en
Feedback
𝗧𝗲𝗿𝗶𝗾𝗮𝘁 𝗔𝗹- ሁብ

𝗧𝗲𝗿𝗶𝗾𝗮𝘁 𝗔𝗹- ሁብ

Open in Telegram

ልብ ከ ከጥልቅ ሲፅፍ ብእሩ የሚመታ ልብ አለው🔎🖋️

Show more
1 748
Subscribers
+924 hours
+417 days
+15630 days
Posts Archive
🔥የድል ረመጥ🔥 ክፍል 3 አገኘው መብረቅ የመታው ይመስል ደርቆ ቀረ። እሚለው ጠፋው ከአንድ ቀን በፊት ከስሩ ሆኖ ሲሰራ እንደ አለቃ ሳይሆን እንደ አባት የሚወደው፣ ሰው ጥሩ እና ትሁት የነበረለት ብቸኛ ሰው መሞት ከፋው፣ አስደነገጠውም። ወንጀሉን የያዘው ኢንስፔክተር ያየህይራድ በቃሉ ከአገኘው ሁኔታ በመንተራስ የምርመራ መስቀለኛ ጥያቄውን ያቀርበለት ጀመረ። "አቶ አገኘው፣ ከሟች ጋር ያላቹ ግንኙነት እንዴት ነበር? ባደረግነው ምርመራ መሰረት ሳይቱ ላይ ካሉ ሰራተኞች ሟችን እንደ እርሶ እሚቀርባቸው የለም።" አለው። እውነታውን ከአንደበቱ ይልቅ ከዓይኖቹ የሚያድን ይመስል ነበር፣ ትክ ብሎ ሲመለከተው ላየ። አገኘውም የተናነቀውን የእምባ ሳግ ለመግታት እየሞከረ፣ "ልክ ኖት፣ ኢኒስፔክተር፣ በተቻለኝ አቅም ስራዬን በአግባቡ እሰራለሁ። ሚስቴ እንዳያችኋት ነብሰ ጡር ናት፣ መውለጃዋ ስለተቃረበ ቤተሰቤም በአንድ እጥፍ ሊያድግ በመሆኑ ከወትሮው በተለየ ገንዘብ ስለሚያስፈልገኝ ይበለሰጥ እተጋለሁ። ኢንጂነር አብዱል ረዛቅም ለዚሁ ተግባሬ ይወዱኛል፣ እኔም አከብራቸዋለሁ። አንዳንዴም አብረን ከስራ እንወጣለን። በዚ ገቢ ቤተሰብ መምራት መቼም ከባድ ነው። ጠንክረህ ስራ እማያልፍ የለም ሲሉ ተስፋ ይሰጡኛል አልፎም ጭብጥ ገንዘብ ጉያዬ እየወሸቁ፣ አይዞህ ይሉኛል።" ሲል መልካምነታቸው እያወጋ ሊዘልቅ አልቻለም። የተናነቀው ሳግ አቋረጠው። መርማሪውም ስጋ እንዳየ አሞራ በአገኘው ዙሪያ እያንዣበበ፣"እንዲህ ያሉ ጥሩ ሰው ከነበሩ፣ ስለምን ልትገላቸው ወሰንክ? ያጎረሰን እጅ መንከሱስ ተገቢ ነውን? በሳቸው ላይ ለመጨከን ያነሳሳህስ ምንድነው? በመሐከላቹ ፀብ ነበር ወይ? ገንዘብ ሰለሚያስፈልግህ ከሌላ አካል በተሰጠህ ትዛዝ ነው ነፍሳቸውን ያጠፋኸው? አሁን የአዞ እንባ ማንባትህን አቁምና እውነቱን ብቻ መልስልኝ። ምናልባትም ቅጣትህ ይቀልልህ ይሆናል!" አለው፣ ጠረፔዛውን በጡጫው ተደግፎ የአገኘውን ዓይኖች በጥልቀት እየተመለከተ። የአገኘው ምላሽ ግን፣ ፍፁም አላደረኩትም፣ በሰውም ትእዛዝ በራሴም ተነሳሽነት ይህንን ወንጀል እኔ አልፈፀምኩም የሚል ቁርጠኝነት የተሞላበት ነበር። መርማሪውም የምፀት ፈገግ እያለ፣ "ይሄ ምላሽ ነፃ እሚያወጣህ ይመስልሃልን? ፖሊስ ያለመረጃ አይወነጅልም። እንደምትለው ንፁ ብትሆን እዚ ባልተገኘህ ነበር። 1ኛ፣ እንደነገርኩህ ትናንት በመኖሪያ ደጃቸው ላይ ተጥሎ ያገኘነውን የሟችን አስክሬን ስንመረምር፣ በጃኬታቸው አንገት ማለትም ኮሌታ ላይ የአንተ አሻራ ነበር የተገኘው። 2ተኛ፣ ሟች ሕይወታቸው ያለፈው በመንደራቸው ሳይሆን በስራ ቦታቸው ነበር። ያ ማለት አስክሬናቸውን ለማዘዋወር የረዳህ ሰው እንዳለ እና ብቻህን እንዳላደረከው ያሳያል። 3ተኛ፣ በግንባታ ሳይቱ ላይ በደረግነው መረጃ የሟችን ደም የያዘ አካፋ አጊንተን ነበር። አካፋውም ያንተ መገልገያ ሲሆን አሻራው ትኩስነቱ ከሟች አስክሬን ጋር ተመሳሳይ የሰዓት አድሜ ነበረው። 4ተኛ፣ እንዳንተው ምርመራ ያደረግንባቸው የቀን ሰራተኞች እለተ ረቡዕ ቀትር ላይ ስትጨቃጨቁ፣ ማለትም ሟች በርሶ ላይ ሲቆጡ ማይታቸውን መስክረዋል። 5ተኛ፣ ድርጊቱ በተከሰተበት እለት ከወትሮው አምሽተው ወደ ቤት መግባቶን፣ ለባለቤቶም ወድ ቀሚስ ገዝተው መግባቶ እንዲሁም ሀሙስ እለት ከስራ ገበታ መቅረቶን ጨምሮ፣ አስካሁን የገኘናቸው ፍንጮች በሙሉ በትክክል ድርጊቱን መፈፀሞን ይናገራሉ። ስለዚህ፣ ከዚ ጀርባ ማን አብሮት እንዳለ፣ ገመዱን የያዘውስ ማነው የሚለውን እውነቱን በማጋለጥ ለኛም ስራችንን ለርሶም ቅጣቶን ያቅሉ።"ሲል አምባረቀበት። በአኘው ዝርዝሩን ሲሰማ ምድር ተደባለቀችበት። በጆሮው ውስጥ ድምፆች ያስተጋቡ ያዙ፣ ለምን እሚሉ ጥያቄዎች ይመላለሳሉ። አብሯቸው ድንጋይ ሲፈልጥ፣ ሲሚንቶ ሲሸከም፣ ብረት ሲያግዝ ከሚውላቸው ባልደረቦቹ አንድ እንኳ እሱ ይሄን ሊያደርግ አይችልም እሚል ቃል የሰጠ አለመኖሩ ልቡን ሰበረው። ሆኖም ግን፣ ንፅህናውን የሚያውቀው አገኘው ሁሉንም በለዘብታ ተረጋግቶ ማስረዳት እንዳለበት በማመን፣ አንድ በአንድ ሁኔታውን ማስረዳት ጀመረ። "ኢኒስፔክተር፣ የገለፅከው ሁሉ ስህተት የለውም። በወቅቱ ኢንጂነር የተቆጡት በኔ አልበረም። መበሳጨታቸውን ባየው ግዜ ነበር ስራዬን አቋርጬ የጠየኳቸው። እሳቸውን ያስቆጣቸው የአቅርቦት እቃ ጥራት ጉለት ነበር። ያቀን ሲበሳጩ የመጀመሪያ አልነበረም። እርግጥ ነው፣ የአቅርቦቱ ኋላፊነት ላይ የተመደበው ማን እንደሆነ አላውቅም። ነገር ግን፣ ከተበጀተው በጀት ላይ በዋጋ ቅናሽ፣ በጥራትም እምብዛም ያልሆነ የግንባታ እቃ በማቅረብ የተቀረውን ገንዘብ ልግል ጥቅማቸው እያዋሉ መሆናቸውን ያወቀው ኢንጂነር በሃላፊነቱ ላይ ያሉት አካል ጋር በተደጋጋሚ ግጭት ይገጥማቸው ነበር። ነገሩንችላ በማለት እሷቸውም የጥቅሙ ተካፋይ እንዲሆኑ ቢጠየቁም እምቢኝ አሻፈረኝ ሲሉ በቤተሰባቸው ይዝቱባቸው ነበር። ያን ቀንም ይሄን በቁጣ ሲያስረዱኝ ነበር እንጂ፣ ምክኒያቱ እኔ አልነበርኩም። በተጨማሪም እዚያ የምንሰራ የቀን ሰራተኞች እቁብ አለን። ያንቀን ለኔ ነበር የደረሰኝ። ካጠራቀምኩት ጨምሬ ለባለቤቱ የምትወደውን ቀሚስ ገዛሁላት። ዘወትር አብረን ከስራ የምንወጣ ሲሆን፣ ያን ቀን ግን እዚ የምጨርሰው ጉዳይ አለኝ ሲሉኝ፣ ሁሌም እንደማደርገው ኮታቸውን ከሚሰቅሉበት አውርጄ ከሰጠኋቸው ኋላ ለነጋታው ሚስቴ ክትባት ስላላት ፍቃድ ጠይቄ ተሰማምተውኝ በግንባታው ቦታ ላይ ታቻቸው ወጣሁ። ነገር ግን፣ ቀሚሱን ገዝቼ ወደቤት ልሄድ ስል የምሳቃዬን መርሳቴ ሲታወሰኝ ወደ ሳይቱ ተመለስኩ። ጨለምለም ብሏል እኔ ስደርስ፣ ኢንጂነር አልነበሩም። ያለወትሮው አካፋዬን ካለቦታው ሳየው፣ እንዴት እዚ ተውኩት ስል እያጉረመረምኩ አንስቼ ቦታው ከመለስኩ ኋላ የምሳ እቃዬን ወስጄ ወደቤቴ ሄድኩ። ነገር ግን፣ ዝናብ በመንገዴ ያዘኝ እና አምሽቼ ነበር የደረስኩት። ፍቃድ ስለነበረኝ ሀሙስ እለት ስራ አልገባሁም። ከባለቤቴ ጋር ቤተሰብ መምሪያ ነበርኩ።አሁን ትዝ ያለኝ ነገር ግን፣ ኢንጂነር ክፉ ቀን መምጫው አይታወቅም አገኘው፣ ጠላት ሲኖህ መጠንቀቅ ይበጃል ከእሱ እኩል መራመድ ባትችል፣ ወይም ባትቀድመው እንኳ ከኋላው አትቅር፣ ከትንፋሹ ቅርብ ሁን ባታተርፍ እንኳ አትከስርም፣ ሲሉ እያወጉኝ የሰቀሉት ካሜራ ከግንባታው 2ተኛ ወለል ላይ አለ። ጠቃሚ ነገር የምታገኙ ከሆነ እሱን ፈትሹት። እኔ ግን ነፃ ነኝ። ከዚህ ውጪ የምለው የለኝም።" ሲል ንግግሩን ቋጨው። ለመርማሪውም አሳማኝ እና አዲስ ጠቃሚ መረጃ ነበር። ቢሆንም ግን፣ እስኪጣራ ንፅህናው እስኪረጋገጥ ማረፊያ ቤት እንደሚቆይ ተነገረው። ምን ይዋጠው? ወኔው ከዳው፣ ሰውነቱ ራደ። ነብሰጡሯ ሚስቱ፣ ዘመድ የሌላት ብቸኛዋ እመቤቱ ፊቱ ድግን አለችበት። ግን ምንም ማድረግ አይችልም። በሃዘን ከመዋጥ እና በቁጭት ከመብሰልሰል በቀር። ደራሲ✍🦋zewa🦋

Repost from N/a
➲የተለያዩ ዲናዊ ምክሮች📝 ➲ቁርዓን እና ሀዲስ የምታገኙበት📖 🧩 áˆáˆ­áŒĽáŠ“ ተወዳጅ ቻናል ✨       # ተቀላቀሉ ✅👇

Repost from N/a
🌀 ለቻነል ባለቤቶች በሙሉ👇 👉ኑ በነፃ 💯 ቻነል እናሳድጋለን ፈጥነው ያስመዝግቡ 📥 ለ ተወሰኑ ቻነሎች ብቻ ቦታ አለን 🏃‍♂‍➡️          🧩 ቻናላቹ👇 🎯Above 1k+ subscribers✅ ከ1ሺ በላይ ተከታዮች ሊኖረው ይገባል      🌀 ቻናል ለማስመዝገብ አናግሩኝ  ... ........  👇👇........... ...... @selluhi 👉Logo እንሰራለን 👉video edit እናደርጋለን 👉ለሽያጭ የቀረቡ ኢስላማዊ ቻናሎችም አሉ

⚰በቴሌግራም ምርጥ ምርጥ እስላማዊ ቻናል  ይፈልጋሉ❓ ስልኩን📞 በመጫን ብቻ ይቀላቀሉን😀 📞📞ለመ🀄️ለ🀄️ል📞📞        ≼😀😀👇≽ ┌───────────┐╯ ‌│⫸╭─━━━━━━╮⫷│╯ │⫸│  ╰─ â” â”€â•Ż    │⫷│╯ │⫸│▅▅▅▅▅▅▅│⫷│╯ ‌│⫸│╰╮ • ★•╭╯   │⫷│╯ │⫸┃┊  🄷🄷🅆  ┊    ┃⫷│╯ ‌│⫸┃┊  🄳🄳🅅  ┊    │⫷│╯ │⫸┃┊  🄷🄳🄴  ┊    ┃⫷│╯ ‌│⫸┃┊  ▓⓪▓  ┊    ┃⫷│╯ │⫸┃╰─◦◇◦╯    ┃⫷│╯ ‌│⫸┃██████    ┃⫷│╯ │⫸│→         â”        ←┃⫷│╯ │⫸╰━━━━━━━╯⫷│╯ ╰━━━━━━━━━━━╯╯ ❤️𝐀𝐝𝐝 📌✅ 𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥                   👇👇 😀 𝐖𝐚𝐯𝐞 :-@HudHud_waver

Repost from N/a
አዲስ ስራ ለሚፈልጉ፣ ስራ መቀየር ላሰቡና የተሻለ የስራ አማራጭ ለሚፈልጉ ሐላል ጆብስ ቤታቸው ነው። እንዲሁም ቀጣሪዎች የስራ ማስታወቂያቸውን በነፃ እንዲለቁበት በማሰብ የተዘጋጀ ቻናል ነው!👇

🔥የድል ረመጥ🔥 ክፍል 2 ብዙም ሳንጓዝ "በይ ደርሰናል፣ እንውረድ። መኪናሽን የኛ ሹፌር ቦታው ያደርሰዋል" አለቺኝ።😱 ገና ከመግቢያው ነው የተገረምኩት። የበሩ ውበት ለማየት አያሰለችም፣ ውስጡ ምን ሊመስል እንደሚችል እያጤንኩ ዘለቅኩ። ስሙኝ እማ፣ ቆይ white house ያለው አሜሪካ አይደለምን?🤔 የቤቱ ግርማ እና ግዝፈት በቃል ለመግለፅ የሚመች አይደለም። የግቢው መሬት ተፈጥሮ ባበቀለችው ሳርና አለፍ አለፍ ብሎ መሐል ላይ በተሰደሩት ጠፍጣፋ ድንጋዮች አጊጧል። በውስጡም የተተከሉት የፎራፍሬና የዋርካ ዛፎች አማዞንን ያስንቃል ውበት እና ብዛታቸው። የአበቦቹን ከንፈር የሚስሙት በተለያየ ህብረ ቀለም ያሸበረቁት ቢራቢሮዎች እና ንቦች የተለየ ስሜት ይፈጥራሉ። የአእዋፋቱ ፉጨት ከእርግቦቹ ጥምረት የጥንቸሎቹ ውር ውር ማለት ከድመቶቹ ሩጫ ጋር ተዋህዶ የተጠና ትርዒት አስመስሎታል። ወደግራ ዞር ስል አምበሳ የሚያስንቅ ግርማሞገስ ያለው ጨዋ ውሻ ተኝቷል። በውበቱ እየተደመምኩና በአንድ ምድር ላይ የሚኖሩ ግና የሰማይና የምድርን ያህል የተራራቀ ኑሮን የሚገፉ ፍጥረትን እያሰብኩ የለኝን ለሰጠኝ አላህ ልባዊ ምስጋናዬን እየቸርብኩ ከፊት እሰቀድማኝ ወደ ውስጥ ዘለኩ። እናንተዬ በአንድ ግቢ ውስጥ የተለያየ አለም ይኖራል? ቤቱ የሰከነና ውብ ነው። ነጭ ሴራማኩ ግድግዳው ከተቀባው ግራጫ ቀለም ጋር የተለየ ውበት ፈጥሯል። ፈንጠር ብሎ ያለው የመመገቢያ ጠረፔዛ የነገስታት ማዕድን ያስታውሳል፣ በሱ ትይዩ ፊትለፊት ላይ ዙሪያውን በወርቃማ ቀለም ያሸበረቁት ነጫጭ ሶፈዎች ከውበታቸው የአቀማመጥ ስርዓታቸው የንጉስ መንበርን ያስንቃሉ።በመሃከላቸውም ለውበታቸው የሚመጥን ጠረጴዛ በነጭ የፈር ምንጣፍ ላይ ተኮፍሷል። የቴሌቭዥኑ ስፋት ከአ.አ ስታዲየም የኳስ ሜዳ ይስተካከላል ብል ግነት አይሆንም፣ የግድግዳው ሰዓትና ጌጦች ትኩረትን የሚስቡ ናቸው። የዕጣኑና እየተቆላ ያለው ቡና መዓዛ ልቤን ገዝቶታል። እንድቀመጥ እየጋበዘቺኝ መጣት፣ የምፈልገውን ትኩስ ነገር አማረጠቺኝ ካላስቸገርኩ ቡና በወተት ከውሃ ጋር እንዲመጣልኝ እየነገርኳት ተቀመጥኩኝ።  "ተጫወቺ እንጂ ሂልዊ ቤቱን እንዴት አየሽው?" የሚለው ከሷ አንደበት የፈለቀው ቃል ዝምታውን እስኪሰብረው ድረስ። “ቆንጆ ነው፣ ነፍፍፍ ዓመት በደስታና በአፊያ ኑሪበት” አልኳት፣ ፈገግታዬን እየመረኩላት። “መጀመር እንችላለን?” ስል ጠየቅኳት፣ ከቦርሳዬ የድፅ መቅጃ ማስታወሻ ደብተር እና እስክሪብቶ አውጥቼ ከጠረጴዛው እየዶልኳቸው። “እንዴታ እንችላለን” አለቺኝ ፍፁም ትሁት ሁና። የድምፅ መቅጃዬን አስጀምሬው ስክሪፕቶዬን ከማስታወሻዬ እያገናኘው ከአንደበቷ የሚወጣውን የእናቱን ጡጥ ለመጥባት እንደሚጠባቀቅ ሕፃን አሰፍስፌ እጠባበቅ ጀመርኩኝ። ይኸውልሽ ታሪኩ የተፈፀመው ከዛሬ 26 አመት በፊት በሰኔ ወር እለተ ዐርብ ቀን 27 በአነስተኛ መንደር ውስጥ ነበር። የዛሬውን ቀን መርጬ የቀጠርኩሽም ዛሬ የ27ተኛ አመቱ መጀመሪ ቀን ሰለሆነ ነው። ሌሊቱን ሙሉ ያለማቋረጥ ሰዚንብ ያደረው ዝናብ ነጋቱን ጨምሮ መዝነቡን ተያይዞታል። አስደንጋጭ መብረቅ ሰማዩን ሲያርሰው ደመናው አምርሮ ያነባል። መሬቱን ያጥለቀለቀው ጎርፍ ቆሻሻ፣ ባዶ ጀሪካን፣ ሃይላንዶችንና አንዳንድ እግር ጫማዎችን እያንሸራሸረ ያልፋል። ከዝናቡ ለመጠለል በየሱቁ ጥጋጥግ ኩርምት ብለው የተወሸቁት ሰዎች የድባቡ አንድ አካል ናቸው። ይህ አስፈሪ ዝናብ ከመከሰቱ ሶስት ወራት በፊት በዛች አነስተኛ መንደር በአንድ ደሳሳ ጎጆውስጥ የሚኖሩ አገኘው ተመስገን አና ፅገሬዳ አበበ የተሰኙ ጥንዶች ነበሩ። ለኑሮ የሚለፉ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ምስኪኖች ናቸው። ፅገሬዳ የስድስት ወር ነፍሰጡር ናት። መውለጃዋ እየተቃረበ በመሆኑ አገኘው ከበፊቱ በበለጠ ይተጋል፣ ለምሳ አይመለስም አምሽቶ ነው ቤቱ የሚገባው። የሚሰራውም በኮንስትራክሽን ስራ ላይ በመሰማራት ሲሆን የቀን ሰራተኛ ነበር። ጥሩ ስነምግባር ያለው አንገቱን ደፍቶ እንደተጨመተ ወጥቶ የሚገባ ሰው ነው፣ ፀብ አያውቀውም። በስራው ትጉ በምግባሩም መልካም ስለሆነ ግንባታውን የሚመራው ኢንጂነር በጣም ይወደዋል፣ በሳይቱ ላይ ካሉ ሰራተኞች እንደሱ የሚያቀርበው ሰው የለም። በዛም የተነሳ አንዳን ሰራተኞች አገኘውን ይተቹታል። ከኛ በምን ተለይተህ ነው በሱ ለመወደድ ስታሸረግድ እንጂ ሲሉ ይሸነቁጡታል። ሆኖም ግን ክፉ አይወጣውም ሰርቶ ገንዘብ ማግኘትን እንጂ ፀብ አይወድም።ታዲያ አንድቀን ጠዋት እንደሁል ግዜው ሀገር ሰላም ብሎ አገኘሁ የሚስቱን ግንባር ስሞ ወደስራው ለማቅናት ገና እግሩ ደጅ ከመሽሎኩ ፖሊሶች መጥተው የመጥሪያ ወረቀት እያሳዩት ለጥያቄ እንደሚፈልጉት ነገሩት። ግራም እንደመጋባትም እንደመደንገጥ እንደመፍራትም ስሜቱ ዋዠቀበት፣ ፊቱን ላብ አጠመቀው። አንደምንም እራሱን ሰብስቦ ምን አጠፋሁ ከሰው እንኳ የማልጋጭ ለፍቶ ከዳሪ ነኝ እማላውቀው ምን ወንጀል ፈፀምኩ ሲል ራሱን እንደመከላከልም እንደመማፀንም በሚመስል ለዘብታን በታጠቀ ድምፅ ጠየቃቸው። ፖሊሶቹ ግን እሱን ጣቢያ ስትደርስ የምታውቀው ይሆናል የሚል ከውሃ የቀጠነ ምላሽ ሰጥተውት እጁን በካቴና ጠፍንገው ይዘውት ወደጠቢያ አመሩ። አገኘውም ግራ በመጋባት ስሜት ይከተላቸዋል፣ ባለቤቱ ልከተልህ ብትለው ፍፁም እርግጠኛ በሆነ ስሜት እንዲህ አላት፦ “የኔ አበባ፣ የኔ ፅገሬዳ፣ እኔ ያንቺ ባል ምንም ወንጀል አልፈፀምኩም፣ የሆነ ያለመግባባት እንደተፈጠረ ግልፅ ነው፣ ስለዚህ የምትሰጊበት ምንም ምክኒያት የለም። ለሚጠይቁኝ ጥያቄ መልሱን ካገኙ እዛ አያቆዩኝም፣ ስመለስ ያማረሽን ብርቱካን ይዤልሽ እመጣለሁ” አላት፣ ዓይኖቹን እያንከራተተ። ነገሩን ከበራቸው ጥግ ቆመው እሚያስተውሉት ጎረቤቶችም ያንሾኳሽኩ ይዘዋል። ግማሹ እንደው ይሄ ምስኪን ምን አደረገ ነው እሚሉት፣ ጭምትነቱ ከመልአክ እንጂ ከሰው አማይመል ሲወጣ ሲገባ ድምፁ ተሰምቶ የማያውቅ ጥብቅ ምፅ እያሉ ከንፈር ይመጣሉ። ግማሾቹም አንገት ደፊ ሀገር አጥፊ አሉ፣ የሰራውን ማን ያውቃል፣ ይሄኔ ከሚሰራበት ዘርፎ ይሆናል ማን ያውቃል ሲሉ አሉባልታ መንዛት ይዘዋል። ሀበሻም አይደለን፣ በማያገባን መግባት የሰው ኑሮን መፈትፈት እና ሃሜት ከባህል አልባሳታችን በላይ የምንጌጥባቸው እንቁ ናቸው። ጥያቄ ቢፈጥርበትም በንፅህናው እርግጠኛ ሆኖ ጣቢያ ያቀናው አገኘው ልክ ከምርመራ ክፍል ሲቀርብ ፍፁም ነገሮች የተወሳሰቡ ሆነው አገኛቸው። እሱን በተለየ መልኩ ከሰራተኞቹ ለይቶ እሚወደው የሳይቱ ኢንጂነር አበዱል ረዛቅ ረዲ የተባሉትን ግለሰብ ሕይወት ቀጥፈዋል በሚል የመጠርጠሩን መርዶ አረዱት።              ደራሲ✍🦋zewa🦋

አላህዋ በትንሹ የዚን 1-10 እፈልጋለሁ ታውቃለህ ባያስፈልገኝ አልጠይቅም ዝምብለህ ጀባ በለኝ🥹🥹

የልብ ወለዱን የመጀመሪያ ክፍል እንዴት አያችሁት
Anonymous voting

የ ልብ ወለዱን የ መጀምሪያ ክፍል እንዴት አያችሁት ,
Anonymous voting

ከሕይወቴ ገፅ 1     🔥 የድል ረመጥ 🔥 ከሌሊቱ 11:00 Am ለሱብሂ ሰላት የሞላሁት አላርም ነበር የቀሰቀሰኝ። አህየይና ባዕደማ ማትና ብዬ ከተጋደምኩበት ነቃሁ። ውዱዕ አድርጌ የጌታዬ ሀቅ የሆነውን ነብያችን የአላህ እዝነት፣ሰላት፣ ሰላም እና በረከቱ በሳቸው ላይ ይሁንና የዓይኔ መርጊያ ሲሉ የሚጠሯትን፣ ለኔም የአኺራ ስንቄ የሚዛን ላይ ግራሜ የሆነችውን ሰላት ከጌታዬ ፊት ከተዋደቅኩ በኋላ የፍጡራን ሁሉ መመሪያ የሆነውን ቅዱስ ቁርዓን አንብቤ ለሥራዬ ራሴን ላዘጋጅ ተነሳሁ። የአላህ ሰላም፣ እዝነት እና በረከቱ ባሮቹ ሁሉ ላይ ይሁን። ሂልዋ አብደላህ እባላለሁ። በሥራዬ ጋዜጠኛ ነኝ፤ የምሠራውም የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ውስጥ ተቀጥሬ ነው። ዋና ርዕሴን ከሕይወቴ ገፅ ያልኩበት ምክንያት በዚሁ የሥራ መስኬ ላይ ከገጠሙኝ ታሪኮች ለእናንተ የማጋራበት የፅሁፍ አምድ ስለሆነ ነው። የሬዲዮ ጋዜጠኛ መሆን የተለየ ስሜት አለው። በሬዲዮ ጣቢያ ላይ እርሶ ቢሆኑ የተሰኘ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ነኝ። ሥራዬን በትጋት እሠራለሁ፣ የሚገባውን ክብርም እሰጠዋለሁ። በዚህ የሥራ ዘርፌ ላይ ብዙ የታሪክ ገፆች፣ ብዙ ዓይነት ማንነት እና ጥንካሬ ያላቸው ሰዎች ገጥመውኛል። የሰው ልጆች በፍፁም ይህቺ ምድር ባዘለችላቸው ነገር እርግጠኛ ሊሆኑ አይችሉም፣ ብቸኛው የምድር ገዢ የሆነው አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላ ቢሆን እንጂ። ጊዜ ያነሳል፣ ይጥላል፤ ጊዜ ያነግሳል፣ ጊዜ ለግዞት ይዶላል፣ ያከብራል፣ ያቀላል፣ ይቸራል፣ ይነሳል። በየትኛው ቅፅበት ምን ሊፈጠር እንደሚችል አናውቀውም። ኦውው! እናንተን ሳናግር ከሥራዬ አርፍጄ ነበር። በሉ፣ አብረን ወደ ሥራ እንሂድ። የጧት አድማቂ የሆነችው አይናፋሯ ፀሐይ ከመስኮቷ ብቅ እያለች ነው። እኔም ባለፈው ዓመት ለሥራዬ ባሳየሁት ታታሪነት የተሸለምኳትን መኪናዬን አስነስቼ ከቤቴ ወጣሁ። ታታሪ ሰዎች ልክ እንደታታሪዎቹ ንቦች እየተጣደፉ ወደ ሥራ ቀያቸው ይተማሉ። ቢጫ የለበሱ ምስኪን የፅዳት ሠራተኞች መንገዱን በማፅዳት ተጠምደዋል። አንዳንድ ኑሮን ለመግፋት የሚጣጣሩ ሴቶች ሻይና ፓስቲ ያዞራሉ። በመንገዱ አለፍ ብሎ ጋዜጣ ሻጮች ይታያሉ። በመንገዱ ጥጋጥግም ብርድ ያኮራመታየው ረሃብ የደቆሳቸው ሽማግሌዎች፣ እናቶች እንዲሁም ወጣቶች እራሳቸውን አቅፈው ተኝተው ይስተዋላሉ። ወደ ትምህርት ገበታቸው የሚፈልሱት ተማሪዎች ሌላው የጎዳናው ውበት ናቸው። ሱቃቸውን በመክፈት ላይ ያሉ ነጋዴዎችም የድምቀቱ አካል ሲሆኑ ይስተዋላል። አይደረስ የለምና፣ እኔም ደርሼ ወደ ሥራ ገበታዬ አመራሁ። እንደተለመደው ዛሬም ቀድሜ የደረስኩት እኔ ነበርኩ። ሁላችንም ከተሰበሰብንና ሁሉም ወደ ሥራ ድርሻው ከተሰማራ በኋላ፣ ፕሮግራሜን የምመራበት ወንበሬ ላይ ተቀምጬ ወረቀቶቼን፣ ማይክራፎኔን እና የመሳሰሉት መሣሪያዎቼን እያዘጋጀሁ የቴክኒሻኑን ምልክት በመጠባበቅ ላይ ነኝ። «ጤና ይስጥልኝ አድማጮቻችን፣ ዘወትር ረቡዕ ማለዳ 3:30 ላይ የሚቀርብላችሁ ‘እርሶ ቢሆኑ’ የተሰኘው ፕሮግራማችን እንሆ ተጀመረ። ፕሮግራሙን አዘጋጅቼ የማቀርብላችሁ እኔ ሂልዋ አብደላህ ነኝ። ከፕሮግራማችን ጋር መልካም ቆይታ እየተመኘሁ፣ ከአፍታ የሙዚቃ ግብዣ በኋላ ተመልሰን እንገናኛለን።» «ክቡራን እና ክቡራት አድማጮቻችን፣ ከሙዚቃ ግብዣችን ተመልሰናል። ዘና እንዳላችሁበት ተስፋ እያደረግን፣ በቀጥታ ወደ ዛሬው ታሪካችን እናልፋለን። እናንተም በቀጥታ የስልክ መስመራችን አሊያም በአጭር የመልእክት ሳጥን ቁጥራችን ሐሳብና አስተያየታችሁን አድርሱን።» «በሰኔ ወር ዓርብ ማለዳ ነበር። ስልኬ የጠራው ባለታሪካችን ነበረች የደወለችልኝ።»«ሃሎ፣ ደህና ደርሰሽ ሂልዊ?»«ደህና ደርሰሽ ወ/ሮ ፍትህ፣ እየመጣሽ መሆኑን እርግጠኛ ለመሆን ነበር።» አለችኝ ከሀር በለሰለሰ ድምፅ።«አዎን፣ እየመጣሁ ነው።»«አቅጣጫውን በደንብ ተረድተሽኛል አይደል? እንዳትቸገሪ አስቤ ነው።»ቅንነት ከልሳኗ ይስተዋላል።«አታስቢ፣ አይዞሽ። አካባቢውን በደንብ ስለማውቀው አይጠፋኝም።»«እሺ፣ ደና ሁኚ። እንገናኛለን።»ንግግራችን በእነዚህ የቃል ምልልሶች ተቋጨ። እኔም ወደተነገረኝ መንደር ሜክሲኮ መኪናዬን አስነስቼ በጎዳናው ላይ እንደውሃ ፈሰስኩ። አዕምሮዬ ማብሰልሰሉን ይዟል። ምን ዓይነት ነገር ይገጥመኝ ይሆን? አስደሳች ወይስ አሳዛኝ? አስገራሚ ወይስ አስደንጋጭ? እያልኩ ሳብሰለስል፣ ሳላስበው፦ «ስትደርሺ ደውይልኝ» ካለችበት መገንጠያ ስደርስ ከሰጠምኩበት የሐሳብ ባሕር ወለል ተንሳፈፍኩ እና ጊዜ ሳላባክን ወደ ስልኳ አቃጨልኩ።«ሃሎ!»«ወዬ፣ ሂልዊ!»ይህቺን እንስት ልመለከት ጓጓሁ። አንደበቷ ከውቅያኖስ መስከን እያስደመመኝ፣ ካልሺኝ ቅያስ ደርሻለሁ ወ/ሮ ፍትህ አልኳት።«መጣሁ፣ ጠብቂኝ። ብዙ አላቆይሽም።» አለችኝ።የጉንጮቿ ጡንቻዎች እስኪሰበሰቡ ፈገግ ያለች ይመስል ነበር። ብዙም ሳትቆይ ነበር የመጣችው። ዓይኔን ማመን አቃተኝ።በጠቢቡ ሰለሞን ዘመን ተፈጥራ ቢሆን ንግስት ሳባ ቅናት ይዟት ሰራዊት አሰልፋ የምትገጥማት ይመስለኛል እኛም ታሪካዊ ሀሜት ይኖረን ነበር።አቤት ውበት! የኔ ነገር አይታወቅም፤ ሳላውቀው ጀነት ገባሁ እንዴ? 🤔ስል ራሴን ቼክ ሳደርገው፣ እዛው መኪናዬ ውስጥ ነኝ። አጠገቤ ደርሳ የመኪናዬን መስታወት ስትቆረቁር፣ ከሄድኩት ሐሳብ ነቃሁ።«እ… መጣሽ እንዴ?» እያልኩ በሩን ከፈትኩላት።«የት ሄድሽ? ፍዝዝ አልሽ እኮ!» አለችኝ፣ ብይ እሚመስሉ ዓይኖቿን እያንከራተተች።«በየትኛው ደረጃዬ መልዓክ እንዳይ እንደተፈቀደልኝ ሳስብ ነበር» አልኳት። ፈገግታ እሸለምኳት።«አታሽኮርምሚኝ እንጂ!» ብላ ስታቀረቅር፣ አወይ! ስርጉዶቿ ማማራቸው! ፀሐይ ለምን ያለሰዓቷ እንዲህ እንደተቆጣች ገባኝ፤ ለካስ ቅናት ብጤ ሸንቆጥ አድርጓት ነው የሚል ሙገሳ ብጤ ጣል አድርጌባት፣ ተሳስቀን ወደ መኖሪያ ቤቷ አመራን። ደራሲ✍🦋zewa🦋

Repost from N/a
የአረብኛ ቋንቋ በነፃ መማር ትፈልጋላችሁን?   መልሳችሁ áŠ á‹Žâœ… ከሆነ  ይሄ ማስታወቂያ ለናንተ ነው 🫵 🚨ከናንተ ሚጠበቀው ቻናሉን ተቀላቅሎ መማር ብቻ ነው👇 https://t.me/abuyusuf1595

Repost from N/a
🚨ፈጥኖ ማን ይመልስ ‼️🏃‍➡️🏃‍➡️ ትክክለኛውን  መልስ ያገኝ ሰው  ብዙ  ጠቃሚ ኢስላማዊ ቻናሎችን add የሚለውን በመጫን ያገኛል ። Free promoter👉 @selluhi 👉ጥያቄ፦  ቁርዓን ስንት ምዕራፍ አለው⁉

🔥የ ድል ረመጥ 🔥 የ ተሰኘው ልብ ወለድ የ መጀመሪያ ክፍል ነገ 1:30 ይለቀቃል ❤️‍🔥 ለወዳጆቻቹ share በማረግ ይጠብቁን ....
🔥የ ድል ረመጥ 🔥 የ ተሰኘው ልብ ወለድ የ መጀመሪያ ክፍል ነገ 1:30 ይለቀቃል ❤️‍🔥
ለወዳጆቻቹ share በማረግ ይጠብቁን
....

የሰይድ አበራሙዝ ሃሪማ መስጂድ ግንባታ ሃሪማችንን ባማረ ሁኔታ ግንባታ ተጀምሮዎል በዚህ ግንባታ ላይ መስተፋ የምትፈልጉ እህት ወንድሞች በባንክ አካውንት 1000733515817 የቻላቹትን አውጡ ማደግ
+1
የሰይድ አበራሙዝ ሃሪማ መስጂድ ግንባታ ሃሪማችንን ባማረ ሁኔታ ግንባታ ተጀምሮዎል በዚህ ግንባታ ላይ መስተፋ የምትፈልጉ እህት ወንድሞች በባንክ አካውንት 1000733515817 የቻላቹትን አውጡ ማደግ የፈለገ መሻይሆችን መድረሳዎችን አሊሞች ላይ ይበርታ አላህ ሁላቹንም ይቀበለን ሀጃችን ይውጣ

Repost from N/a
✅😀☂☄ን ፈተ🌪👀👀❓ ✅ስንት ቁ✅ር ☄ታያችኋል❓ 🅰️🅰️🅰️ 📌✅ 𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥⤵ 💎𝐖𝐚𝐯𝐞 :-@HudHud_waver🇵🇸
✅😀☂☄ን ፈተ🌪👀👀❓ ✅ስንት ቁ✅ር ☄ታያችኋል❓ 🅰️🅰️🅰️ 📌✅ 𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥⤵ 💎𝐖𝐚𝐯𝐞 :-@HudHud_waver🇵🇸

☔️ለክረምት የሚነበቡ ምርጥ ኢስላሚክ ታሪክ ትፈልጋላችሁ⁉️ 👇🏽ከስር ነክተው በምርጥ ታሪኮች ይደሰቱ👇🏽 😊ወላሒ ሐቂቃ ማስታወቂያ ነው😊
☔️ለክረምት የሚነበቡ ምርጥ ኢስላሚክ ታሪክ ትፈልጋላችሁ⁉️ 👇🏽ከስር ነክተው በምርጥ ታሪኮች ይደሰቱ👇🏽 😊ወላሒ ሐቂቃ ማስታወቂያ ነው😊

Repost from N/a
ኢስላማዊ ታሪኮች ዲናዊ ምክሮች የተለያዩ ዳዓዋዎችን ቁርዓን እና ሀዲስ የምታገኙበት 🧩 áˆáˆ­áŒĽáŠ“ ተወዳጅ ቻናል ✨       # ተቀላቀሉ ✅👇 https://t.me/+KXmTq2tJLzxjYzQ0

Repost from N/a
ኢስላማዊ ታሪኮች ዲናዊ ምክሮች የተለያዩ ዳዓዋዎችን ቁርዓን እና ሀዲስ የምታገኙበት 🧩 áˆáˆ­áŒĽáŠ“ ተወዳጅ ቻናል ✨       # ተቀላቀሉ ✅👇 https://t.me/+KXmTq2tJLzxjYzQ0