en
Feedback
"እንዴት ልዋብ?"

"እንዴት ልዋብ?"

Open in Telegram

ይህ የ"እንዴት ልዋብ?" መድረክ ቤተሰቦች ቻናል ነው። "እንዴት ልዋብ?" በሙስሊም ሴቶች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የሚሰናዳ ዝግጅት ሲሆን ቤተሰብን በዚህ ቻናል ተደራሽ ያደርጋል። https://quizzory.in/id/6975050d98cfb14a2c61331c. Muslim women network Form

Show more
613
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+3330 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+19
in 0 channels
August '26
+26
in 1 channels
Get PRO
July '26
+13
in 0 channels
Get PRO
June '26
+30
in 0 channels
Get PRO
May '26
+26
in 0 channels
Get PRO
April '26
+5
in 0 channels
Get PRO
March '26
+16
in 0 channels
Get PRO
February '26
+47
in 0 channels
Get PRO
January '26
+16
in 1 channels
Get PRO
December '25
+83
in 1 channels
Get PRO
November '25
+50
in 0 channels
Get PRO
October '25
+153
in 1 channels
Get PRO
September '25
+4
in 1 channels
Get PRO
August '25
+227
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
10 September0
09 September+1
08 September+4
07 September0
06 September+1
05 September0
04 September+2
03 September+4
02 September+6
01 September+1
Channel Posts
የረቢዕ ማስታወሻዎች 28 አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡- “አንድ ሰው ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ቀረበና ችግር ደርሶብኛል (ተርቤያለሁ፣ ተጠምቻለሁ፣ ታርዣለሁ)› አላቸው፡፡ ከሚስቶ
የረቢዕ ማስታወሻዎች 28 አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡- “አንድ ሰው ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ቀረበና ችግር ደርሶብኛል (ተርቤያለሁ፣ ተጠምቻለሁ፣ ታርዣለሁ)› አላቸው፡፡ ከሚስቶቻቸው ወደ አንዷ, ቤት (አንዳች የሚቀመስ ነገር ትልክ ዘንድ) ላኩባት። ‹በእውነት በላከዎት አምላክ እምላለሁ! ከውሃ በቀር ምንም ነገር የለኝም› አለች። ከዚያም ወደሌላዋ (ሚስታቸው) ላኩ እርሷም ተመሳሳይ መልስ ሰጠች። (ከሁሉም የነቢዩ ሰ.ዐ.ወ ሚስቶች) ዘንድ ተላከ። መልሳቸው ተመሳሳይ ሆነ። ‹በእውነት በላከዎት እምላለሁ! ከውሃ በቀር ከኔ ዘንድ ምንም ነገር የለም!› ‹(ይህን እንግዳ) ዛሬ ማን ያስተናግዳል?› በማለት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) (ባልደረቦቻቸውን)ጠየቁ፡፡ ከአንሷሮች መካከል አንዱ፡- ‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እኔ አስተናግደዋለሁ› አላቸው፡፡ ከዚያም ወደ ቤቱ ይዞት ሄደ። ለባለቤቱም የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንግዳ በጥሩ ሁኔታ አስተናግጂ› አላት፡፡ በሌላ ዘገባ እንደተመለከተው ‹አንዳች (የሚበላ) ነገር አለሽን?› በማለት ጠየቃት። ‹ከሕጻናቱ ምግብ በስተቀር ምንም ነገር የለኝም, አለችው። ‹እነርሱን በአንዳች ነገር አታሊያቸው፡፡ እራት ሲፈልጉ ደግሞ (አባብለሽ) አስተኚያቸው፡፡ እንግዳችን ሲመገብ መብራቱን አጥፊው እኛ የምንመገብ እንዲመስለውም አድርጊ› አላት። ተቀመጡ እንግዳውም ተመገበ። እነርሱ ግን ጾማቸውን አደሩ። ሲነጋ ማልደው ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሄዱ። ነቢዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹አንተና ባለቤትህ በዚህች ሌሊት ለእንግዳችሁ በፈፀማችሁት መስተንግዶ አላህ እጅግ ተደስቷል› አሉ፡፡” (ቡኻሪና ሙስሊም) ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1

2
የረቢዕ ማስታወሻ 27 ۞ وَعَنَتِ الْوُجُوهُ لِلْحَيِّ الْقَيُّومِ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنْ حَمَلَ ظُلْمًا «ፊቶችም ሁሉ ሕያው እና አስተናባሪ ለሆነው (አላህ
የረቢዕ ማስታወሻ 27 ۞ وَعَنَتِ الْوُجُوهُ لِلْحَيِّ الْقَيُّومِ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنْ حَمَلَ ظُلْمًا «ፊቶችም ሁሉ ሕያው እና አስተናባሪ ለሆነው (አላህ) ተዋረዱ። (በዚያን ቀን) በደልንም የተሸከመ ሰው በርግጥ ከሠረ።»( ጣሀ 111) ከሺርክ ቀጥሎ አላህ (ሱ.ወ.) እንደ በደል የሚጠላው ነገር የለም።አላህ በደልንም በዳዮችንም ይጠላል፤ አላህ በደልንና በዳይን የሚጠላ ስለመሆኑ ከማሳያዎች መካከል፦ የተበደለ ካፊር በበደለው ሙስሊም ላይ የሚያደርገው ዱዓእ ተቀባይነት አለው። ግና በዚህን ጊዜ አላህ የካፊርን ዱዓእ የሚቀበለው ካፊሩን ወዶ አይደለም፤ ወይም ሙስሊሙን ጠልቶ አይደለም። ነገርግን ፍትሕን ስለሚወድና በደልንም ስለሚጠላ እንጂ! ሸይኽ ኢብኑ ተይሚየህ እንዲህ ብለዋል፦"አላህ ፍትሓዊ የሆነችውን የካፊር መንግሥት በዳይ በሆነችው ሙስሊም መንግሥት ላይ ይረዳል።" ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
176
3
ውዴታችንን አንደብቅ «አንድ ሰው በነቢዩ [ﷺ] አጠገብ አለፈ። በእርሳቸው አጠገብ አንድ ሰው ተቀምጦ ነበር። ሰውየው እንዲህ አለ: ‐ «የአላህ መልክተኛ ሆይ እኔ ይህንን ሰው ለአላህ ብዬ እወደዋለሁ
ውዴታችንን አንደብቅ «አንድ ሰው በነቢዩ [ﷺ] አጠገብ አለፈ። በእርሳቸው አጠገብ አንድ ሰው ተቀምጦ ነበር። ሰውየው እንዲህ አለ: ‐ «የአላህ መልክተኛ ሆይ እኔ ይህንን ሰው ለአላህ ብዬ እወደዋለሁ።» የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ አሉ: ‐ «ነግረኸዋልን?!»ሰውየው«አላሳወቅኩትም።» በማለት መለሰ። «ተነስና ንገረው። ውዴታችሁ ይፀናል።» አሉት።ሰውየውም ከተቀመጠበት ተነሳና ተከትሎት በመሄድ ነገረው። «እኔ ለአላህ ብዬ እወድኻለሁ።» አለው። ሰውየውም: ‐ «ለርሱ ብለህ የወደድከኝ አላህ ይውደድህ።» በማለት መለሰ።» አቡዳዉድ እና ነሳኢይ አነስ ኢብኑ ማሊክን [ረዲየላሁ ዐንሁ] በመጥቀስ ዘግበውታል። ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
388
4
የረቢዕ ማስታወሻ 23 ‹‹ትእግስት በመጀመሪያው የመከራ ቅጽበት ላይ ነው፡፡›› በቀብር ጉብኝት (ዚያራ) ወቅት ይደረጉ የነበሩ የመሐይምነት( ጃሒሊያ) ድርጊቶችንና ልምዶችን ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ባዩ ጊ
የረቢዕ ማስታወሻ 23 ‹‹ትእግስት በመጀመሪያው የመከራ ቅጽበት ላይ ነው፡፡›› በቀብር ጉብኝት (ዚያራ) ወቅት ይደረጉ የነበሩ የመሐይምነት( ጃሒሊያ) ድርጊቶችንና ልምዶችን ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ባዩ ጊዜ ሙእሚኖችን ከቀብር ዚያራ ከለከሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን እንደገና እንዲህ በማለት ፈቀዱ፡- ‹‹ቀብር እንዳትዘይሩ ከልክያችሁ ነበር፡፡ ለሙሐመድ የእናቱን ቀብር እንዲዘይር ተፈቅዶለታል፡፡ ስለሆነም መቃብሮችን ዘይሩ፡፡ መጭውን ዓለም ያስታውሷችኋልና፡፡›› የሰውን ልጅ ከረዥም ምኞት የሚያነቃ ትምህርት ከመቃብሮች ይገኛል፡፡ የአላህ መልእክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ቀብር አዘውትረው ይጎበኙ ነበር፡፡ የኡሁድ ሸሂዶችን ቀብር ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜ ይጎበኙ ነበር፡፡ አነስ እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በአንድ መካነ መቃብር አጠገብ ሲያልፉ አንዲት እንስት ከአንድ ቀብር አጠገብ ሆና ስታለቅስ አገኟት፡፡ ‹‹አላህን ፍሪ፣ ታገሽም›› አሏት፡፡ ‹‹ከአጠገቤ ዘወር በል፡፡ እኔን ያገኘኝ መከራ አንተን አላገኘህም፡፡ ስለዚህ (ሕመሜን) አታውቀውም›› አለች፡፡ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) መሆናቸው ሲነገራት ደነገጠች፡፡ ወደቤታቸውም መጣች፡፡ ‹‹ስላላወቅኩዎት ነው›› አለቻቸው፡፡ ‹‹ትእግስት በመጀመሪያው የመከራ ቅጽበት ላይ ነው›› አሏት፡፡ በአራት ቃላት ብዙ ቅጽ ማብራሪያዎች የሚያስፈልጉት መልዕክት ነገሯት፡፡ ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
402
5
«አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፤ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፤ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ።» (ሱረቱ አል-አሕዛብ 33:56) ا
«አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፤ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፤ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ።» (ሱረቱ አል-አሕዛብ 33:56) اَللّٰهُمَّ صَلِّ عَلَىٰ مُحَمَّدٍ وَّعَلَىٰ اٰلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيْمَ وَعَلَىٰ اٰلِ إِبْرَاهِيْمَ، إِنَّكَ حَمِيْدٌ مَّجِيْدٌ. اَللّٰهُمَّ بَارِكْ عَلَىٰ مُحَمَّدٍ وَّعَلَىٰ اٰلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيْمَ وَعَلَىٰ اٰلِ إِبْرَاهِيْمَ، إِنَّكَ حَمِيْدٌ مَّجِيْدٌ. መልካም ጁምዓ ይሁንላችሁ "እንዴት ልዋብ?" ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
267
6
የረቢዕ ማስታወሻ 21 ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በአንድ ወቅት ፍየል አረዱ። ከዚያም “የትኛው የአካል ክፍሏ ቀረ?" አሏት እርሷም ትከሻዋ ብቻ እንጂ የቀረ ሥጋ የለም ሁሉም
የረቢዕ ማስታወሻ 21 ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በአንድ ወቅት ፍየል አረዱ። ከዚያም “የትኛው የአካል ክፍሏ ቀረ?" አሏት እርሷም ትከሻዋ ብቻ እንጂ የቀረ ሥጋ የለም ሁሉም ተመጽውቷል” በማለት መለሰች። እርሳቸውም “ከትከሻዋ ውጭ ያለው ሁሉ ቀርቷል(ተርፏል)” አሏት። (ቲርሚዚ) ይህን ሐዲስ ልብ ብለን እናስተውል። ዓኢሻ (ረ.ዐ) ሌሎች ሥጋዎች ተመጽውተው ትከሻዋ ብቻ እንደቀረ ነገረቻቸው፡፡ እርሳቸው ግን እርሱ ሲቀርሌሎች ሥጋዎች እንደተረፉ መለሱላት። በዚህ አገላለጽ _ ማመልከት የፈለጉት አንድ ሰው እውነተኛ ሃብቱና ትርፉ ለራሱ የተመገበው ወይም የተጠቀመበት ሳይሆን የመጸወተው መሆኑን ነው፡፡ ምክንያቱም ለራስ ፍጆታ ያዋሉት ወይም የተመገቡት ጠቀሜታው ለዚህች ዓለም ብቻ ነው ሲያልፍ ያልፋል። ለምጽዋት የዋለው ግን ምንዳ ያስገኛል። እናም ለመጪው ዓለም አልፎ ይቆያል። ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
387
7
ውድ የ"እንዴትልዋብ?" ቤተሠቦች 13ኛ መድረካችንን በተለያየ ምክንያት መገኘት ላልቻላችሁ አሁን በሚንበር ቲቪ በመተላለፍ ላይ ስለሆነ እንድትከታተሉት በአክብሮት ጋብዘናችኋል።
ውድ የ"እንዴትልዋብ?" ቤተሠቦች 13ኛ መድረካችንን በተለያየ ምክንያት መገኘት ላልቻላችሁ አሁን በሚንበር ቲቪ በመተላለፍ ላይ ስለሆነ እንድትከታተሉት በአክብሮት ጋብዘናችኋል።
308
8
የረቢዕ ማስታወሻዎች 20 ከእናታችን ዓኢሻ (ረድየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፦ «በአካሄድ፣ በሥነ-ምግባርና በጠባይ ከፋጢማ [ረዲየላሁ ዐንሃ] የበለጠ የአላህ መልእክተኛን [ﷺ] የሚመስል
የረቢዕ ማስታወሻዎች 20 ከእናታችን ዓኢሻ (ረድየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፦ «በአካሄድ፣ በሥነ-ምግባርና በጠባይ ከፋጢማ [ረዲየላሁ ዐንሃ] የበለጠ የአላህ መልእክተኛን [ﷺ] የሚመስል ሰው አላየሁም። ፋጢማ ነቢዩ [ﷺ] ዘንድ ሲገቡ እርሳቸው ይነሱላት ነበር፣ እጇንም ይይዙና ይስሙት ነበር፤ ከዚያም በተቀመጡበት ስፍራ ላይ ያስቀምጧት ነበር። እርሳቸው [ﷺ] እርሷ ዘንድ በገቡ ጊዜም ከተቀመጠችበት ትነሳላቸው ነበር፣ እጃቸውን ትይዝና ትስማቸው ነበር፤ ከዚያም በመቀመጫ ስፍራዋ ላይ ታስቀምጣቸው ነበር።» ይህን ሐዲስ አቡዳዉድ እና ሌሎችም ዘግበውታል። ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
290
9
የረቢዕ ማስታወሻ 19 የአላህ ነቢይ [ﷺ] የመጀመሪያውን ወሕይ ከተቀበሉ በኋላ በፍርሃት ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ እናታችን ኸዲጃ [ረዲየላሁ ዐንሃ] እንዲህ በማለት አጽናናቻቸው፦ «كَلَّا وَاللّ
የረቢዕ ማስታወሻ 19 የአላህ ነቢይ [ﷺ] የመጀመሪያውን ወሕይ ከተቀበሉ በኋላ በፍርሃት ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ እናታችን ኸዲጃ [ረዲየላሁ ዐንሃ] እንዲህ በማለት አጽናናቻቸው፦ «كَلَّا وَاللَّهِ لَا يُخْزِيكَ اللَّهُ أَبَدًا...» «በፍጹም አይሆንም! በአላህ እምላለሁ፣ አላህ ፈጽሞ አያዋርድህም፤ ዝምድናን ታፀናለህ፣ እንግዳን ታከብራለህ፣ ችግረኞችን ትረዳለህ፣ በእውነተኛ መንገድ ላይ በሚደርሱ ድንገተኛ መከራዎች ላይም ሰዎችን ታግዛለህ።»… ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። ©©© ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
343
10
የረቢዕ ማስታወሻ 18 አስማ (ረ.ዐ) በኡሁድ ዘመቻ ወቅት ወንድሟ፣ ባሏ፣ አባቷ እና ልጇ በሸሂድነት እንደወደቁ ሲነገራት «ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ደህና ናቸውን?» ስትል ጠየቀች። «አልሐምዱ ሊላህ እርሳ
የረቢዕ ማስታወሻ 18 አስማ (ረ.ዐ) በኡሁድ ዘመቻ ወቅት ወንድሟ፣ ባሏ፣ አባቷ እና ልጇ በሸሂድነት እንደወደቁ ሲነገራት «ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ደህና ናቸውን?» ስትል ጠየቀች። «አልሐምዱ ሊላህ እርሳቸው ደህና ናቸው» ሲሏት፡ ​«እርሶ ደህና ከሆኑ ከእርሶ በኋላ የሚመጣ ማንኛውም መከራና ጭንቅ ለእኔ ቀላል ነው!» («ኩሉ ሙሲበቲን ባዕደከ ጃለል») ​ብላ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በሰላም ስታያቸው ልቧ የታገሰና ለአላህ መልእክተኛ የነበራትን ጥልቅ ፍቅር ያሳየች ታላቅ ሴት ናት ቻናላችንን በመቀላቀል ቤተሠብ ይሁኑ! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
401
11
ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ለአላህ ይሁን! ውድ የ"እንዴት ልዋብ?" ቤተሰቦቻችን የዛሬው 13ኛ መድረካችን ባማረ መልኩ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት በድምቀት ተካሒዶ አልፏል:: መድረኩን የተሳተፋችሁ፤በማስ+7
ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ለአላህ ይሁን! ውድ የ"እንዴት ልዋብ?" ቤተሰቦቻችን የዛሬው 13ኛ መድረካችን ባማረ መልኩ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት በድምቀት ተካሒዶ አልፏል:: መድረኩን የተሳተፋችሁ፤በማስተወዋወቅ ለሌሎች ያደረሳችሁ እንዲሁም ስፖንሰር በማድረግ ከጎናችን ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችን ከልብ ነው። በቀጣይ በ"እንዴት ልዋብ?"14 የምንገናኝ ይሆናል ኢንሻአላህ! ሌሎች ፕሮግራሞቻችን ለመሳተፍ የቴሌግራም ፌስቡክ እና ቲክቶክ አድራሻዎቻችንን ፎሎው አድርጉ እናመሠግናለን !! Telegram @endetlewab1 TikTok https://www.tiktok.com/@muslim.women.netw?_r=1&_t=ZS-99JowEJZeN8 Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=61573007426748
611
12
ዝግጅታችንን ጨርሠን እየጠበቅናችሁ ነው።ነገ ጠዋት በአምባሳደር ቲያትር ከጠዋት 3፡00-6:30 የነፃነት መንገድ ልዩ መድረካችን በድምቀት ይካሔዳል:: መግቢያ በነፃ
ዝግጅታችንን ጨርሠን እየጠበቅናችሁ ነው።ነገ ጠዋት በአምባሳደር ቲያትር ከጠዋት 3፡00-6:30 የነፃነት መንገድ ልዩ መድረካችን በድምቀት ይካሔዳል:: መግቢያ በነፃ
645
13
No text...
286
14
የረቢዕ ማስታወሻ 15 የአላህ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ) የሚከተለውን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፡- “ሶደቃ (ምጽዋት) ገንዘብን አታጎድልም። ይቅር ባይ የሆነ ሰው አላህ ክብርን እንጂ
የረቢዕ ማስታወሻ 15 የአላህ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ) የሚከተለውን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፡- “ሶደቃ (ምጽዋት) ገንዘብን አታጎድልም። ይቅር ባይ የሆነ ሰው አላህ ክብርን እንጂ አይጨምርለትም። አንድ ሰው ለአላህ ብሎ ራሱን ዝቅ አያደርግም (አይተናነስም) ሃያልና ልዑል የሆነው አላህ ከፍ ያደረገው ቢሆን እንጂ።” (ሙስሊም) ቸር መሆንና የለጋስነት ባሕሪ የአላህንና የሰዎችን ፍቅር ያስገኛል። ዓሊ ኢብን አቡ ጣሊብ (ረ.ዐ) “ሃይማኖት ልክ እንደ ዛፍ ሲሆን ሥሩ ጠንካራ እምነት ነው። ቅርንጫፉ ተቅዋ (አላህን መጠንቀቅ)፣ ቅጠሉ ሐያእ፣ ፍሬው ደግሞ ለጋስነት ነው።" ማለታቸው ለዚህ ነው። አስማእ ቢንት አቡበክር (ረ.ዐ) የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) የሚከተለውን ነግረውኛል በማለት አስተላልፋለች፡- “(ገንዘብሽን) ቋጥረሽ ምጽዋት አትከልከይ፡፡ አላህ (እርሱ ዘንድ ያለውን ሲሳይ) ይከለክልሻልና።” በሌላ ዘገባ ደግሞ “መጽውች አትያዥ (አታከማቺ)። አላህ (ከርሱ ዘንድ ያለውን ጸጋና ሲሳይ) ይይዝብሻልና። አትቋጥሪ አላህም ይቋጥርብሻልና” እንዳሏት ተጠቅሷል። "እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
679
15
"እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ መልካም ጁምአ ይሁንላችሁ!
"እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ መልካም ጁምአ ይሁንላችሁ!
400
16
የረቢዕ ማስታወሻ 14 ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ማክበር (ሐያእ ማድረግ) የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦቻቸው እንዴት ያከብሯቸው እንደነበር ለማወቅ _ አንዱ _ ባልደረባቸው (አላህ _ ሥራውን
የረቢዕ ማስታወሻ 14 ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ማክበር (ሐያእ ማድረግ) የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦቻቸው እንዴት ያከብሯቸው እንደነበር ለማወቅ _ አንዱ _ ባልደረባቸው (አላህ _ ሥራውን ይውደድለትና) የተናገረውን ማየቱ ይበቃል “በአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ዙሪያ ስንቀመጥ ጸጥ ከማለታችን የተነሳ በጭንቅላታችን ላይ ወፎች ያረፉብንና እንዳይበሩ የምንሰጋ ይመስል ነበር።” (አቡ ዳውድ ኢብኑ ማጃህ) የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦቻቸው ከልብ ያከብሯቸውና ይጠነቀቁላቸው ነበር ፊታቸውን ደፍረው የሚመለከቱ ባልደረቦቻቸው በጣም በቁጥር  ጥቂት ነበሩ። አቡበክር (ረ.ዐ) እና ዑመር (ረ.ዐ) ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ኹጥባ ሲያደርጉ በቀጥታ ፊታቸውን አይመለከቱም ነበር። ግብጽን የከፈተው ዝነኛ ሶሃባ ዐምር ኢብን አል-ዐስ (ረ.ዐ) እንዲህ ይላል፡- “ከአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) የበለጠ ክቡርና በእኔ አይን የተላቀ ሰው የለም። በዚህም የተነሳ ፊታቸውን በሙሉ ዐይኔ ተመልክቼ የማላውቅ በመሆኑ መልካቸው ምን እንደሚመስል ብጠየቅ መናገር አልችልም። ምክንያቱም በሙሉ ዐይኔ አይቻቸው አላውቅማ!” (ሙስሊም 192) ኃያሉ አላህ እንዲህ የመሰሉ ፊታቸው እንደ ጨረቃ ቁራጭ የሚያበራ የሆነ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ) ነው የሰጠን፡፡ አዘወትረንም በእርሳቸው ላይ ሰለዋትና እዝነት እንድናወርድባቸውም ያዘናል "እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
542
17
የረቢዕ ማስታወሻ 13 ኢብኑ ጁናዳህ (ረ.ዐ) እና ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል “የትም ብትሆን አላህን ፍራ፡፡ መጥፎ ሥራህን በመልካም ተግባር አስከትል ሃጢአትህን ታብስልሃለችና። ከሰዎ
የረቢዕ ማስታወሻ 13 ኢብኑ ጁናዳህ (ረ.ዐ) እና ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል “የትም ብትሆን አላህን ፍራ፡፡ መጥፎ ሥራህን በመልካም ተግባር አስከትል ሃጢአትህን ታብስልሃለችና። ከሰዎች ጋር ያለህም ግንኙነት ግብረገባዊ ይሁን።” ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል፡- “አንድ ዕለት ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ኋላ ነበርኩ። እንዲህም አሉኝ፡- “አንተ ልጅ እኔ ጥቂት ቃላትን ላስተምርህ። የአላህን ትዕዛዝ ጠብቅ እርሱ ይጠብቅሃልና። አላህን ጠብቀው ከፊት ለፊትህ ታገኘዋለህና። ስትጠይቅ አላህን ጠይቅ። እርዳታን ከፈለግህ በአላህ ተረዳ። ሕዝቦች ሁሉ ሊጠቅሙህ ቢሰበሰቡ አይጠቅሙህም አላህ በርግጥ የወሰነልህ ነገር ሲቀር። ሊጎዱህ ቢሰበሰቡ ሊጎዱህ አይችሉም አላህ በእርግጥ በአንተ ላይ የወሰነብህ ቢሆን እንጂ። ብዕሮች ተነስተዋል ገጾችም ደርቀዋል።" በሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ የሚል ተመልክቷል፡- “አላህን ጠብቀው ከፊትህ ታገኘዋለህ። ከአላህ ጋር በሰላም ጊዜ ተዋወቅ በችግር ጊዜ ዕውቅና ይሰጥሃልና። ያላጋጠመህ ነገር ሊደርስብህ ያልነበረና የደረሰብህ ነገር ደግሞ የሚያልፍህ እንዳልነበር ዕወቅ፡፡ ድል ከትዕግስት ጋር እርካታ ከጭንቅ ጋር ችግርም ከምቾት ጋር መኖሩን ዕወቅ።" "እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
346
18
የረቢዕ ማስታወሻ 12 የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ ሰምቻለሁ በማለት ዓኢሻ (ረ.ዐ) አስተላልፋለች፡- “ሙእሚን በመልካም ሥነ-ምግባር የጿሚዎችና የቋሚዎችን (የሰጋጆችን) ደረጃ ያ
የረቢዕ ማስታወሻ 12 የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ ሰምቻለሁ በማለት ዓኢሻ (ረ.ዐ) አስተላልፋለች፡- “ሙእሚን በመልካም ሥነ-ምግባር የጿሚዎችና የቋሚዎችን (የሰጋጆችን) ደረጃ ያገኛል።” አቡ ኡማመተል ባሂሊይ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “እውነተኛ እንኳን ቢሆን ክርክርን የተወ ከጀነት ዳርቻ ላይ ለቀልድም እንኳን ቢሆን የማይዋሽ ከጀነት እንብርት ላይ፣ የመልካም ሥነ-ምግባር ባለቤት ደግሞ ከጀነት የላይኛው ክፍል ቤት እንደሚያገኙ ዋስትና እሰጣቸዋለሁ።” (አቡ ዳውድ) ጃቢር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-“በዕለተ ቂያማ ከእኔ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅና ቦታቸውም ወደኔ ቀረብ የሚለው ከመካከላችሁ በሥነ-ምግባር ይበልጥ መልካሞቹ ሲሆኑ ከእኔ ዘንድ ይበልጥ የተጠሉና ከእኔ በጣም የሚርቁት አላስፈላጊ ንግግር የሚያበዙና በንግግራቸው በሌሎች ላይ የሚኮፈሱ እንዲሁም የተወጠሩት ናቸው” በማለት ተናገሩ፡፡ ባልደረቦቻቸውም “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! የሁለቱን ማንነት አውቀናል የተወጠሩ የሚባሉት እነማን ናቸው? ሲሉ ጠየቋቸው “ትዕቢተኞች (ኩራተኞች)" ሲሉ መለሱ፡፡ (ቲርሚዚ) "እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
474
19
"እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
"እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
638
20
የረቢዕ ማስታወሻ 11 የሰው ልጅ በዚህች ምድር ሲኖር ላይና ታች እያለ በተዓብ (መከራ) ሕይወቱን መግፋት ዕጣ ፋንታው ነው። በውስጡ የመከራ ቅንጣቢዎችን ተሸክሞ እንደመኖሩ ለፈገግታና ፊቱን ፈታ ለማ
የረቢዕ ማስታወሻ 11 የሰው ልጅ በዚህች ምድር ሲኖር ላይና ታች እያለ በተዓብ (መከራ) ሕይወቱን መግፋት ዕጣ ፋንታው ነው። በውስጡ የመከራ ቅንጣቢዎችን ተሸክሞ እንደመኖሩ ለፈገግታና ፊቱን ፈታ ለማድረግ የሚያስችሉት በርካታ ምክንያቶችም ሞልተዋል። ስለሆነም ህገ-ኢስላም የሰው ዘር ይህችን ዓለም የሳቅና የሁከት ካዝና እንዲያደርጋት ባይጠበቅበትም ለሕይወቱ እንደ ጨውና ቅመም ያህል የሚያገለግለው ፈገግታ ቢላበስ ከጽድቅ ቢቆጠርለት እንጂ ከቶም ተወቃሽ አያደርገውም። የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በነቢይነት ከተላኩ ጀምሮ በርካታ የሃዘን አጋጣሚዎችንና ቅስምን እንክትክት አድርገው የሚሰባብሩ ትዕይንቶችን ቢያስተናግዱም  ከቶም ፈገግታ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ አያውቅም። ይህንንም በራሳቸው አንደበት “በአላህ መንገድ ላይ እንደኔ መከራን የተቀበለ የለም” በማለት ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ያ ሁሉ የመከራ ውርጅብኝ የሕይወት ሚዛናቸውን ጠብቀው እንዳይጓዙ አላደረጋቸውም። ምንም እንኳን ውስጣቸው በሃዘንና በትካዜ የተሞላ ቢሆንም ፊታቸው ላይ እንደ ንጋት ፀሐይ የሚበራ ፈገግታ ጠፍቶ አያውቅም ማንኛውም ሰው በሚያጋጥመው መልካም ነገር እንደሚደሰት ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህን ስሜቱን በቅጡ በመያዝ አላህን ማመስገን ብሎም ፀጋውን ለታለመለት ዓላማ ማዋል ይጠበቅበታል። ሙስሊም በምድራዊ ሕይወቱ በሚገጥሙት መከራዎች ተስፋ ቆርጦና ተበሳጭቶ ከፈጣሪው መንገድ መውጣቱ መልካም ያለመሆኑን ያህል ቅጥ ባጣ ደስታ መዘፈቁም የዚያኑ ያህል ዋጋ በማስከፈል ክብሩንና የመጪውን ዓለም ሕይወቱን ያበላሽበታል። "እንዴት ልዋብ?"13 የነጻነት መንገድ በአምባሳደር ቲያትር እሑድ ነሀሴ 24 ከጠዋት 3፡00-6:30 መግቢያ በነፃ
524