜ ሾለ ሁላችሁ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።”    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

በሰሞኑ አርሲ ጉዳይ እስልምናን ለማጠልሸት ድራማ እየፈጠሩ ነው ። ብዙ ቪድዮ እያራገቡ ነው። ይህ የገረመኝ ቪድዮ ነው ከመነሻው ቪድዮው እንኳን እውነት ሊሆን ለአቅመ ድራማ እንኳን አይበቃም ። የትኛውም ሙስሊም ጂሃዲስት ብሎ አይጠራም። ጂሀድ የሚለው  መሠረተ ቃል ትርጉሙ  ትግል ሲሆን  የሚታገለው አካል ሙጃሂድ ነው የሚባለው ። ከእስልምና ውጭ ያሉት በተለይም ምዕራባውያን ናቸው ስለማያውቁ ጂሃዲስት እያሉ የሚጠሩት ። ማንም ሙስሊም ጂሃዲስት አይልም 😁 ። 🌠 ኦርቶዶክሶች  በአርሲው ጉዳይ ተደብቀው የአክሱም ድምፃችንን ረግጠው ራሳቸውን በሙስሊሞች የተጎዱ አድርገው ተቀምጠዋል። የሙስሊም ሚዲያዎች ታሪካዊ ስህተት ነው የሰራችሁት ። ፍትህ ለአርሲ እያላችሁ ዘላችሁ መቀላቀል አልነበረባችሁም። ለብቻችሁ ፍትህ ለአክሱም እና አርሲ ብላችሁ ኦርቶዶክስም ሌላ ቦታ ላይ እረገጠች መሆኗን መናገር ነበረባችሁ። የፖለቲካ አላማቸውን ሳታዩ እንዲሁ ቅን ልብ ብቻ ይዛችሁ ስታራግቡላቸው  ይኸው አርሲ ላይ ንፁሃንን የገደለው  ሸኔ ነው ቢባሉም አላማቸው አርሲን  ሰበብ አድርገው ሙስሊሙ ያገኘውን ነፃነት መርገጥ ስለሆነ ዞረው ገዳዮቻችን ሙስሊሞች ናቸው  ገድለውን ሲያበቁ  አብረውን ያለቅሳሉ በማለት መጮህ ጀመሩ። እናንተም እኛ አይደለንም የገደልነው እያላችሁ እነሱ አልቃሽ እናንተ ደግሞ እሹሩሩ ባይ ሆናችሁ። ለሌላ ጊዜ ተማሩበት ተዘሎ በስሜት አይገባም ። የፖሊቲካ አላማው ይታያል መጀመሪያ ። የሙስሊም ሚዲያዎችን ያህል ፕሮቴስታንቶች አላሽቃበጡም። ፕሮቴስታንቶች ያውቃሉ የኦርቶዶክስ ፅንፈኞችን አላማ። ተማሩበት ለሌላ ጊዜ !    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

+1
ሙስሊሞች መች እንደምትነቁ አላውቅም ። ከላይ እስቲ የአንድ ሰው ቪድዮ ምሳሌ ይሆናችሁ ዘንድ ላሳያችሁ ። የመጀመሪያውን ቪድዮ ስታዩት ዲያቆኑ አርሲ ሰው ሞተብን እዬዬ እያሉ ምን እናርግ ብለው መንግስት ክዶናል እያሉ ሲጮኹ ያሳያል። ሲታይ በቃ ለአርሲ ንፁሃን ሞት ብቻ የሚጮኹ ይመስላል። ሁለተኛውን ደግሞ ተመልከቱ ። ዲያቆኑ ልሹ ደግሞ  አክሱም ላይ መስጊድ ይሰራ የሚለውን የሙስሊም ድምፅ መጥፋት አለበት የኦርቶዶክስ ሲኖዶስ መልስ ይስጥ እያለ ጭቆናውን እንዲቀጥል ሲናገር ይታያል።  🌠 ይኸውላችሁ አርሲ ላይ ሰው ሞተ ብለው ሰሞኑ መንግስት ላይ የሚጮኹት ይህን ሰበብ አድርገው የድሮው ፈላጭ ቆራጭነታቸው እና ተፅዕኖ ፈጣሪነታቸው ስለቆመ ያ ተሰሚነታቸው እንዲመለስ ይህን ሰበብ አድርገው መንግስት ላይ ብዙ ነገር ጫና ለማድረስ ነው። አንተ ዘለህ ተሰልፈህ አብረህ ትጮኻለህ ?? አርሲ የሞቱት ያሳዝናሉ መሞት የለባቸውም ኢስላም ለሰው ያዝናል ። የትኛው የቁርአን አንቀፅ ነው ጅል ሁን ያለህ ደግሞ ?? የፖለቲካ ዜማቸው ካለቀ ቡኃላ እኛ ሙስሊሞች በገንዘብም ሆነ በሌላም አርሲ ያሉትን ወገኖች ማገዝ መደገፍ እንችላለን ። አክሱም ያሉትን ኦርቶዶክስ ናቸውኮ ረግጠው ይዘው ያሉት ። ከረጋጭ ጋ ተሰልፈህ ሾለ ረገጣ ትቃወማለህ ?? 🌠 ሌላው አህባሾች ደግሞ ተረጋጉ በራሳችሁ ሳንባ ተንፍሱ ። ነገር በመጣ ቁጥር አራጋቢ አትሁኑ ... አርፋችሁ ታቦት ሲወጣ እና ሲገባ አልሃምዱሊላህ በሉ ! ።    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------

የሙስሊሞች የተሳሳተ የተቃውሞ መንገድ እኛ ሙስሊሞች የማንንም ንፁህ ሰው ሞት እንቃወማለን  እናወግዛለን ። አርሲ የደረሰውን ሞት እንቃወማለን ነገር ግን የምትቃወሙበትን መንገድ አስተካክሉ። ዘለህ ኦርቶዶክስ ተገፋች ተገደለች  ተጨቆነች  አትበል ! አክሱም ላይ በሰላም ለመኖር ተውና  ለመሞት እንኳት አትቀበሩም ታረክሳላችሁ በማለት ሙስሊሞችን ረግጠው ያሉት እነማን ሆኑና ? ራሳቸው ኦርቶዶክስዎች ናቸው። የአርሲ ንፁሃንን ሞት  ብቻ ነጥለህ ተቃወም !  የንፁሃን ደም መፍሰስ የለበትም ። የኦርቶዶክስ የፖለቲካ መስሪያ ድምፅ አትሁን። 🌐 ለመቃወም ከፈለክ በምን መልኩ እንደምትቃወም  2 ናሙና ልስጥህ ናሙና 1️⃣ "በአርሲ የደረሰውን የንፁሃን ሞት እና በአክሱም ሙስሊሞች ላይ ኦርቶዶክስ የምታደርሰውን ስቃይ እቃወማለሁ " ናሙና 2️⃣ " ለአክሱም ሙስሊሞች ስቃይ እና ለአርሲ ንፁሃን ሞት መንግስት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጠን እንጠይቃለን " ከላይ ያሉትን ናሙናዎች  መንገዱን ላሳያችሁ እንጂ በተሻለ መልኩ ፅፋችሁ ሀሳባችሁን መግለፅ ትችላላችሁ ።    ✍️ Abdulkerim https://t.me/Facethetruth22 ------------------------------------------------------