en
Feedback
መራኁት

መራኁት

Open in Telegram

መራኁት ማለት መፍቻ፣ መክፈቻ፣ ቁልፍ ማለት ነው። ጥያቄዎቻችንን ቋጠሮአችንን በአባቶች ትምህርት እየፈታን አብረን እንጓዛለን። Tiktok: @mera_hut YouTube: @merahuut https://t.me/merahutchat

Show more
5 996
Subscribers
-124 hours
-127 days
-2830 days
Posts Archive
photo content

"ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም፤ ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ።" ማቴዎስ 4፥4 ነፍሳችን እንደ ሥጋችን ሁሉ ምግብ ትፈልጋለች። የሚያጸናት፣ የሚያበረታት፣ ወደ ክርስቶስ የሚያቀርባት ምግብ ግን የእግዚአብሔር ቃል ነው። ይህንን ሕይወት የሚሰጥ ቃል በልብ እና በተግባር ለማኖር የሚያግዙ መንፈሳዊ መጻሕፍት በቀሲስ ታምራት ውቤ ተዘጋጅተው ሊመረቁ ነው። ። 📅 ሐምሌ 5፣ 2018 ዓ.ም 🕗 ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ 📍 ቦሌ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን አዳራሽ #ቀሲስታምራትውቤ #EOTC #Sober #መጻሕፍትምረቃ #EpiphaniaTube

ይገርምላችኋል መጽሐፉ የኔ አይደለም🫣 አንድ ብርቱ ካህን ያዘጋጁት ነው የፊታችን ሐምሌ 11 ይመረቃል። pdf ላክልን ያላችሁ ግን ነፍሳችሁ አይማርም😂

ኸ!😁
+1
ኸ!😁

ነገ የታላቁን አባት የሙሴ ጸሊምን በዓል ከኛ ጋ ለማክበር ለወደዳችሁ ወዳጆቻችን አድራሻ በጠየቃችሁት መሠረት https://maps.app.goo.gl/nssc7NRatZ6yp6Ey6?g_st=ac አያት 49 እንደደረሱ ወደ አራብሳ የሚወስደውን አስፓልት ይዘዉ ቀጥታ ወደ 400 ሜትር አካባቢ እንደሄዱ በስተግራ በኩል “ የኩራ ጅዳ ደብረ ገነት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቅድስት አርሴማ ወሙሴ ጸሊም ቤተክርስቲያን “ የሚል ታፔላ ያገኛሉ ከዛዉ በዓለ ወልድ ብለው ባጃጅ ይዘው ቀጥታ ቤተክርስቲያኑ ያደርሱዎታል። ለበለጠ መረጃ በ 0941448030 ይደውሉ

+++ ጸሎት +++ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ›› ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ! አሁንም ጌታ ሆይ! በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡ ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር ፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅርኄህ የተነሣ እንደትረዳኝ እለምንሃለሁ፡ ጌታ ሆይ ‹‹ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል›› ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡  ‹‹ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም›› ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ!! አሜን!" ቅዱስ አቡነ ቄርሎስ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ሁሉ እግዚአብሔር በጎ የሆነውን ነገር ያድርግላችሁ። ጭንቀታችሁን በታመናችሁለት አምላክ ላይ ጣሉ። ቅዱስ አባታችን አቡነ ቄርሎስ ያዘጋጁላችሁን ጸሎት እነሆ አብረን እንጸልያለን።😊

እንኳን አደረሳችሁ ተወዳጆች😊 እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖርም እነዚህን መጻሕፍት እናስመርቃለን። የምንወዳቸው መምህራን ዲ/ን Bereket Azmeraw ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ Yaregal Abegaz
+1
እንኳን አደረሳችሁ ተወዳጆች😊 እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖርም እነዚህን መጻሕፍት እናስመርቃለን። የምንወዳቸው መምህራን ዲ/ን Bereket Azmeraw ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ Yaregal Abegaz ዲ/ን ኅሊና በለጠ ዳሰሳ እንደሚያቀርቡ ሰምተናል። መማር ለሚወድ ሰው ትልቅ ብፌ ነው። በዝማሬ አገልግሎትም ሲ/ር ሕይወትን ጨምሮ ሌሎች ተወዳጅ አገልጋዮች እንደሚኖሩ አውቀናል። ከነዚህ መምህራን ትምህርት ሱታፌ ለማድረግና ለዲ/ን ዮሐንስ ያለንን አክብሮት ለመግለጽ በቦታው እንገኛለን። አደራ ግብዣ ነው😊

ይሰማል?

photo content

መጽሐፍ ንባባችን ዛሬም ይቀጥላል፣ እየጠበቅናችሁ ነው። https://t.me/merahuut?livestream
መጽሐፍ ንባባችን ዛሬም ይቀጥላል፣ እየጠበቅናችሁ ነው። https://t.me/merahuut?livestream

የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ፦አቤቱ የሰራዊት ጌታ ሆይ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተማዎች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው አለ። (ዘካ 1:12) ሩሕሩሕ መልአክ፣ የኛ አማላጅ! ኢትዮጵያን የማትምራት እስከ መቼ ነው? በልልን

photo content

የመጽሐፍ ንባባችንን እንቀጥላለን https://t.me/merahuut?livestream

የመጽሐፍ ንባባችንን ለነገ ማታ 3 ሰዓት ብናዘዋውራትስ😊

የዚህ ጽሑፍ ሐሳብ በግርድፉ ሲተረጎም " መልካም ነገርን የምታደርግ ከሆነ ለእግዚአብሔር ብቻ ብለህ አድርገው። ስለዚህም የሰዎችን ምስጋና ቢስነት በጭራሽ አትመልከት። ከዚህ (ከምድር) ያልሆነ ከሰማይ ከጌታ ዘንድ የሆነ ሽልማትን ብቻ አስብ። ከምድር የምትጠብቅ እንደሆነ እንዲሁ በከንቱ ይሆናል ሳታገኘውም ትቀራለህ።" የሚል ነው። ይህም ድንቅ ሐሳብ ነው። ጌታን ብቻ አስቦ ከሰዎች ምንም ሳይጠብቁ መልካም ማድረግ ክርስቲያናዊ ጎዳና ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም "እውነተኛ ፍቅር ማለት መቀበል ሳይሹ መስጠት ነው" ያለው ይህንን ነው። እውነተኛ ፍቅር ይስጠን😊

Repost from Gracious ✝
photo content

የዲያብሎስ ውጊያዎች ክፍል 2.m4a8.23 MB

ከዛሬው ምንባብ ምን ተማራችሁ?☺️